Administrator
Friday, 12 September 2025 16:03
በኖርዌይ ለአገራዊ ምርጫ የሚወዳደረው የቀድሞው የኦፌኮ አባል
"በአገር ቤት የነበረኝ የፖለቲካ ተሳትፎ ምንም አልረዳኝም"
ከኢትዮጵያ ወደ ኖርዌይ ከሄደ አስር ዓመት ሆኖታል። ኢትዮጵያ ሳለ በጅማ ዩኒቨርስቲ ለ11 ዓመታት የቋንቋ እና ሥነ ልሳን መምህር ነበር። የሦስተኛ ዲግሪውን ለመሥራት ነበር ወደ ኖርዌይ ያመራው። በእርግጥ በኢትዮጵያ ሳለ ለፖለቲካ ባዕድ አልነበረም። የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) አባል በመሆን በፓርቲው የተለያዩ እንቅስቃሴዎች ውስጥ ተሳትፏል።
ቢቢሲ እንደዘገበው፤ ወደ ኖርዌይ ለትምህርት ሲሄድ በኢትዮጵያ የተለያዩ ከተሞች ውስጥ የተቃዋሞ እንቅስቃሴ ተስፋፍቶ ነበር። የቀድሞው የጅማ ዩኒቨርስቲ መምህር አማኑዔል ራጋ ወደ አገሩ መመለስ ስጋት ሲፈጥርበት በኖርዌይ ኑሮውን አደረገ። በኖርዌይ ዜግነት አግኝቶ መኖር ከጀመረ ወዲህ ደግሞ ፖለቲካ ውስጥ በመምረጥም ሆነ በመመረጥ መሳተፍ እንዳለበት ወሰነ።
ከዚያም በኋላ የክርስቲያን ዲሞክራቲክ ፓርቲ አባል ሆኖ መሳተፍ ጀመረ። ከሁለት ዓመት በፊት ፓርቲውን ወክሎ ለኦስሎ ከተማ ምክር ቤት ተወዳድሮ ነበር። ያ ተሳትፎ በፈጠረለት ዕድል የኦስሎ አንድ ክፍለ ከተማ የክርስቲያን ዲሞክራቲክ ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበር ሆኖ ተመረጠ። በዚያውም በአካባቢው የክርስቲያን ዲሞክራቲክ ፓርቲ አስተዳደር አባል መሆን ቻለ።
ኖርዌይ ወደ አገራዊ ምርጫ ስታመራ የተለያዩ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች፣ ፓርቲው እንዲሁም ግለሰቦችም ፓርቲውን ወክሎ እንዲወዳደር መረጡት። አሁን ደግሞ በአገራዊ ምርጫ ላይ ፓርቲውን ወክሎ እየተሳተፈ ነው።
የኖርዌይ ፖለቲካ ከኢትዮጵያ እጅጉን የተለየ ነው የሚለው አማኑዔል፤ በአገር ቤት የነበረው የፖለቲካ ተሳትፎ ምንም እንዳልረዳው ይናገራል።
"ዲሞክራሲና አካታች የሆነ መንፈስ መፍጠርን፣ ተቃዋሚ ቢመጣ እንደ ጠላት ማየት ሳይሆን የራሱ ዕይታ ያለው የአገሪቱ ዜጋ መሆኑን መቀበልን የተማርኩት እዚህ ነው" ሲል ከቢቢሲ ጋር በነበረው ቆይታ ወቅት ተናግሯል።
በአገሪቱ ውስጥ በርካታ ዕድሎች አሉ የሚለው አማኑዔል፤ "ቁጭ ብሎ ከመመልከት ይልቅ በመሳተፍ የበኩሌን አስተዋጽኦ በማድረግ የምፈልገውን ለመለወጥ መጣር እንዳለብኝ ወሰንኩ" ይላል።
አማኑዔል በኖርዌይ ፖለቲካ ውስጥ ሰፊ አንቅስቃሴ የሚያደርጉ ፓርቲዎች ቢኖሩም የክርስቲያን ዲሞክራቲክ ፓርቲን የመረጠበት ምክንያት በቤተሰብ ዕሴቶች፣ በሰው ልጆች መብትና በሰብዓዊነት ላይ አተኩሮ ስለሚሠራ መሆኑን ለቢቢሲ ተናግሯል።


