በጋዜጠኛ፣ ደራሲና ሃያሲ ደረጄ በላይነህ የዛሬ አምስት ዓመት በመጽሐፍ ታትሞ የነበረው “የዲያስፖራና የአገር ቤት ልጅ ፍቅር” የፍቅር ምልልስ መጽሐፍ በትረካ መልክ በሲዲ ታትሞ ቀረበ፡፡ ተራኪዎች “የኢትዮ ሊትሬቸር ፖል ቶክ” ወንድ እና ሴት ጋዜጠኞች ናቸው፡፡ “የዲያስፖራና የሀገር ቤት ልጅ ፍቅር” በ2000 ዓ.ም “የናፍቆት ጥላዎች” በሚል ርእስ ታትሞ እንደነበር ይታወቃል፡፡ በጃዕፈር መጽሐፍት ቤት እና በሌሎችም መደብሮች ለሽያጭ የቀረበው የትረካ ሲዲ በ18ብር እየተሸጠ ነው፡፡ ደራሲው ካሁን ቀደም ስድስት መፃሕፍት አሳትሞ ለንባብ አብቅቷል፡፡