በደራሲ ባየህ ንጉሴ የተዘጋጀው “ፋሽን” የተሰኘ በፋሽን እና ሞዴሊንግ ላይ ትኩረቱን ያደረገ መጽሐፍ ቅዳሜ ሚያዝያ 19/2016 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ጀምሮ የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር) አዳራሽ ጥሪ የተደረገላቸው
የጥበብ ቤተሰቦች እና እንግዶች በተገኙበት ይመረቃል ይመረቃል።በስድስት ምዕራፍ የተከፈለው መጽሐፉ ስለ ሞዴሊንግ አይነቶች፣ ሞዴል የመሆን ትሩፋቶች እና ተግዳሮቶች፣ የቁንጅና ውድድር፣ ሻምፖ እና ኮድሽነር አመራረጥ፣ ፖርትፎሊዮና ሌሎችም ዝርዝር ጉዳዮችን ይዟል።
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና