Saturday, 10 February 2024 09:49

የሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ የግብረሰዶማዊነት መብትን የሚፈቅድ ስምምነት መፈፀሙን ተቃወመ

Written by 
Rate this item
(3 votes)

የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ፣ መንግስት ከኢትዮጵያ ህዝብ የሃይማኖትና የባህል እሴቶች ጋር የሚፃረር ፅንሰ ሃሳቦችና ትርጓሜዎች ያላቸውን ይዘቶች ያካተተውን መንግስት ስምምነት መፈረሙን በጥብቅ

እንደሚቃወም አስታወቀ፡፡ በአውሮፓ ህብረትና በአፍሪካ፣ በካረቢያንና በፓስፊክ አገራት ለቀጣዮቹ 20 ዓመታት እንዲዘልቅ ታሳቢ ተደርጎ የተከናወነው የንግድና ኢኮኖሚ ትብብር በሚል ሽፋን የቀረበውና ሰሞኑን

የተፈረመው ስምምነት፣ ከግብረ ሰዶማዊነት መብቶች፣ ከፆታ መቀየር፣ ከውርጃና ሁሉን አቀፍ ግልሙትናዎችን ህጋዊ ማድረግ ይገኝበታል ተብሏል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም እጅግ አደገኛ ይዘት ያለው ለአህጉሪቱ ልጆችና

ታዳጊዎች ሁሉን አቀፍ የወሲብ ትምህርት አስገዳጅ ትምህርት ሆኖ እንዲሰጥ የሚያደርግ እንደሆነም ተገልጿል፡፡በኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ የበላይ ጠባቂ አባቶች ሰሞኑን የተሰጠው ይኸው መግለጫ፣

መንግሰት ከሰሞኑ የፈፀመውን ይህንኑ ስምምነት በጥብቅ እንደሚቃወሙትና እንደማይቀበሉት በመጥቀስ፣ ጉዳዩን መንግስት በአንክሮ እንዲመለከተው ጠይቀዋል፡፡


Read 1217 times