Monday, 02 March 2015 08:43

ህዝቡ በእውቀት ላይ ተመስርቶ እንዲመርጥ ኢዴፓ ጠየቀ

Written by  አለማየሁ አንበሴ
Rate this item
(0 votes)

በግንቦቱ ምርጫ ህዝቡ በእውቀት ላይ ተመስርቶ እንዲመርጥ ያሳሰበው ኢዴፓ፣ ህብረተሰቡ የፓርቲውን አማራጭ አስተሳሰቦች ገምግሞ እንዲመርጥ የሚያስችል የመወዳደሪያ ማኒፌስቶ ማውጣቱንም አስታውቋል፡፡
ፓርቲው ለአዲስ አድማስ በላከው መግለጫ፤ ቢመረጥ ሊተገብራቸው የሚፈልጋቸውን ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ አማራጮችን ከገዥው ፓርቲ በተለየ በግልፅ ማስቀመጡንና ለወጣቱ ትውልድም ልዩ ትኩረት እንደሚሰጥ ጠቁሟል፡፡
“የስልጣን መገኛው መንገድ ምርጫና ምርጫ ብቻ ነው” ያለው ፓርቲው፤ የግንቦቱ ምርጫ  የተሳካና ፍፁም ሰላማዊ እንዲሆን የበኩሉን ግዴታ ለመወጣት ዝግጁ መሆኑን ገልፆ ገዥው ፓርቲም ሆነ ምርጫ ቦርድ ባላቸው ኃላፊነት ከአድሎአዊነትና ከወከባ የፀዳ የፖለቲካ ምህዳር እንዲያመቻቹ፣ ለመድብለ ፓርቲ የፖለቲካ ስርአት መጠናከርም ቁርጠኝነታቸውን በተግባር እንዲያረጋግጡ ጠይቋል፡፡
መራጩ ህዝብም በጭፍን ከመደገፍና  ከመቃወም ይልቅ በእውቀት ላይ ተመስርቶ አማራጭ ሃሳቦችን በመገምገም ያሻውን ፓርቲ በሰለጠነ መንገድ እንዲመርጥ ኢዴፓ ጥሪውን አስተላልፏል፡፡

Read 1036 times