Sunday, 12 November 2023 20:30

በአልባኒያ ሊግ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ የነበረው ጋናዊው አጥቂ በጨዋታ መሐል ሕይወቱ አለፈ

Written by 
Rate this item
(2 votes)
በአልባኒያ ሊግ ዘጠኝ ግቦችን በማስቆጠር ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ የነበረው ጋናዊው አጥቂ ራፋኤል ድዋሜና በጨዋታ መሐል ሕይወቱ ማለፉ ብዙዎችን አሳዝኗል፡፡
ተጫዋቹ የተሰለፈበት ኢግናቲያ ክለብ ከፓርቲዛኒ ጋር እየተጫወተ ባለበት ወቀት በ23ኛው ደቂቃ አካባቢ ተዝለፍልፎ የወደቀ ሲሆን፤ አፋጣኝ የሕክምና ክትትል ቢደረግለትም በአሳዛኝ ሁኔታ ህይወቱ ሊያልፍ ችሏል፡፡
ዳዋሜና ራሱን ስቶ ከወደቀ በኋላ በህክምና ባለሙያዎች እርዳታ ከሜዳ እንዲወጣ ከተደረጓ በኋላ ሕይወቱ ማለፉን ነው የአልባኒያ እግርኳስ ፌዴሬሽን የገለጸው፡፡
የ28 ዓመቱ ራፋኤል ድዋሜና በስፔን፣ ስዊዘርላንድ፣ ኦስትሪያ እና ዴንማርክ ባሉ ክለቦች በመጫወት የተሳካ ጊዜ አሳልፏል።
በዚህ የውድድር ዘመን በአልባኒያ ሊግ ዘጠኝ ግቦችን በማስቆጠር ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ነበር ሲሆን፤ በፕሮፌሽናል የእግር ኳስ ህይወቱም ዘጠኝ ጊዜ ለሀገሩ ጋና ተጫውቷል።
ተጫዋቹ ከልብ ሕመም ጋር በተያያዘ በ2021 ከእግር ኳስ ራሱን እንዲያገል ከህክምና ባለሙያዎች ምክር ቀርቦላት እንደነበር ዶቼ ቬለ ዘግቧል፡፡
Read 720 times