Saturday, 02 December 2023 19:36

የአሜሪካ ኤምባሲ አዲስ አበባን ፊንፊኔ ሲል መጥራቱ ተቃውሞን አስነሳ

Written by  መታሠቢያ ካሣዬ
Rate this item
(1 Vote)

መቀመጫውን በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ያደረገው በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኤምባሲ በይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገፁ ርዕሰ መዲናይቱን አዲስ አበባን ፊንፊኔ ሲል መጥራቱን ሃያሁለት  የሲቪክ ማህበራት ድርጅቶች ተቃወሙት። ማህበራቱ ተቃውሞአቸውን በመግለፅ ለአሜሪካው የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ቢሊንከን ደብዳቤ ልከዋል።
ኤምባሲው የሚሰጣቸውን የቪዛና ሌሎች አገልግሎቶችን አስመልክቶ ከትናት በስቲያ በማህራዊ ትስስር ገፁ ላይ በአፋን ኦሮሞ ባወጣው ማስታወቂያ ላይ አዲስ አበባ በሚለው የርዕሰ መዲናይቱን መጠሪያ ምትክ “ፊንፊኔ” የሚለውን ስም ተጠቅሟል።  ይህን የኤምባሲውን አጠራር ተከትሎ ተቀውሞአቸውን ያሰሙት በአብዛኛው ነዋሪነታቸውን በውጪ አገር ያደረጉ ኢትዮጵያውያን ሲቪክ ድርጅቶች ለአሜሪካው የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ደብዳቤ ልከዋል።
 ማበራቱ በዚሁ የተቃውሞ ደብዳቤአቸው “በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ የሚገኘው የአሜሪከ ኤምባሲ አጨቃጫቂ በሆነውና በአክራሪ የኦሮሞ ቡድኖች የሚቀነቀነውን “ፊንፊኔ” የሚለውን ስም በመጠቀሙ ቁጣችንን እንገልጻለን ብለዋል። በሌላ በኩል ይህን የኤምባሲውን አጠራር የደገፉ የኦሮሞ ማህረሰብ ድርጅቶች ኤምባሲው ርዕሰ መዲናዋን የጠራበት ፊንፊኔ የተሰኘውን መጠሪያ የሚደግፉ መሆኑን አመልክተዋል።

Read 1971 times