Monday, 01 April 2024 07:37

”የኢትዮጵያ ሙዚቃ ቀን” በእስራኤል ሊካሄድ ነው

Written by 
Rate this item
(1 Vote)
  • • ጎሳዬ ተስፋዬ፣ ሳሚ ዳንና ጃኪ ጎሲ ይሳተፉበታል

           ታዋቂ የኢትዮጵያ ድምፃዊያን የሚሳተፉበት “የኢትዮጵያ ሙዚቃ ቀን” በእስራኤል ቴላቪቭ እንደሚካሄድ  አፍሮ ስታይል ኢንተርቴይመንት አስታወቀ፡፡  
    የእስራኤል የነፃነት ቀንን ምክንያት በማድረግ፣ ግንቦት 5 ቀን 2016 ዓ፣ም የኢትዮጵያ የሙዚቃ ቀን በቴላቪቭ የሚካሄድ ሲሆን፤ አፍሮ ስታይል ኢንተርቴይመንት ባዘጋጀው በዚህ  ኮንሰርት ላይ ጎሳዬ ተስፋዬ፤ ሳሚ ዳንና ጃኪ ጎሲ እንደሚጫወቱ ተገልጿል። ታዋቂ የጃማይካ ዳንስሆል አርቲስትም በኮንሰርቱ ላይ  እንደሚሳተፍ  ተጠቁሟል።
    የኢትዮጵያ የሙዚቃ ቀንን ለማክበር የተሰናዳው መርሐግብር ከሚያዚያ 29 እስከ ግንቦት 10 ቀን 2016 ዓ.ም  የሚቆይ ሲሆን፤ በተለያዩ የሙዚቃ ዝግጅቶችና በእስራኤል ከተሞች በሚካሄዱ ጉብኝቶች የሚታጀብ ይሆናል ተብሏል።
    ከሚያዚያ 29 እስከ ግንቦት 4 ቀን 2016 ዓ.ም በእየሩሳሌም ከተማ ጉብኝቶች የተዘጋጁ ሲሆን፤ ግንቦት 5  በሃንገር 09 አዳራሽ ቴላቪቭ ላይ የኢትዮጵያ ሙዚቃ ቀን ልዩ  ኮንሰርት እንደሚካሄድ ተጠቁሟል፡፡  በተመሳሳይ ቀን የቴላቪቭ ከተማን ለማስጎብኘትም ታቅዷል።  ግንቦት 8 ቀን 2016 ዓ.ም በሚር ያቆብ አዘጋጅነት በቴላቪቭ ሐንገር 09 አዳራሽ፣ የሬጌ ሙዚቃ ዝግጅትና ዳንስ እንደሚቀርብም ታውቋል።

Read 421 times