በቅድስት ይልማ ተዘጋጅቶ በማህደር አሰፋ ፕሮዲዩስ የተደረገው ዶቃ ልብ አንጠልጣይ ፊልም "Los Angeles”ከተማ ውስጥ በተዘጋጀው በፓን አፍሪካን ፊልም ፌስቲቫል ላይ ተሳትፎ በ" Audience Choice Awards” አሸናፊ መሆን ችሏል::
በአፍሪካዊያን የጥበብ ስራዎች ላይ ትኩረትን ያደረገው ፓን አፍሪካ ፊልም ፌስቲቫል ከ32 ዓመታት በፊት የተመሰረተ ነው።
ቅድስት ይልማ ከአሁን ቀደም "ረቡኒ" ፣ "ታዛ" ፊልሞችንና "እረኛዬ" ድራማን ጨምሮ ከአስር በላይ ስራዎችን ለተደራሲያን ማቅረቧ ይታወሳል::
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና