Monday, 06 April 2015 08:49

“ሰሙነ ህመማት የስነ - ፅሁፍና የበገና ምሽት” ይካሄዳል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

በኢጋ ሚዲያና ኮሙዩኒኬሽን አዘጋጅነት የሚቀርበው “ሰሙነ ህማማት የስነ ጽሑፍና የበገና ምሽት” የፊታችን ሰኞ ከቀኑ 11፡30 ሰዓት ጀምሮ በዋቢ ሸበሌ ሆቴል እንደሚካሄድ አዘጋጆቹ አስታወቁ፡፡
በዝግጅቱ ላይ አንጋፋና ወጣት ፀሐፍት፤ ግጥሞችንና ወጐችን በባህላዊ የሙዚቃ መሳሪያዎች እየታጀቡ ያቀርባሉ ተብሏል፡፡
በምሽቱ ከ20 በላይ የበገና ደርዳሪዎች በአንድ ላይ ተጣምረው በገና በመደርደር ዝግጅቱን እንደሚያደምቁም ተገልጿል፡፡ የዝግጅቱ አላማ ባህላዊ የሙዚቃ መሳሪያና ስነ - ጽሑፍ ያላቸውን ተዛምዶ ለማህበረሰቡ ማስገንዘብና ትኩረት እንዲሰጣቸው ማድረግ ነው ብለዋል - አዘጋጆቹ፡፡  

Read 3026 times