አውቶብሱ ለመቆም ፍጥነቱን መቀነስ ሲጀምር የአበባ ዕቅፍ የያዙት ሽማግሌ ከተቀመጡበት ብድግ አሉ ፡፡
መውረጃቸው ደርሶ ነው፡፡ ከመውረዳቸው በፊት ግን በቀጥታ ያመሩት ወደ ድምቡሽቡሿ ወጣት ነበር፡፡ አጠገቧ ሲደርሱም ፈገግ አሉና በእጃቸው የያዙትን ዕቅፍ አበባ በከፊል የተጋለጡ ፍም ጭኖቿ ላይ አስቀመጡላት፡፡ ወጣቷ በድንጋጤ የምትለው ጠፍቷት ስትርበተበት ሽማግሌው ተናገሩ “አበቦቹን የወደድሻቸው ስለመሰለኝ ነው፡፡ በእርግጥ ለሚስቴ የገዛሁት ስጦታ ነበር…ግን ለአንቺ በመስጠቴ አይከፋትም…ደሞ አልዋሻትም…እነግራታለሁ” ብለው መልሷን ሳይጠብቁ ከአውቶብሱ ወረዱ፡፡
ወጣቷ በአበቦቹ ብትደሰትም አንዲት የምስጋና ቃል ትንፍሽ ሳትል ሽማግሌው ስላመለጧት ቆጭቷታል፡፡
ወዲያው ዓይኗን በመስኮት ስትልክ ሽማግሌው መንገድ ዳር ላይ ወዳለው ቤ/ክርስቲያን ገብተው አንድ የመቃብር ሃውልት ጋ ቆመው ተመለከተች፡፡
( “chicken soup ” ከሚለው መፅሃፍ ታሪክ መነሻ ሃሳብ ተወስዶ የተፃፈ )