Administrator

Administrator

ኢትዮጵያ ምርቶቿን ከቀረጥ ነጻ በሆነ ሥርዓት ወደ አፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ማዕቀፍ አባል ሀገራት መላክ እንደምትጀምር የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዶ/ር ካሳሁን ጎፌ፤ መስከረም 29 ኢትዮጵያ አህጉራዊ ነፃ የሸቀጦች ንግድ ትግበራን በይፋ ታስጀምራለች ሲሉ ተናግረዋል።
በዚህም ኢትዮጵያ በሚቀጥለው ሳምንት ወደ አፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ማዕቀፍ አባል ሀገራት ለመጀመሪያ ጊዜ ምርቷን ከቀረጥ ነፃ መላክ ትጀምራለች ያሉት ሚኒስትሩ፤ ይህም የንግድ ተወዳዳሪነትን እንደሚጨምር ተናግረዋል።
የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ስምምነት ትግበራ፣ ከንግድ ቀጠናነት ባሻገር የአፍሪካ ዘላቂ ዕድገትን ለማረጋገጥ የጎላ ጠቀሜታ እንደሚኖረው ሚኒስትሩ አክለው ገልጸዋል፡፡
ቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
የውሃ ሚኒስትር ሐብታሙ ኢተፋ፣ ሰሞኑን በሱዳን የተከሠተው ጎርፍ ከሕዳሴ ግድብ ጋር የተያያዘ አይደለም ማለታቸውን አሶሴትድ ፕሬስ ዘግቧል።
ሚኒስትሩ ይህን የተናገሩት፣ አንዳንድ የግብጽ የውሃ ባለሙያዎች፣ የሱዳኑን ጎርፍ በሕዳሴ ግድብ ምክንያት የተከሠተ መኾኑን መግለጣቸውን ተከትሎ እንደኾነ ዘገባው ጠቅሷል።
ጎርፉ የኋይት ናይል ወንዝ ሙላት የፈጠረው ሊሆን ይችላል ያሉት አቶ ሐብታሙ፣ ግድቡ ባይኖር የጎርፍ አደጋው እጅግ የከፋ ሊሆን ይችል ነበር ብለዋል ተብሏል።
ግድቡ እንዲያውም ጎርፉ ከፍተኛ ውድመት እንዳያደርስ በመከላከል ረገድ ቁልፍ አስተዋጽዖ ማድረጉን ሚኒስትሩ መግለጣቸውንም ዘገባው አመልክቷል።
ሚኒስትሩ፣ ኢትዮጵያ ከግድቡ ትርፍ ውሃ አለመልቀቋንም ተናግረዋል ተብሏል።
ዋዜማ-
ቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
በኢትዮጵያ ሀገራዊ የኤችአይቪ ስርጭቱ ካላፉት ዓመታት የተሻለ ቢሆንም፣ ከክልል ክልል፣ ከከተማ ከተማ የስርጭቱ መጠን እንደሚለያይ ተነግሯል።
በተለይ በወጣቶችና ለኤችአይቪ እጅግ ተጋላጭ ተብለው የተለዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ላይ የመያዝ እድሉ በመጨመሩ መዘናጋት እንዳያስከትል ጥንቃቄ እንደሚያስፈልግ የጠቆሙት በኤድስ ሄልዝ ኬር ፋውንዴሽን (AHF) ኢትዮጵያ የኤችአይቪ መከላከልና ምክር አገልግሎት አስተባባሪ እንዲሁም የህብረተሰብ ጤና ባለሙያ የሆኑት አቶ ቢኒያም ባዩ ናቸው።
በጠቅላላው የማህበረሰብ ክፍል ውስጥ ያለው የስርጭት መጠን ከዚህ ቀደም ከ 1 በመቶ በላይ ተሻግሮ የነበረውን በትብብር በመሰራቱ የስርጭቱ መጠን ከጊዜ ወደ ጊዜ እየቀነሰ ቢመጣም፣ በተለይም በስራቸውና በጾታቸው ምክንያት ተጋላጭ የሆኑ ሰዎች ቁጥር ከፍተኛ መሆኑንም አቶ ቢኒያም ይናገራሉ።
