Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62

በ2003 ዓ.ም ከግል ህይወቴ ስጀምር የመኖሪያ ቤቴ ጉዳይ ነው የሚመጣው፡፡ ወይ ቤቱ ይታደስ ወይ ተተኪ ሌላ ቤት ይሰጠኛል የሚል ተስፋ ነበረኝ፡፡ በ2003 ክረምት ቤቱ እየፈረሰ ነው፤ አሁን ያለሁበት አንዱ ክፍል እስከ መኝታ ቤቴ ድረስ ያፈሳል፤ ሌሊት ሳልተኛ ነው የማድረው፡፡ በግሌ ያጣሁት ይሄን ነው፡፡ በፖለቲካው ዘርፍ በድርጅቶቻችን በኩል አንዳንድ ነገሮችን ብንሰራም የሚፈለገውን ያህል አልተንቀሳቀስንም፡፡ በውስጥ መደራጀትና መገማገም ቢኖርም ከህዝብ ጋር ለመወያየትና ለመከራከር እድል አላገኘንም፡፡

በአጭር ጊዜ የሚታየኝ ተስፋ የለም
በ2003 አጣሁት የምለው ነገር የለም በግሌ፡፡ በአገሪቱ ግን የታጡ ብዙ ነገሮች አሉ፡፡ በደቡብ እና በደቡብ ምስራቅ የአገሪቱ ክፍሎች ድርቁ እና ረሀቡ እጅግ ተስፋፍቶ መሄዱ ያሳዝናል፡፡ መንግሥት ድርብ አሀዝ እድገት አምጥቻለሁ በሚልበት ሰዓት ይሄን ነገር መቋቋም አለመቻሉን ትልቅ ችግር እና እጦት አድርጌ አየዋለሁ፡፡ ሁለተኛው በተለይ የዋጋ ንረቱ የከተማውን ህዝብ ለረሀብ የዳረገው መሆኑ ነው፡፡ መንግስት ችግሩን መፍታት ተስኖት አንዴ የዋጋ ተመን ሌላ ጊዜ የተለያዩ ነገሮችን ሲሞክር በነጋዴውና በዜጋው ላይ ጥፋት ጉዳት አድርሷል፡፡ በአባላቶቻችን ላይ እስርና ወከባ መፈሙ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ምህዳር የባሰ መጥበቡን ያሳያል፡፡

በ2012 ኢኳቶርያል ጊኒና ጋቦን ወደ የሚያዘጋጁት የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ ሲደረግ በቆየው ዓመት የፈጀ የማጣርያ ውድድር በምድብ 2 ያለችው ኢትዮጵያ በ5ኛው ዙር ወደቀች፡፡ ከወር  በሚደረጉ የመጨረሻ ዙር ግጥሚያዎች ማጣርያው ሲገባደድ በታላላቅ ቡድኖች የሞት ሽረት ትግል ይታይበታል፡፡

በ13ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ በ7 ወርቅ፤ በ6 ብርና በ4 የነሐስ bxºÝላይ ከዓለም በሶስተኛ ደረጃ ያገባደደችው ኬንያ ከታላቆቹ አሜሪካና ራሽያ ተርታ መግባቷን የአገሪቱ ጋዜጦች አወሱ፡፡ በአንፃሩ ደካማ WºðT ያስመዘገበው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ቡድን  ከለንደን ኦሎምፒክ በፊት ስር ነቀል ለውጥ  እንደሚያስፈልገው እየተነገረ ነው፡፡ በዓለም ሻምፒዮናው በ47 የውድድር አይነቶች 1848 አትሌቶች 203 አገራትን በመወከል ተሳታፊ ሆነዋል፡፡

በአዲስ አበባ ስታድዬም በሚደርገው
የመልስ ጨዋታ የኢትዮጵያ ሴቶች ብሄራዊ ቡድን ከደቡብ አፍሪካ ይገጠማሉ”” ለሉሲ
በ4 ንፁህ ጎል ማሸነፍ ፤ ለባናያና አቻድልና በ2 ንህ ጎል መሸነፍ የለንደን
ኦሎምፒክ ትኬት የሚቆረጥባቸው እድሎችይሆናሉ ፡፡ ሁለቱ ቡድኖች ከሳምንት በፊት ስዌቶ በሚገኘው ኦርናልዶ ስታዲየም ተገናኝተው ባናያናዎች  3ለ0 በመርታታቸው የማለፍ እድላቸውን ቢያሰፉም፤ በሜዳቸው የሚጫወቱት ሉሲዎች ተመጣጣኝ ዕጣ ይዘዋል፡፡

..ያልተዳሰሱ ምስጢሮች.. ሲዳሰስ
ባለፈው ሳምንት ቢሮዬ የመጣልኝ    መሃፍ ለየት ያለ ነው፡፡ የመጽሐፉ ርዕስ ጉጉት የሚፈጥር     ዓይነት ነው፡፡ ..ያልተዳሰሱ ምስጢሮች.. ስለሚል ምስጢሮቹ     ምን ይሆኑ በሚል ለንባብ ይገፋፋል፡፡ መሃፉ በዲያቆን ኃ/ጊዮርጊስ ተፈራ የተዘጋጀነው፡፡ በርግጥ ደራሲው መጽሐፍ ለማሳተም አዲስ አይደለም፡፡ ከዚህ ቀደም ያሳተማቸው ስምንት መፃህፍት ያሉት ሲሆን በቅርቡ የሚያሳትማቸውን ሰባት መፃህፍት ዝርዝር በዚህኛው መሃፍ ጀርባ ላይ አስፍሯል፡፡ ቀደም ሲል ካሳተማቸው መካከል ..ክርስቲያናዊ ጋብቻ.. ቁጥር አንድና ሁለት፣ ..እውነተኛ ፆምና መንፈሳዊነት..፣ ..ነቅዕ ገነት (የነፃነት ምን´ የሚሉት ይጠቀሳሉ፡፡ በቅርቡ ከሚያሳትማቸው ውስጥ አንደኛው በእንግሊዝኛ ቋንቋ ሲሆን |Football and Spiritual life´ ይሰኛል፡፡

