በባሮክ ኢቨንት ኦርጋናይዘር አ.ማ የተዘጋጀው የፋሲካ ባዛርና ኤክስፖ ቅዳሜ ሚያዝያ 12 ቀን 2016 ዓ.ም ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት፣ ባለሃብቶችና ታዋቂ ግለሰቦች በተገኙበት በሚሊኒየም አዳራሽ በይፋ ተከፈተ፡፡
የፋሲካ ባዛርና ኤክስፖው እስከ ሚያዝያ 26 ቀን 2016 ዓ.ም ለጎብኚዎች ክፍት ሆኖ እንደሚቆይ ታውቋል፡፡
በዚህ ባዛርና ኤክስፖ ሸማቹ የህብረተሰብ ክፍል በዓልን ምክንያት አድርጎ ከሚገጥመው የዋጋ ንረት በተመጣጣኝና በቅናሽ ዋጋ ከራሱ ከአምራችና አስመጪው የሚገበያይበት ሲሆን፤ አምራችና ሸማቹም ከፍተኛ የገበያ ሽያጭ በማግኘት ተጠቃሚ የሚሆንበት ነው ተብሏል፡፡
Published in
ዜና