Saturday, 21 February 2015 13:45

የጋዜጠኛ ሰለሞን ታደሰ “በተውኩት” የትረካ ሲዲ ለገበያ ሊውል ነው

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(1 Vote)

“ቦሌ ፒኮክ ጋ ጠብቂኝ” እንዲሁም “የሸገር ወጎች 1 እና 2” በሚል መፃሕፍቶቹ የሚታወቀው ጋዜጠኛ ሰለሞን ታደሰ አዲስ የትረካ ሲዲ ሊያወጣ ነው፡፡
“የትረካ ሲዲው ገቢ ሙሉ ለሙሉ ወላጆቻቸውን ላጡ ህፃናት ይውላል” ያለው ጋዜጠኛው፤ “ቦሌ ፒኮክ ጋ ጠብቂኝ” ከሚለው መፅሀፍ ላይ የተመረጡ አዝናኝ ታሪኮችና አዳዲስ ታሪኮች በማጀቢያ ሙዚቃ ተቀናብረው ተካተውበታል ብሏል፡፡
የቀረፃና ሌሎች ወጪዎች ከእስራኤል ሀገር በመጡ ሁለት በጎ አድራጊዎች መሸፈኑን የገለፀው አዘጋጁ፤ የትረካ ሲዲው በበጎ አድራጊዎቹ በኩል እንደሚከፋፈል ጠቁሞ በትረካው ላይ ስድስት  ታዋቂ ጋዜጠኞችና አርቲስቶች ሃሳቡን በመደገፍ በነፃ እንደተሳተፉበት ተናግሯል፡፡

Read 1678 times