Friday, 05 April 2024 20:10

አዲስ አበባ ሌጀንድ ኢንተርናሽናል ፕሮ ቴኳንዶ አሶሴሽን የመጀመሪያዎቹን 3ኛ ደረጃ የዳኝነት ሰልጣኞች አስመረቀ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)
• ለመጀመሪያ ጊዜ በኦንላይን የተመዘገበ ሰርተፊኬት ተሰጥቷል
የአዲስ አበባ ሌጀንድ ኢንተርናሽናል ፕሮ ቴኳንዶ አሶሴሽን፤ የ2016 ዓ.ም የመጀመሪያዎቹን የ3ኛ ደረጃ የዳኝነት ሥልጠናና ዓለማቀፍ የፕሮ ቴኳንዶ የመጀመሪያ ራስን መከላከል ስልጠና ተሳታፊዎች ትላንት መጋቢት 26 ቀን 2016 ዓ.ም በወወክማ አዳራሽ አስመረቀ፡፡
ሥልጠናው ከአዲስ አበባና ከክልሎች ለተውጣጡ 28 ተሳታፊዎች ለ15 ቀናት ሲሰጥ የቆየ ሲሆን፤ ተመራቂዎቹ ለመጀመሪያ ጊዜ በኦንላይን የተመዘገበ ሰርተፊኬት ማግኘታቸው ታውቋል፡፡
 
ከሰልጣኞቹ መካከል 19 ያህሉ ሥልጠናውን በተሟላ መልኩ አልፈዋል የተባለ ሲሆን ሁለቱ አለማለፋቸው ነው የተነገረው፡፡
በምረቃ ሥነስርዓቱ ላይ እንደተነገረው፤ ሳኦል ኹነቶች ለአራት ሰልጣኞች የስፖርት ማዘውተሪያ አዳራሽ ያመቻቸ ሲሆን፤ በቅርቡ ፒያሳ አካባቢ በኮሪደር ልማት ሳቢያ የስፖርት ማዘውተሪያ ለፈረሰበት አንድ ወጣት በቀጣይ ቦታ ለማመቻችት ቃል ተገብቶለታል።
የአዲስ አበባ ሌጀንድ ኢንተርናሽናል ፕሮ ቴኳንዶ አሶሴሽን ፕሬዚዳንት ማስተር ሃይለየሱስ ፍስሃ በመርሐግብሩ ላይ እንደገለጹት፤ የተሰጠው 3ኛ ደረጃ የዳኝነት ሥልጠና፣ ሌጀንድ ኢንተርናሽናል በኢትዮጵያ የሠጠው የመጀመሪያ ኮርስ ነው፡፡
የሌጀንድ ኢንተርናሽናል ፕሮ ቴኳንዶ አሶሴሽን የአፍሪካ ፕሬዚዳንት የኢትዮጵያ የበላይ ጠባቂ ግራንድ ማስተር (ፒ ኤች ዲ በማርሻል አርት ሳይንስ) ሄኖክ ግርማ፣ለተመራቂዎቹ ሰልጣኞች ሽልማት ሰጥተዋል፡፡
 
ይህ በዚህ እንዳለ፣ የአዲስ አበባ ወርልድ ቴኳንዶ ፌዴሬሽን ከሳኦል ኩነቶች ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የአዲስ አበባ ወርልድ ቴኳንዶ 2016/2024 ኦፕን ቶርናመንት፣ ከግንቦት 3 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ የሚካሄድ ሲሆን፤ ውድድሩን አስመልክቶ ነገ ቅዳሜ በአራት ኪሎ ስፖ/ትም/ሥልጠና ማዕከል በሚገኘው ትልቁ ጅምናዚየም ጋዜጣዊ መግለጫ እንደሚሰጥ ታውቋል፡፡
Read 462 times Last modified on Friday, 05 April 2024 20:33