Monday, 11 May 2015 08:51

የየአገሩ ምሳሌያዊ አባባል

Written by 
Rate this item
(21 votes)

ድር ቢያብር አንበሳ ያስር፡፡
የኢትዮጵያውያን አባባል
ብዙ እጆች ሥራን ያቀላሉ፡፡
የታንዛንያውያን አባባል
ሁለት ጉንዳኖች አንድ አንበጣን ለመጐተት አያንሱም
የታንዛንያውያን አባባል
አንድ አምባር ለብቻው አይንሿሿም፡፡
የኮንጐአውያን አባባል
አንድ እንጨት ይጨሳል እንጂ አይነድም፡፡
የአፍሪካውያን አባባል
በፍጥነት ለመጓዝ ከፈለግህ ብቻህን ሂድ፤ ሩቅ ለመጓዝ ከፈለግህ በህብረት ሂድ፡፡
የአፍሪካውያን አባባል
ቤተሰብ እንደዛፍ ነው፤ ይጐብጣል እንጂ አይሰበርም
የዩቴ አባባል
የቅርብ ወዳጅ የቅርብ ጠላት ይሆናል፡፡
የአፍሪካውያን አባባል
ጓደኛ ማጣት ከመደህየት እኩል ነው፡፡
የታንዛንያውያን አባባል
ለከብቶችም እንኳን ወጣትነት ውበት ነው።
የግብፃውያን አባባል
ቁንጅና ተሸጦ አይበላም፡፡
የናይጄሪያውያን አባባል
ቡናና ፍቅር የሚጣፍጠው በትኩሱ ነው፡፡
የኢትዮጵያውያን አባባል
ፍቅር ባለበት ጨለማ የለም፡፡
የቡሩንዲያውያን አባባል
ከአንተ የሚበልጥ እግር ያላት ሴት አታግባ።
የሞዛምቢካውያን አባባል
ትዕግስት ሁሉንም ችግሮች የሚፈታ ቁልፍ ነው፡፡
የሱዳናውያን አባባል
ስለሮጡ ብቻ ይደረሳል ማለት አይደለም፡፡
የስዋሂሊ አባባል
ትዕግስት ድንጋይ ያበስላል፡፡
የአፍሪካውያን አባባል

Read 6740 times