Saturday, 27 January 2024 00:00

አቶ ተመስገን ጥሩነህ የብልፅግና ም/ፕሬዚዳንት ሆነው ተመረጡ ፓርቲው አቶ ደመቀ መኮንን በክብር ሸኝቷል

Written by 
Rate this item
(4 votes)

ብልፅግና ፓርቲ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር የሆኑትን አቶ ተመስገን ጥሩነህን የፓርቲው ም/ፕሬዚዳንት አድርጎ የሾመ ሲሆን፤ ፓርቲውን በም/ፕሬዚዳንትነት ሲያገለግሉ የቆዩትን ም/ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን በክብር አሰናብቷል።አቶ ተመስገን ጥሩነህ ከዚህ ቀደም የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት ሆነው ለጥቂት ጊዜ ካገለገሉ በኋላ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተርና የብልፅግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ሆነው እያገለገሉ ይገኛሉ።ብልፅግና ትላንት ጥር 17 ቀን 2016 ዓ.ም ቀትር ላይ ይፋ እንዳደረገው፤ ፓርቲው የአሰራር ስርዓትንና የአመራር መተካካትን መርህ በመከተል የፓርቲው ም/ፕሬዚዳንት ሆነው ሲያገለግሉ የነበሩትን አቶ ደመቀ መኮንን በክብር አሰናብቶ አቶ ተመስገን ጥሩነህን በአብላጫ ድምፅ መርጧል።

Read 1035 times