Saturday, 18 November 2023 00:00

ኢትዮጵያ ወደከፋ የእርስበርስ ጦርነት እንዳትገባ አሜሪካ ትታደጋት ዘንድ ተጠየቀ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ኢትዮጵያ ወደከፋና የለየለት የእርስበርስ ጦርነት እንዳትገባ፣ በአገሪቱ ሰላም ለማስፈን የሚቻልበትን መንገድ በማፈላለግ፣ ከከፋ አደጋ ትታደጋት ዘንድ ለአሜሪካ ጥሪ ቀረበ። ጥሪውን ለአሜሪካው ፕሬዚዳንት ያቀረቡት በአሜሪካ የሚገኙ የኢትዮ-አሜሪካን ሲቪል ማህበራት
ናቸው።
ማህበራቱ በአሁኑ ወቅት ደብዳቤውን ለፕሬዚዳንት ባይደን ለመፃፍ የተነሳሱበትን ምክንያት ሲያስረዱም፤ በአገሪቱ በአሁኑ ወቅት እየተካሄደ ያለው የእርስበርስ ጦርነት በአለማቀፍ ማህበረሰብ፣ በአሜሪካ መንግስትም ሆነ በሌሎች ተፅዕኖ ማሳደር በሚችሉ አካላት ሁሉ ታውቆ በዲፕሎማቲክ መንገድ ጦርነቱን ለማስቆም እንዲችሉ ለማድረግ ታልሞ እንደሆነም ጠቁመዋል፡፡
በፊደራል መንግስቱና በአማራ ከልል ውስጥ በሚንቀሳቀሱ የፋኖ ታጣቂዎች መካከል ያለው ውጥረት ተባብሶ የትጥቅ ትግል ማስከተሉን ያወሳው የማህበራቱ ደብዳቤ፤ ይህ ችግር አፋጣኝ መፍትሄ ካላገኘ ወደ የእርስበርስ ጦርነት በማደግ ኢትዮጵያን ወደ ማተራመስና ለአፍሪካ ቀንድ ትልቅ ስጋት መጋረጡ አይቀሬ ኢትዮጵያ ወደከፋ የእርስበርስ ጦርነት እንዳትገባ አሜሪካ ትታደጋት ዘንድ ተጠየቀ መሆኑን አመልክቷል፡፡ አሜሪካ ይህንን ጦርነት የማስቆምና ሰብአዊ መብቶችን የመጠበቅ የሞራል ግዴታ እንዳለባትም ተጠቁሟል፡፡  

አሁን በአገሪቱ በስራ ላይ ያለው ብሄር ተኮር ፊደራሊዝም ሀገሪቱን በፍጥነት ከቁጥጥር ውጪ ወደሚሆን ሁከት እየከተታት እንደሆነም ማህበራቱ በደብዳቤያቸው መጠየቃቸውን የዘገበው ዶቼቪሌ የዜና አውታር አሜሪካ ተቀባይነት ያለው መንግስታዊ ሽግግር በማመቻቸት ለኢትዮጵያ አዲስ ህገ መንግስት የሚዘጋጅበት ሂደት እንድትደግፍ ጥሪ ማቅረባቸውን ገልጿል፡፡

Read 1136 times