Published in
ዜና
Tagged under
Friday, 12 September 2025 10:10
ቡርኪናፋሶ ቪዛ አያስፈልግም አለች!!
አሁን ሁሉም አፍሪካውያን ወደ ቡርኪናፋሶ ለመግባት ቪዛ አያስፈልጋቸውም ተብሏል፡፡ የቡርኪናፋሶ መንግሥት ማንኛውም አፍሪካዊ ያለቪዛ ወደ አገሪቱ መግባት እንደሚችል አስታውቋል፡፡
Published in
ዜና
Tagged under
Friday, 12 September 2025 10:09
ጋና ከአሜሪካ የተባረሩ 14 የምዕራብ አፍሪካ ዜጎችን ተቀበለች
ጋና ከአሜሪካ የሚባረሩ ሰነድ አልባ የምዕራብ አፍሪካ ዜጎችን ለመቀበል በተስማማችው መሰረት፣ 14 የምዕራብ አፍሪካ ዜጎችን መቀበሏ ተዘግቧል፡፡
14 ግለሰቦችን ያካተተው የመጀመሪያው ቡድን አክራ መድረሱም ተሰምቷል። ከነዚህም መካከል ናይጄሪያውያንና ቢያንስ አንድ ጋምቢያዊ ይገኙበታል ተብሏል።
የጋና ፕሬዝዳንት ጆን ድራማኒ ማሃማ ውሳኔው በከፊል በ ECOWAS የነፃ እንቅስቃሴ ፕሮቶኮል ምክንያት ነው ብለዋል - በፕሮቶኮሉ መሰረት ምዕራብ አፍሪካውያን ያለ ቪዛ ወደ ጋና መግባት ይችላሉ።
ጋና ከአሜሪካ የምትቀበላቸውን ሰነድ አልባ የምዕራብ አፍሪካ ዜጎች ቁጥር አልገለጸችም።
Published in
ዜና
Tagged under
Friday, 12 September 2025 10:00
ኬንያና ሩዋንዳ የእስራኤልን ጥቃት አወገዙ
ኬንያና ሩዋንዳ እስራኤል ባለፈው ማክሰኞ በኳታር ዋና ከተማ ዶሃ ላይ የፈጸመችውን ጥቃት ባወጡት መግለጫ አወገዙ።
የኬንያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ትናንት ሐሙስ መስከረም 1 ቀን 2018 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ፤ “ጥቃቱ የኳታርን ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት መጣስ ብቻ ሳይሆን ለመካከለኛው ምስራቅ ቀጠና እና ለአለም አቀፍ ሰላምና ደህንነት ከፍተኛ ስጋት ይፈጥራል” ብሏል።
ሩዋንዳ በበኩሏ ትናንት ባወጣችው መግለጫ፤ "እስራኤል መሠረታዊ የግዛት ሉዓላዊነትን ያለአግባብ መጣሷ አደገኛ ነው፤ ይህም ዓለምን ወደ ሥርዓት አልበኝነት እየመራት ነው" ብላለች።
የሁለቱ አገራት መግለጫዎች የተሰሙት ቀደም ሲል ሌሎች እንደ ናይጄሪያ፣ግብፅ፣ሞሮኮ፣አልጄሪያና ሶማሊያ ያሉ የአፍሪካ ሀገራት በተመሳሳይ እስራኤል በኳታር ላይ የፈጸመችውን ጥቃት ማውገዛቸውን ተከትሎ ነው።


Published in
ዜና
Tagged under
Tuesday, 09 September 2025 08:20
ጳጉሜ 4 ቀን 2017 ዓ/ም ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታው ተጠናቆ ለምረቃ በመብቃቱ መላውን ኢትዮጵያ ህዝብ እንኳን ደስ አላቹሁ
Published in
ዜና
Tagged under
Tuesday, 09 September 2025 07:04
በሕዳሴው ግድብ ዙሪያ ለሚመሰረቱ ከተሞች ማስተር ፕላን እየተዘጋጀ ነው
• ዘመናዊ የመኖሪያና የቱሪዝም ከተሞች ይመሰረታሉ ተብሏል
በሕዳሴው ግድብ በተፈጠረው "ንጋት" 246 ኪ.ሜ ባህር ዙሪያ ለሚመሰረቱ ዘመናዊ ከተሞች ማስተር ፕላን የማዘጋጀት ሥራ መጀመሩ ተገለጸ፡፡
በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ዙሪያ ለሚመሰረቱ ዘመናዊ የመኖሪያና የቱሪዝም ከተሞች ማስተር ፕላን የማዘጋጀት እንዲሁም የአሶሳ ከተማ የማስፋፊያ ፕሮጀክት ሥራ፤ 'ሲቲስ አሊያንስ' በተሰኘ ድርጅት አማካኝነት በይፋ መጀመሩን የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ አስታውቋል።
ወደፊት በአካባቢው ብዙ ከተሞች ይመሰረታሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ የተገለጸ ሲሆን፤ አካባቢው የዓለም አቀፍ ባለሀብቶችን ትኩረት መሳቡ ተነግሯል።
ቀደም ሲልም የኢንቨስትመንት ፈቃድ የወሰዱ አልሚዎች እንዳሉ የጠቆሙት ዳይሬክተሩ፤ የሐይቁን መሃል በተመለከተ ከፌደራል መንግሥት ጋር በትኩረት የሚሰራ መሆኑ የተጠበቀ ቢሆንም፣ ብዙ ደሴቶች በመኖራቸው ጥናት እንደሚፈልግ ተናግረዋል።
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…


