Saturday, 15 November 2014 11:49

“ቁምታም ጾም” በገበያ ላይ ዋለ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በወጣቱ ገጣሚ አያሌው እውነቴ የተጻፈውና በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ የሚያጠነጥኑ ከ65 በላይ ግጥሞችን የያዘው “ቁምታም ጾም”  የተሰኘ የግጥም ስብስብ መጽሃፍ፣ ከትናንት ጀምሮ በገበያ ላይ መዋሉን ገጣሚው ለአዲስ አድማስ ገለጸ፡፡
92 ገጾች ያሉት “ቁምታም ጾም” የግጥም ስብስብ መጽሃፍ፣ በአዲስ አበባና በክልል ከተሞች በሚገኙ የመጽሃፍት መደብሮችና በአዟሪዎች በ42.50 ብር እየተሸጠ ሲሆን፣ ለውጭ አገራት የመሸጫ ዋጋው 9 የአሜሪካ ዶላር ነው፡፡
መጽሃፉ በቅርቡ በአዲስ አበባ፣ በባህር ዳር እና በደብረ ማርቆስ በሚካሄዱ የስነ-ጥበብ ዝግጅቶች በይፋ እንደሚመረቅ የገለጸው ገጣሚው፣ በቀጣይም ለህትመት የተዘጋጁ ሌሎች የግጥምና የወግ ስብስብ ስራዎችን ለአንባብያን እንደሚያበቃ ገልጧል፡፡
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የስነ-ጽሁፍ ተማሪ በነበረበት ወቅት፣ በዩኒቨርሲቲው ባህል ማዕከል የተለያዩ የስነ-ጽሁፍ ስራዎችን በማቅረብ የሚታወቀው ገጣሚው፣ ከ17 አመታት በፊትም ለህትመት የመጀመሪያ ስራው የሆነውን “የበረከቱ አስኳል” የተሰኘ የአጫጭር ልቦለዶች ስብስብ መጽሃፍ ለንባብ አብቅቷል፡፡

Read 1266 times