Saturday, 09 March 2024 20:05

ረቂቁ የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ ለሕዝብ ቀርቦ እንዲተች ተጠየቀ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

በቅርቡ ይጸድቃል ተብሎ የሚጠበቀው ረቂቁ የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ፣ ለሕዝብ ቀርቦ ዜጎች ውይይት እንዲያደርጉበትና  እንዲተች  የሚጠይቅ ምክረሃሳብ ለፍትህ ሚኒስቴር ቀረበ ። ”ስብስብ ለሰብዓዊ  መብቶች በኢትዮጵያ“  የተሰኘ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት፣ ከሌሎች በሰብዓዊ መብቶች ላይ ከሚሠሩ አገር በቀል የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ጋር በመተባበር፣ ለረቂቅ የሽግግር ፍትህ ፖሊሲው  ግብዓት የሚኾኑ ሀሳቦችን የያዘ የምክር ሀሳብ ሰነድ ለፍትህ ሚኒስቴር በጽሁፍ አቅርቧል።
ይኸው ለፍትህ ሚኒስቴር የቀረበው የምክር ሃሳብ ሰነዱ፣ በቅርቡ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርቦ ይጸድቃል ተብሎ የሚጠበቀው  ረቂቅ የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ፣ ለሕዝብ ቀርቦ እንዲተችና ሕዝቡ በጉዳዩ ላይ ሃሣብ እንዲሰጥበት የሚጠይቅ ሲሆን፤  ከሽግግር ፍትህ ፖሊሲው ትግበራ  አስቀድሞ    መንግሥት  በተለያዩ የአገሪቱ  አካባቢዎች በመካሄድ ላይ የሚገኙ  ግጭቶችን  ማስቆም እንዳለበት  እንዲሁም  በፖሊሲው ሂደት አግባብነት ያላቸው ተቋማት ሚና  መካተት እንዳለበት ይጠቁማል፡፡
 በተጨማሪም ሰነዱ የፖሊሲው የተፈጻሚነት ውሰን፣ በሰሜኑ ጦርነት ከባድ ወንጀሎችን የፈጸሙ የኤርትራ ወታደሮችን በልዩ ፍርድ ቤት ማየትን ጭምር እንዲያካትት የሚጠይቁና ሌሎች ምክረ ሃሳቦችንም ይዟል፡፡ ድርጅቱ፤ ከሌሎች በሰብዓዊ መብቶች ላይ ከሚሰሩ ተቋማት ጋር በመተባበር ለፍትህ ሚኒስቴር ባቀረበው ምክረ ሃሣብ፣ ረቂቁ የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ፣ በምክር ቤቱ ከመፅደቁ በፊት ለህዝብ ውይይት ሊቀርብ እንደሚገባው  ጠቁሟል፡፡



Read 757 times