በወጣቶች በኩል የኤችአይቪ የመያዝ ቁጥርም ከፍተኛ ነው የሚሉት ባለሙያው፤ በኤችአይቪ መከላከል ላይ የሚሰሩ አዳዲስ ጥናቶች ወጣቶች ላይ ትኩረት ሊያደርጉ ይገባል ብለዋል፡፡
በቅርብ የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲቱዩት በሰጠው መረጃ መሰረት፤ በወጣቶች ላይ ያለው የኤች አይቪ የስርጭት ሁኔታ 1.7 በመቶ እንደሚጠጋ የተነገረ ሲሆን፤ ከትምህርት ቤት ውጪ ባሉ ወጣቶች 2.2 በመቶና በትምህርት ቤት ባሉት ደግሞ 1.3 በመቶ ነው ተብሏል።
በአጠቃላይ ወጣቶችን ስንመለከት ካለው የኤችአይቪ ስርጭት ሁኔታ ከፍ ያለ መሆኑንና ከሌላው የማህበረሰብ ክፍል በተለየ ሁኔታ ከ10 እስከ 24 ዓመት የእድሜ ክልል ላይ ብዙ መስራት እንደሚያስፈልግ በቅርብ ጊዜ እየወጡ ያሉ መረጃዎች እንደሚያሳዩ ባለሙያው መጥቀሳቸውን ሸገር ዘግቧል፡፡
በትግራይ ክልል የአስገድዶ መድፈር ሁኔታዎች ባለመቆማቸው፣ ወላጆች በ12 ዓመት ዕድሜ ላይ የምትገኝ ልጃቸውን እየዳሩ እንደሚገኙ ተገልጿል፡፡
ፆታን መሠረት አድርገዉ በሴቶች ላይ የሚፈፀሙ የኃይል ጥቃቶችን ለመከላከል የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች በተለይም ከአምስት ዓመት ወዲህ ሲሰራ ቢቆይም፣ ከፀጥታዉ ችግር ጋር ተይያዞ ሙሉ ለሙሉ ጥቃቶችን ማስቆም አለመቻሉን ትግራይ ክልልን ጨምሮ በኦሮሚያ ምሥራቅ ሐረርጌ እንዲሁም በአማራ ክልል ደቡብ ጎንደር የተደረገ ጥናት አመላክቷል፡፡
ይህም የተገለፀው የኢትዮጵያ ሴቶች ማህበራት ቅንጅት፣ በትናንትናው እለት "እሷ ትመራለች" በሚል ላለፋት አምስት ዓመታት ሲተገብር የቆየው ፕሮጀክት መጠናቀቁን አስመልክቶ በተዘጋጀው መድረክ ላይ በቀረበው የጥናት ሪፖርት ነው፡፡
በዚህ ወቅት የታዳጊዎችና ስርአተ ጾታ አለም አቀፍ ድርጅት ጥናት የኢትዮጵያ ተወካይና ተመራማሪ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ዶክተር ወርቅነህ አበበ፤ በትግራይ ክልል ከጦርነቱ አስቀድሞ የልጅነት እርግዝናን ለመግታት የግንዛቤ ስራዎች ሲሰሩ መቆየታቸውን ተናግረዋል።
አክለውም፤ ከጦርነቱ በፊትና በኋላ እነዚህ ሁኔታዎች በመቆማቸው፣ በክልሉ እንደ አዲስ በልጅነት የሚከሰት እርግዝና መንሰራፋቱን አስረድተዋል፡፡
ወላጆች ጥቃቱን ለመከላከል በሚል ልጆቻቸውን ለ-ያለእድሜ ጋብቻ እየዳረጉ መሆኑን ባቀረቡት የጥናት ሪፖርት አመላክተዋል፡፡
ችግሩ በተመሳሳይ በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ሃረርጌ፣ በአማራ ክልል ደቡብ ጎንደር ዞን ደብረታቦር፣ በአፋርና ሶማሊያም አሳሳቢ መሆኑን ጠቁመዋል ሲል ሃራምቤ ሬዲዮ ዘግቧል፡፡
May be an image of 3 people and text that says '"End child marriage and say no to teenage pregnancy" CHR ican mUnion mignto lign to meignto WMarriage'
 
