Monday, 23 October 2023 10:15

ዓለም አቀፍ የስታርትአፕ ሽልማት በአዲስ አበባ ይካሄዳል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ዓለም አቀፍ የስታርትአፕ ሽልማት በአዲስ አበባ ይካሄዳል

ዓለም አቀፍ የስታርትአፕ ሽልማት ጉባዔ በአዲስ አበባ በሳይንስ ሙዚየም ከጥቅምት 14-16/2016 ይካሄዳል።
በጉባዔው ከ300 በላይ አህጉርና አለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ባለቤቶች ይወዳደራሉ።
ጉባዔውን አስመልክተው የስራና ክህሎት ሚኒስትር ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚል ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል።
ሚኒስትሯ በመግለጫቸው ጉባዔው ከጥቅምት 14-16/ 2016 በሳይንስ ሙዚየም ይካሄዳል ብለዋል።
ከእነዚህ ውስጥ የተሻለ ስራ ይዘው ለቀረቡ 15 ተወዳዳሪዎች ሽልማት እንደሚበረከትም ተናግረዋል።
ጉባዔው የልምድ ልውውጥ የሚደረግበትና አለም አቀፍ ትስስር የሚፈጠርበት እንደሚሆንም አንስተዋል።
የኢትዮጵያን ትክክለኛ ገጽታ ለሌላው አለም በማስተዋወቅ ወደ አህጉርና አለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ገበያ ለመግባት ይረዳልም ብለዋል።
ሚኒስትሯ አክለውም "ኔክስት ኢትዮጵያን ስታርትአፕ ኢኒሼቲቭ" ጥቅምት 13 ቀን 2016 ዓ.ም በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ ተናግረዋል።
ይህም ለቴክኖሎጂ ልማት ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር ጠቀሜታው የጎላ መሆኑን አመላክተዋል።
መድረኩ በስራና ክህሎት ሚኒስቴር እና በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ትብብር እንደሚዘጋጅ መገለጹን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

Read 1738 times