Saturday, 10 September 2011 12:14

የመጽሐፍትነገር

የዚህ ጽሑፍ ዓላማ በ2003 ዓ.ም ከመጽሐፍ
ጋር በተያያዘ ስለተፈጠሩ ክስተቶች ጥቂት ነገሮችን ለማንሳት እንጂ በዓመቱስለተከሰተው ነገር ሁሉ የተሟላ ዳሰሳ ለማቅረብ  አይደለም፡፡ ትኩረቴም     ፖለቲካና ታሪክ ነክ በሆኑት ላይ እንጂ፤ እንደ ልብ ወለድ ወይም የሥነልቦና መጻሕፍትን የመሳሰሉትን አላካተተም፡፡ በመጻሕፍቱ አጠቃላይ ኋና ላይ ካልሆነ የመጻሕፍቱን ግምገማንም የሚያካትት አይደለም፡፡
የመጻሕፍት ምርቃት

Saturday, 10 September 2011 12:03

የኔ ቢጤ

እኔ ላንቺ ግጥም
ቃላት ሣጠራቅም
አላዛር ከደዌው
ድኖ አገገመ
ስለዓለም ከንቱነት
ግጥም አሳተመ፡፡
ለውበትሽ ስንኝ
ፊደል አጥቼልሽ
በየመዘክሩ ስንከራተትልሽ
የእዮብ መከራ
ጭንቅ ዘመኑ አለፈ
..መታገስ ነው ደጉ!..
የሚል መጽሐፍ ፃፈ፡፡
እኔ ላንቺ ግጥም
ቃላት ሳጠራቅም
ውዲቷ አገራችን
እጅግ ተራቀቀች
በኤሌትሪክ ሽቦ
ፍቅር አስተላለፈች፡፡
ሰው ባገደመበት
ባለፈበት ስፍራ
ፍቅር አንፀባርቆ
መውደድ በአምፖል ሠራ፡፡
አንድ የተደበቀ
የተቀበረ ቃል
ድንገት ቢኖር ብዬ
ድንጋይ ስፈነቅል
የፍልስጤም ጉብል
ከእስራኤሏ ቆንጆ
ይቅር ተባብለው
ቀለሱልሽ ጐጆ፡፡
ያንቺነትሽን ምስጢር
ቅኔሽን አይቼ
እጽፍልሽ ነገር
እለው ቃል አጥቼ
ቃላት አልሳካ
ከቶ አልሰምር ብሎኝ
የነበረኝ እንኳ
ነጐደልሽ ጥሎኝ
እናም ስለማምላክ
እያልኩ እዞራለሁ
ካገር አገር እያልኩ
ቃል እለምናለሁ፡፡
ምልዕቲ ኪሮስ

Saturday, 10 September 2011 12:05

ወላጅ መጽናኛ!

ወላጅ መጽናኛ!
አንድ ዘመን ሄደ፣
አንድ ዘመን መጣ፣
በአንድ አመት አረጀሁ፣
በአንድ አመት ጐረመስኩ፣
በራሴ ሲያልፍብኝ፣
በልጄ እየደረስኩ፡፡
እምሻው ገ/ዮሐንስ
ሰው፣ ጊዜና ወርቅ!
በትውልድ እድገቱ
ኑሮውና ሞቱ
አድርጐ እንደ ጥላው
በእለትና ወራት
አመታት፣ ዘመናት
ቀምሮ እያሰላው
እንደ አፈር ቆንጥሮ
እንደ አፈር አንጥሮ
የሰው ልጅ ባይቀባው
የክብርን ቀለም፣
ከንቱ ውዳቂ እንጅ
በድን ለዘላለም
በሰው ካልተለካ
ጊዜ ወርቅ አይደለም፡፡  
እምሻው ገ/ዮሐንስ

Saturday, 10 September 2011 12:00

ታሪክን በስፖንሰር

ታሪክያለፈውንለመገምገምየሚመጣውን በወጉ ለመተለም     የሚያገለግላል የማኅበራዊ ሳይንስ መስክ ነው፡፡ የታሪክ ተመራማ ሪያን ወይም ጸሐፍቱ በልዩ ልዩ ምክንያቶች በተጽኖ ስር ሊወድቁ ስለሚችሉ ፍጹማዊ ወይም ትክክለኛ ታሪክ ለማግኘት አዳጋች ነው፡፡ ታሪክን ፍጹማዊ ማድረግ ባይቻል እንኳን ፍላጎቱና ገለልተኝነቱ ካለ የተለያዩ መረጃዎችን በመሰብሰብ፣ በማጥናት፣ ሚዛናዊነት በመጠበቅ እና ሳይንሳዊ ትንተናዎችን በማካተት የተጽኖዎችን ኃይል ቀንሶ ፍጹማዊ ባይሆንም የተሟላ ታሪክ ማቅረብ ይቻላል፡፡በኢትዮጵያ ከ50 ዓመታት ወዲህ ከተከናወኑት ክንውኖች መካከል በአንድ ወገን ብቻ ወደ 55 ሺህ የሚጠጉ ታጋዮችን ህይወት መስዋት ያደረገው ለ17 ዓመታት የተካሄደውን የትጥቅ ትግል የሚተርኩ መጽሐፍት እየወጡ ነው፡፡