 
 
 
 
በሀገረ ስኮትላንድ የሀበሻ ምግብ ቤት የከፈተችው ወይዘሮ ሙና፤ የኢትጵያን ምግቦች በማስተዋወቅ ዝናን አትርፋለች፡፡
በራሷ ሼፍ ሙና የተመሰረተው ምግብ ቤቱ በሀገራችን በብዛት የተለመደውና የኢትዮጵያውያን መለያ የሆነው በየአይነቱ፣ ጥብስ፣ ክትፎ፣ ዶሮ ወጥ፣ ጥሬ ስጋ፣ ዱለትና ሽሮ የመሳሰሉ ምግቦች የሚገኝበት ሬስቶራንት ነው፡፡
ከኢትዮጵያ ተጉዘው ወደ ስኮትላንድ ጎራ የሚሉ ኢትዮጵያውያንን እንዲሁም የኢትዮጵያን ምግብ የለመዱ የሀገሬው ስኮትላንዳውያንን ሞቅ ባለ መስተንግዶ ለዓመታት አገልግሎት ሲሰጥ ቆይቷል፡፡
ወይዘሮ ሙና ከምግብ ቤትና የንግድ ስራዎቿ ባለፈ የኢትዮጵያን ምግቦች በተመረጡ አደባባዮች ይዛ በመውጣት ማስተዋወቋ ደግሞ ሬስቶራንቷን በውጭ ሀገር ከተከፈቱ የሀበሻ ምግብ ቤቶች የተለየ ያደርገዋል፡፡
አንዳንዴ ምግቦችን በነፃ በማቅረብና በማስተዋወቅ እንዲሁም ምግቦች ላይ ልዩ የዋጋ ቅናሽ በማድረግ የኢትዮጵያውያን ምግቦች በስኮትላንድ እንዲታወቁና እንዲለመዱ ማድረግ ችላለች፡፡
ብዙ ጊዜ ምግቦቿን በዋና ዋና ጎዳናዎች ላይ ይዛ በመውጣት እየተመገበች ሌሎችም እንዲመገቡ የምታደርገው የኢትዮጵያ ምግብ አምባሳደሯ ሼፍ ሙና፤ መንገደኞችን ምግቡን በነፃ በማቅመስ ታለማምዳለች፡፡
በዚህም በርካታ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ አትዮጵያውያን እንዲሁም የስኮትላንድ ዜጎች ኢትዮጵያና ምግቦቿን እንዲያውቁ ማድረግ ችላለች፡፡
በዚህ ብቻ ሳታበቃ የኢትዮጵያውያን ብሔር ብሔረሰቦች ባህል፣ ወግ፣ ቋንቋ፣ ጭፈራና የአለባበስ ዘዴ በማስተዋወቅ ለሀገሯ የአምባሳደርነት ሚናዋን እየተወጣች ትገኛለች፡፡
ግለሰቧ የኢትዮጵያን ምግቦች ለማስተዋወቅ በምታደርገው ጥረትም በስኮትላንድ ባይት በተባለው ጋዜጣ እንዲሁም ኢድንበርግ በተባለው የስነ ምግብ ድረ ገፅ ላይ አርዕስት መሆን ችላለች፡፡
-WMCC-
ቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
 
 
 
 
 
 
 
