Thursday, 28 December 2023 20:16

ህገወጥ የቁም እንስሳት ንግድ ከፍተኛ ኪሳራ ማስከተሉ ተገለጸ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

2ኛው ሀገር አቀፍ የህገወጥ ንግድ መከላከል ጉባኤ በዛሬው ዕለት የተካሄደ ሲሆን፤ በመድረኩ ላይ ህገወጥ የቁም እንስሳ ንግድ ከፍተኛ ኪሳራ ማስከተሉ ተጠቁሟል፡፡

በጉባኤው ላይ በቁም እንስሳት፤ በመድኃኒትና ሌሎች የንግድ ዘርፎች ላይ በሚታይ ህገወጥ ንግድ ላይ ጥናታዊ ጽሁፎች ቀርበው ውይይት ተደርጓል፡፡

በንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር የንግድ ስርዓትና ፈቃድ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ፍሰሀ ይታገሱ  እንደተናገሩት፤ ህገወጥ ንግድን ለመከላከል በዘመናዊ መልኩ የንግድ ስርዓቱን ማስኬድና ከጎረቤት ሀገራት ጋር በትብብር መስራት አስፈላጊ ነው ብለዋል።

በሀገር ደረጃ ጤናማ የንግድ ስርዓት እንዲኖር፤ የግሉን ዘርፍ መብት በጠበቀ መልኩ መንግስትም ተገቢውን ግብር እንዲያገኝ የሚያስችሉ መመሪያዎች እየተዘጋጁ እንደሚገኙ ሚኒስትር ዴኤታው ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ የንግድ ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ኢንጂነር መላኩ እዘዘው በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ በቁም እንስሳት በአፍሪካ አንደኛ ብትሆንም፣ ወደ ጎረቤት ሀገራት በሚደረግ  ህገወጥ ንግድ  ምክንያት ተጠቃሚ መሆን አልቻለችም ብለዋል፡፡

 “በመድሃኒት ንግድ አንድ ቢሊዮን ዶላር ግብይት የሚካሄድ ቢሆንም፣ በዘርፉ ባለው ህገወጥነትና ብልሹ አሰራር ምክንያት የሚፈለገው ገቢ አልተገኘም” ብለዋል፤ ፕሬዚዳንቱ፡፡

Read 1389 times