Saturday, 11 July 2015 11:54

አልፋ የዳይሬክተሮች ቦርድ የቀረበ ቅሬታ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በጋዜጣችሁ የሰኔ 13 ቀን 2007 ዓ.ም ዕትም ላይ አልፋ የትምህርትና ስልጠና አ.ማህበርን በተመለከተ ባቀረባችሁት ዜና፤ “ቅሬታው” በአንድ ግለሰብ የቀረበ መሆኑ እየታወቀ “የአልፋ ባለ አክስዮኖችና አመራሮች እየተወዛገቡ ነው” የሚል ርዕስ መስጠታችሁ አሳሳች፣ ለጋዜጣው አንባቢያን ስለ አክስዮን ማህበሩ የተዛባ መግለጫ የሚሰጥና የአክስዮን ማህበሩን መልካም ስምና ዝና የሚያጐድፍ አቀራረብ በመሆኑ በብዙኃን ባለአክስዮኖች ዘንድ ጥያቄ አስነስቷል፡፡
በተጨማሪም በዘገባችሁ፣ በማንኛውም የበጀት ዓመት በአክስዮን ማህበሩ ተገኝቶ የማያውቀውን ብር 30.000.000 (ሰላሳ ሚሊዮን ብር) የተጣራ ትርፍ ማስረጃ ባላገናዘበ ሁኔታ ተገኝቶ ነበር ብላችሁ መግለፃችሁ እንዲሁም በ2006 በጀት ዓመት የተገኘው የተጣራ ትርፍ ብር 4.5 ሚሊዮን እንደሆነ ተገልፆ እያለ፣ በመጨረሻው በጀት ዓመት ብር 1.5 ሚሊዮን ብቻ እንደተገኘ አድርጋችሁ ማቅረባችሁና ቅሬታ አቅራቢው የገለፀውን አመራሩ ከሰጠው መልስ ጋር በማነፃፀር አለመዘገባችሁ ቅሬታ እንደፈጠረብን ልንገልፅ እንወዳለን፡፡
(ቢኒያም ሀይሉ የዳይሬክተሮች ቦርድ ፀሐፊ)

Read 1478 times