Published in
ዜና
Tagged under
Tuesday, 09 September 2025 07:01
ኢትዮጵያ ህዳሴን ለገደበችበት ካሳ መጠየቅ እንዳለባት ተገለጸ
የህዳሴው ግድብ ግንባታ ጠቃሚነቱ በተለይ ለታችኛዎቹ ተፋሰስ ሀገራት በመሆኑ ኢትዮጵያ በራሷ ፋይናንስ ግድቡን ለገደበችበት ካሳ መጠየቅ አለባት ሲሉ ኢንጂነር ጥላሁን ኤርዲኖ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
በአፍሪካ ቀንድና በመካከለኛው ምስራቅ የሃይድሮ ፖለቲካ ተንታኝ ኢንጂነር ጥላሁን ኤርዲኖ፤ ለኢፕድ እንደገለጹት፤ ከግድቡ ግብጽና ሱዳን ከፍተኛ ተጠቃሚ በመሆናቸው ኢትዮጵያ ግድቡን ለብቻዋ መገደብ አልነበረባትም።
የህዳሴ ግድብ ከሌሎች ጥቅሞቹ ባሻገር ግብጽ ውስጥ በከፍተኛ ትነት የሚባክን ውሃን አስቀርቷል ያሉት ኢንጂነር ጥላሁን፤ በዚህም በቀጠናው ተጨማሪ የውሃ ሀብት እንዲኖር ማስቻሉን ጠቁመዋል፡፡
እንደ ኢንጂነር ጥላሁን ገለጻ፤ ግድቡ መገንባቱ የታችኛው ተፋሰስ ሀገራት የሚደርስባቸውን አደጋ ማስቀረት ችሏል፤ ለአብነትም ጎርፍና የመሳሰሉትን ማንሳት ተገቢ ነው፡፡ በዚህም በዓመት ከሦስት እስከ አራት ጊዜ ያለምንም አደጋ ማምረት እንዲችሉ እድል ፈጥሯል፡፡
ግድቡ ከዚህ በተጨማሪም የተለያዩ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታዎች እንዳሉት የጠቆሙ ሲሆን፤ ሀገራቱ አሁንም የዓባይ ተፋሰስ እንዲለማ ድጋፍ ማድረግ እንዳለባቸው አብራርተዋል፡፡
ኢትዮጵያ ውስጥ ውሃ ሲጨምር ሌሎች ሀገራት ላይ መጨመሩ የግድ መሆኑን የገለጹት ኢንጂነር ጥላሁን ኤርዲኖ፤ ህዳሴ በትነት የሚባክነውን ውሃ የሚቀንስ በመሆኑ በድርቅ ጊዜ ለቀጠናው ከፍተኛ እፎይታ የሚፈጥር ነው ብለዋል፡፡

Published in
ዜና
Tagged under
Tuesday, 09 September 2025 06:59
የረዳን ፈጣሪ አምላክ ይመስገን !!
መላዉ ኢትዮዽያዊን በሙሉ እንኳን ደስ አለን!!
የፅናታቻን ፣ የላባችን ፣ የደማችን ፣ የጥረታችን ዉጤት ፣ የዘመናት ቁጭታችን መደምደሚያ ፣ የብልፅግናችን መሰረት ፣ የአይበገሬነታችን ምልክት ለሆነዉ የታላቁ ህዳሴ ግድባችን ምረቃ እንኳን አደረሰን!!
ባንድነት ስንቆምና ስንተባበር የማችለዉም የለም !!
ፈጣሪ ኢትዮዽያና ህዝቦቿን ይባርክ
-ከንቲባ አዳነች አቤቤ-
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…


Published in
ዜና
Tagged under
Tuesday, 09 September 2025 06:58
የህዳሴ ዋዜማ በድሮኖችና በጀልባዎች ትርኢት
የህዳሴ ዋዜማ በእግር ጉዞ፣ በድሮንና በጀልባዎች ትርኢት፣ በባሎንና በሰርከስ ሥራዎች ተጀምሮ እየተካሄደ ነው።
የታላቁ ህዳሴ ግድብ የምረቃ የዋዜማ ዝግጅት በዚያው በጉባ እየተካሄደ ይገኛል።
በምረቃ ዋዜማ ዝግጅቱ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን ጨምሮ፣ ቀዳማዊ እመቤት ዝናሽ ታያቸው፣ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ፣ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ እንዲሁም ሌሎች የመንግስት የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።
በግድቡ መመረቂያ ዋዜማ ላይ የድሮኖች ትርኢት፣ የተለያዩ የሰርከስ፣ የመብራትና የጀልባ ትርኢቶች እየተካሄዱ ነው።
ቀደም ሲልም በግድቡ አናት ላይ የ1 ነጥብ 8 ኪሎ ሜትር የእግር ጉዞ መደረጉም ተዘግቧል፡፡
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…





Published in
ዜና
Tagged under

