Saturday, 31 May 2014 14:19

የሪያል ማድሪድ ‘La Decima’

Written by  ግሩም ሠይፉ
Rate this item
(1 Vote)

ሪያል ማድሪድ ባለፈው ሳምንት የተጎናፀፈውን 10ኛው የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫ  እስኪያገኝ ባለፉት 12 የውድድር ዘመናት የነበረው የውጭ እና ሌሎች ሁኔታዎች እንዲህ ናቸው፡፡
ባለፉት 11 የውድድር ዘመናት ክለቡ ከግማሽ ፍፃሜ ማለፍ ተስኖት ነበር፡፡
በዚሁ ጊዜ ከክለቡ የለቀቁ 12 ተጨዋቾች በተለያዩ ክለቦች የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫን አንስተዋል፡፡
በአጠቃላይ በ12 ዓመታት እስከ 19.5 ቢሊዮን ብር ወጭ ሆኗል፡፡
ባለፉት 10 ዓመታት በተጨዋቾች የዝውውር ገበያ 3 ጊዜ አዳዲስ ክብረወሰኖችን የሰበረው ክለቡ ከ2002 እኤአ ጀምሮ ዘንድሮ እስከተገኘው አስረኛው የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫ ድረስ ሪያል ማድሪድ 62 ተጨዋቾች አስፈርሟል፤ 20 ዎቹ ከእንግሊዝ ፕሪሚዬር ሊግ ናቸው፡፡ በዝውውር ገበያው ወጭ የሆነባቸው ደግሞ 32.74 ቢሊዮን ብር ነው፡፡
በየዓመቱ ለደሞዝ ክፍያ ብቻ የሚያወጣው 2.74 ቢሊዮን ብር የሚደርስ ሲሆን ባለፉት 12 ዓመታት የከፈለው 32.88 ቢሊዮን ብር ነው፡፡
የቡድኑ ዋጋ ግምት 60.45 ቢሊዮን ብር
ተንቀሳቃሽ ትርፉ 3.32 ቢሊዮን ብር
ውዝፍ እዳው 4.49 ቢሊዮን ብር

Read 1243 times