 
ኬንያ ዜጎቿ ወደ ሩሲያ በግዳጅ እየተወሰዱ በዩክሬን ጦርነት ውስጥ እንዲሳተፉ ይደረጋሉ መባሉን ተከትሎ ምርመራ መጀመሯ ተሰምቷል፡፡
ምርመራው ኬንያዊው አትሌት ኢቫንስ ኪቤት፣ የሩሲያ ሰራዊትን እንድቀላቀል ተታልዬ ነበር ማለቱን ተከትሎ የመጣ ነው ተብሏል፡፡
የኬንያ ባለስልጣናት እውነታውን እንዲሁም የተጎጂዎችን ደህንነት ለማረጋገጥ፣ ከሩሲያና ከዩክሬን ባለስልጣናት ጋር እየተነጋገሩ መሆኑ ተዘግቧል፡፡
ይህ ሁኔታ በግጭት ቀጠና ውስጥ የውጭ ሀገር ዜጎችን ኢላማ ያደረገ ቅጥር ላይ ያለውን ስጋት አጉልቶ እንደሚያሳይ ተጠቁሟል፡፡
ኬንያ አንዳንድ ዜጎቿ ወደ ሩሲያ ጦር ሰራዊት በግዳጅ እንደገቡና አሁን በዩክሬን የጦር ምርኮኞች ሆነው እንደሚገኙ የሚገልጽ ዘገባ ከወጣ በኋላ ነው የማጣራት ምርመራውን የከፈተችው፡፡
ቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
• ጉብኝቱ በእዳ ሽግሽግ ዙሪያ ለመምከርና የኢኮኖሚ
ትብብርን ለማጠናከር ያለመ ነው ተብሏል
በአዲሱ የብሔራዊ ባንክ ገዢ ዶ/ር ኢዮብ ተካልኝ የተመራ ልዑክ በቻይና ቤጂንግ የሥራ ጉብኝት እያደረገ ሲሆን፤
ጉብኝቱ በእዳ ሽግሽግ ዙሪያ ለመምከርና በኢትዮጵያና ቻይና መካከል ያለውን የኢኮኖሚ ትብብር ለማጠናከር ያለመ ነው ተብሏል፡፡
ልዑካኑ በቤጂንግ ቆይታቸው ከቻይና ገንዘብ ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች፣ ከቻይና ሕዝብ ባንክ፣ ኤግዚም ባንክ እና ከተለያዩ የንግድ ተቋማት አመራሮች ጋር እንደሚወያዩ ይጠበቃል፡፡
በዚህም በኢትዮጵያ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም የተከናወኑ ሥራዎችንና የተገኙ ውጤቶችን በተመለከተ ገለጻ እንደሚያደርጉ ባንኩ አስታውቋል፡፡
በቀጣይ በኢትዮጵያ የመልማት አቅም ያላቸው የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶችን በተመለከተ ዝርዝር ማብራሪያ እንደሚሰጥ ተጠቁሟል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ ገቢዎች ቢሮ፣ ከመንግሥት ገቢ ሊቀንሱ የሚችሉ ከባድ የሂሳብ ግድፈቶች የፈጸሙ የ10 የሂሳብ ባለሙያዎችና ኦዲተሮች የሙያ ፈቃድ እንዲሰረዝ ለኢትዮጵያ የሂሳብና ኦዲት ቦርድ ጥያቄ አቀረበ።
ቢሮው እንዳስታወቀው፣ በ2017 በጀት ዓመት ውስጥ 13 የግብር ከፋዮችን የሂሳብ መዝገብ በመመርመር ከባድ ግድፈቶች የተገኙባቸውን 10 ባለሙያዎች ለይቷል። ቢሮው ባደረገው የቅድመ ኦዲት ምርመራ፣ እነዚህ ባለሙያዎች ያዘጋጇቸው የሂሳብ መዝገቦች ከፍተኛ መጠን ያለው የገቢ ልዩነት እንዳለባቸውና በታክስ ስወራ መንግሥት ሊያገኘው የሚገባውን ገቢ ሊያሳጣ እንደነበር ገልጿል።
በዚህም መሰረት፣ ቢሮው ከፍተኛ የገንዘብ መጠን የመንግስትን ጥቅም ሊያሳጣ የሚችል ግድፈት የፈጸሙ 10 የሂሳብ ባለሙያዎችና ኦዲተሮች የሙያ ፈቃዳቸው እንዲሰረዝ ጥያቄ አቅርቧል። የቢሮው ሃላፊዎች እነዚህ ባለሙያዎች በቦርዱ የሙያ ፈቃድ የተሰጣቸው መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
ቢሮው በተጨማሪም የከተማው ነዋሪዎችና የግብር ከፋዮች፣ ፈቃዳቸው እንዲሰረዝ የተጠየቀባቸው እነዚህ የሂሳብ ባለሙያዎች የሚያዘጋጁትን የሂሳብ መዝገብ እንደማይቀበል አስጠንቅቋል። የስም ዝርዝራቸውን ከቦርዱ በመጠየቅ የሙያ ስነ ምግባሩን ጠብቀው በሚሰሩ የሂሳብ ባለሙያዎችና ኦዲተሮች የሂሳብ መዝገቡን በማሰራት እንዲያቀርብም አሳስቧል፡፡
የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ከዚህ ቀደምም በሂሳብ መዝገብ አዘገጃጀት ላይ የሚስተዋሉ ግድፈቶችን ለመቀነስ ከቦርዱና ከሙያ ማህበራት ጋር በመተባበር መፅሄት በማዘጋጀትና በመወያየት ትምህርት ሲሰጥ እንደነበር አስታውሷል።
አስ-
• በአባይ ውሃ ላይ የሚያሳድረውን ተጽእኖ "ትልቅ ችግር" ሲሉ ገልጸውታል
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ባለፈው ቅዳሜ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ላይ በሰጡት አስተያየት፤ ግድቡ በአባይ ውሃ ላይ የሚያሳድረው ተጽእኖ ለግብፅ "ትልቅ ችግር" የሚፈጥር ነው ብለዋል፡፡
"ኢትዮጵያ ውስጥ በዓለም ላይ እንደ ትልቅ ግድብ የሚወራለት ትንሽ ግድብ ገንብተዋል፡፡ እናም ወደ አባይ ወንዝ በሚፈሰው ውሃ ላይ ተጽዕኖ ያደርጋል፤ ያ ችግር ነው ትላላችሁ? እኔ ትልቅ ችግር ነው እላለሁ" ሲሉ ተናግረዋል፡፡
ፕሬዚዳንቱ በንግግራቸው፤ ታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ፤ በህንድና ፓኪስታን፣ ታይላንድና ካምቦዲያ፣ አርሜኒያና አዘርባጃን፣ ኮሶቮና ሰርቢያ፣ እንዲሁም በእስራኤልና ኢራን መካከል ያለውን ውጥረት ጨምሮ ከሌሎች ዓለም አቀፍ ቀውሶች ጋር አዛምደው አንስተውታል፡፡
ባለፈው ሐምሌ ወር ትራምፕ፣ ታላቁ የህዳሴ ግድብ በአብዛኛው በአሜሪካ የገንዘብ ድጋፍ የተገነባ ነው ሲሉ አወዛጋቢ የሆነ መልዕክት ማስተላለፋቸው አይዘነጋም፡፡
ቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
May be an image of 1 person and the Oval Office
 
 
 
 
Page 6 of 790