ላለፉት ሦስት ወራት በኢቴቪ ሦስት ዝግጅቶቹን ሲያቀርብ የነበረው አርኪ ካሜራ ዛሬ ተመርቆ በይፋ ስራውን እንደሚጀምር አዘጋጆቹ አስታወቁ፡፡ አዘጋጆቹ የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት (ኢሬቴድ) እና MS Consulting Architects ለዝግጅት ክፍላችን እንዳስታወቁት፤ ዛሬ ካዛንቺስ በሚገኘው የአዲሱ ራዲሰን ብሉ ሆቴል የሚመረቀው የ45 ደቂቃ ዝግጅት በኪነ ሕንፃ፣ ከተማ ፕላን፣ ዲዛይን እና ተያያዥ ጉዳዮች “ሕንፃም ይታከማል” በሚል ንዑስ መርህ በመታገዝ ዘወትር ሐሙስ ምሽት፣ ቅዳሜ እና ሰኞ በቴሌቪዥን ቻናሉ ይታያል፡፡