Friday, 15 March 2024 00:00

ዲ ኤም ሲ ሪል እስቴት ለነባር ደንበኞቹ ልዩ ቅናሽ ማድረጉን አስታወቀ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

ቶሎ ማስረከብና ልዩ ዲዛይን ዋና መገለጫዎቼ ናቸው ብሏል

ባለፉት 27 ዓመታት በመንገድ ግንባታ ሥራ ልምድ እንዳካበተ የገለጸው ዲ ኤም ሲ ሪል ስቴት ወደ መኖሪያ ቤት ማልማት መግባቱንና ለነባር ደንበኞቹ ልዩ ቅናሽ ማቅረቡን አስታወቀ። ድርጅቱ ይህንን ያስታወቀው ከትላንት በስቲያ ለቡ መብራት ሃይል በሚገኘው የግንባታ ሳይት ለመገናኛ ብዙሃን ባደረገው የጉብኝትና የመግለጫ መርሃ ግብር ነው። ዲ ኤም ሲ ሪል እስቴት በዳንኤል ማሞ ኮንስትራክሽን (ዲ ኤም ሲ) ስር ካሉ አምስት ኩባንያዎች አንዱ ሲሆን በተለይም በሀዋሳ በአርባ ምንጭና በሌሎች አካባቢዎች ላለፉት 27 ዓመታት ያካበተውን የመንገድ ግንባታ ልምድ ወደ ሪል እስቴት ልማት በማምጣት ለቤት ፈላጊዎች ሲኖሩበት የሚደሰቱበት ቤት ለማስረከብ አዳዲስ ቴክሎጂዎችንና 24 ሰዓት የሚሰሩ ሰራተኖችን ይዞ ወደ ስራ መግባቱን የኩባንያው ሃፊዎች አብራተዋል።
ዲኤምሲ ወደ ሪል እስቴት ልማት ከመግባቱ በፊት በዘርፉ ያሉ ተግዳሮቶችን ለመለየት አንድ ዓመት ተኩል የፈጀ ጥናት ማካሄዱ የተገለጸ ሲሆን በጥናቱም ከተለዩት ዋና ዋና ችግሮች ቤቶቹን ለነዋሪዎቹ በወቅቱ የማስረከብና የዲዛይን ችግር ቀዳሚዎቹ ናቸው ሲሉ ከኩባንያው ሃፊዎች አንዱ አቶ ፋንታሁን ግርማ ገልጸው ዲኤምሲ ይህን ለመቅረፍ አንድ ስላፕ በ10 ቀን የሚሞላ ቴክኖሎጂ ከጣውላና ከእንጨት የጸዳ አሉሙኒየም ፍሬም ወርክ ቴክሎጂን በመጠቀም እስከ ሁለት ዓመት ከስድስት ወር ባለ ጊዜ ውስጥ ለማስረከብ 24 ሰዓት እየሰራ መሆኑን አብራርተዋል። በለቡ መብራት ሃይል በ65ሺ 395 ካ.ሜ ዋናው መንገድ ላይ በሚገነባው ትልቅ የመኖሪያ መንደር ለነባር ደንበኞቹ እስከ 1 ነጥ አራት ሚሊዮን ብር ቅናሽ ማድረጉን የገለጸ ሲሆን በአንድ ህንፃ ላይ እስከ 200 አባዎራ እንደሚኖርና በየህንፃው ለ200 አባወራ አንድ ቤት በእጣ ለእድለኛ እንደሚሰጥም ተነግሯል።
ከስቱዲዮ እስከ ባለ 4 መኝታ ቤት ለገበያ ያቀረበው ኩባንያው ቤቶቹ ከ6 ሚሊዮን እስከ 20 ሚሊዮን የሚደርስ ዋጋ እንዳላቸው የተገለፀ ሲሆን ባለ 186 ካ.ሜ ባለ አራት መኝታ ቤት  ወዲያው ከፍሎ ለሚገዛ 6 ሚሊዮን ማለትም የ1 ስቱዲዮ መግዛ ያህል ቅናሽ ይደረጋል ብለዋል የዲ ኤም ሲ ሃላፊዎች።
ቤቶቹን በጊዜ ማስረከብ ስለመቻላቸው ለቤት ፈላጊዎች ዋስትናቸው ምንድን ነው በሚል ከጋዜጠኞች ለተነሳው ጥያቄ ሃላፊዎቹ ሲመልሱ ቤቶቹን በ2 ዓመት ከስድስት ወር ለማስረከብ ውል መገባቱን ነገር ግን ከአቅም በላይ የሆነና አስገዳጅ ጉዳይ ካጋጠመ  ከ3-6 ወር የጊዜ ገደብ ጭማሪ ኩባንያው እንደሚጠይቅ ሆኖም በዚህ ጊዜ ማስረከብ ካልቻለ የቤቱን ዋጋ 20 በመቶ ኩባንያው እንደሚቀጣ በውሉ ላይ መቀመጡን ሃላፊዎቹ አብራተዋል።
 ለደንበኞች ተዓማኒ ለመሆንም ሆነ በወቅቱ ባለማስረከብ ከሚመጣው ቅጣት ኩባንያው ራሱን ለመጠበቅ ለሰራተኞች በግንባታው ሳይት ላይ መኖሪያ፣ ምግብና ሌሎች አስፈላጊ ቁሳቁሶችን አሟልቶ 24 ሰዓት ግንባታው መቀጠሉም ተብራቷል። ዲ ኤም ሲ ሪል ስቴት በአሁኑ ወቅት ቤቶቹን በካሬ 90 ሺህ ብር ለሽያጭ ያቀረበ ሲሆን በቀጣይ በፒያሳ፣ በቦሌና በሌሎች ተመራጭ ቦታዎች ቤቶቹን ለማልት መዘጋጀቱን ገልጿል።
ዲኤም ሲ ሪል ስቴት የሚገነባቸው ቤቶች በልዩ ዲዛይን የተገነቡና ለኗሪው አስደሳች ናቸው የተባለ ሲሆን በየአንዳንዱ ህንፃ ላይ አምስት አሳንሰሮች የሚገጠሙና ከአምስቱ አንዱ እስከ ዛሬ በሪል እስቴት ባልተለመደ መልኩ ትልልቅ እቃዎችን የሚያጓጉዝ ሰርቪስ ሊፍት ይኖረዋል ተብሏል። መናፈሻ፣ ጂም ፣ የመዋኛ ገንዳዎች፣ የመኪና  ማቆሚያ፣ የህፃናት መጫዎቻ ቦታና ሌሎችም ለኑሮ አስፈላጊ የሆኑ መሰረተ ልማቶች የሚገኙበት ቅንጡ መንደር እንደሚሆን የገለጹት ኃላፊዎቹ በቀጣይ ከሚዲያ ባለሙያዎች ጋር ያለውን ቁርኝት ለማጠናከር በማሰብ ጋዜጠኞቹ በተመቻቸው ጊዜ ቀረፃና ኤዲቲንግ የሚሰሩበት ትልቅና ዘመናዊ ስቱዲዮ በመገንባት ላይ መሆኑንም ዲኤምሲ ሪል እስቴት ሀሙስ ረፋድ ላይ ለቡ መብራት ሀይል በሚገኘው የሽያጭ ቢሮው በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ  አብራሯል።

Read 733 times Last modified on Saturday, 16 March 2024 20:31