“የዮድ አቢሲኒያዋ እመቤት” የሚል ቅፅል ስም በተሰጣት የባህል ዘፋኝ እመቤት ነጋሲ የተዘጋጀው “ሰንደዓ በል” የተሰኘ የሙዚቃ አልበም ባለፈው እሁድ በዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ ተመርቋል። አልበሙን ለማዘጋጀት ከ250ሺህ ብር በላይ እንደወጣበትም ተገልጿል፡፡
ድምፃዊ ፀጋዬ እሸቱን ጨምሮ በርካታ አርቲስቶች በተገኙበት የተመረቀው አልበሙ፤ በዕለቱ ለታዳሚዎች በሽያጭ ቀርቧል፡፡
ድምፃዊቷ በዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ ቤት አዳራሽ ለስምንት አመታት የሰራች ሲሆን ዮድ አቢሲኒያን በመወከል በውጭ አገራት አምስት ስራዎቿንና ባህሏን አስተዋውቃ መመለሷም ተገልጿል። “ሰንደዓ በል” የተሰኘው የአልበሙ መጠሪያ የሙዚቃ ቪዲዮ የተሰራለት ሲሆን ወደፊት ለሁሉም ዘፈኖች ክሊፕ እንደምትሰራ ድምፃዊቷ በምረቃው ላይ ገልፃለች፡፡ ድምፃዊቷ የፈረመችበት አንድ ሲዲም ለጨረታ ቀርቦ አንድ የምሽቱ ታዳሚ በ6500 ብር አሸንፎ እንደወሰደው ታውቋል፡፡
Saturday, 14 June 2014 12:27
“ሰንደዓ በል” የሙዚቃ አልበም ተመረቀ
Written by ናፍቆት ዮሴፍ
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና