በደራሲ ደሞዝ ጐሽሜ ተፅፎ ለንባብ የበቃው “ሶስተኛው ኪዳን” ልብወለድ መፅሀፍ ትናንት ምሽት በብሔራዊ ቤተ መፃሕፍትና ቤተ መዛግብት ኤጀንሲ አዳራሽ ተመረቀ፡፡
ለመጀመሪያ ጊዜ በሐምሌ 2003 ዓ.ም የታተመው መጽሐፉ፤ ሁለተኛው እትም ባለፈው መስከረም የወጣ ሲሆን ጭብጡ በኢትዮጵያ መንፈሳዊ ስልጣኔ ላይ የሚያጠነጥን ነው ተብሏል፡፡
በምረቃ ሥነስርዓቱ ላይ የመጽሐፍ ዳሰሳና ውይይትም ተካሂዷል፡፡ የምርቃት ሥነስርዓቱን ያዘጋጀው ኢጋ ሚዲያ እና ኮሙኒኬሽን እንደሆነ ታውቋል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና