Administrator

Administrator

ከ100 ሺ በላይ ጎብኝዎች የሚታደሙበት ሃይል ቁጠባ አረንጓዴ አፍሪካ የተሰኘ የኤሌክትሪሲቲ ኤግዚብሽን ሊካሄድ ነው።
3A ኤቨንትስ ኃ/የተ/የግ/ማህበር ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪካል መሃንዲሶች ማህበር ጋር በመተባበር  " ሃይል ቁጠባ አረንጓዴ አፍሪካ " በሚል መሪ ቃል 4ኛውን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪሲቲ ኤግዚብሽን ከየካቲት 13 እስከ የካቲት 16/2016 ዓ.ም ድረስ በታላቅ ድምቀት በሚልንየም አዳራሽ ለማካሄድ በዛሬው ዕለት በሰጡት መግለጫ አስታወቁ።
በተጨማሪም የኢትዮጵያ ኤልክትሪካል መሃንዲሶች ማሀበር 25ኛ አመቱን በታላቅ ድምቀት ያከብራል ተብሏል።
በኤግዚቢሽኑ ከ 300 በላይ የሚሆኑ በሃገር ውስጥ ያሉና ከውጭ የሚመጡ በኤሌክትሪሲቲ ዘርፍ
፣ላይ የተሰማሩ አምራቾች አስመጪዎችና አቅራቢዎች  ከ100,000 በላይ የሚሆኑ ጎብኚዎች የሚሳተፉ ሲሆን በዝግጅቱ ላይ የተለያዩ ሲምፖዚየሞች፣ ሴሚናሮች እና ጥናታዊ ፅሁፎች ይቀርቡበታል ተብሏል።
የ3A ኢቨንትስ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ አብዱልፈታህ  አሊ እንደገለጹት በኤግዚቢሽኑ ላይ የሚሳተፉ ድርጅቶች ምርትና አገልግሎታቸውን የሚያስተዋውቁበት የሚያሳዩበት፣ በዘርፉ የካበተ ልምድ ያላቸውን መንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን በማግኘት  የልምድ ልውውጥ ለማድረግ፤ ለቀጣይ ስራ አጋርነት ለመፍጠር እንደሚያስችል እና እንደሚረዳ ገልጸዋል።


ከ100 ሺ በላይ ጎብኝዎች የሚታደሙበት ሃይል ቁጠባ አረንጓዴ አፍሪካ የተሰኘ የኤሌክትሪሲቲ ኤግዚብሽን ሊካሄድ ነው።
3A ኤቨንትስ ኃ/የተ/የግ/ማህበር ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪካል መሃንዲሶች ማህበር ጋር በመተባበር  " ሃይል ቁጠባ አረንጓዴ አፍሪካ " በሚል መሪ ቃል 4ኛውን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪሲቲ ኤግዚብሽን ከየካቲት 13 እስከ የካቲት 16/2016 ዓ.ም ድረስ በታላቅ ድምቀት በሚልንየም አዳራሽ ለማካሄድ በዛሬው ዕለት በሰጡት መግለጫ አስታወቁ።
በተጨማሪም የኢትዮጵያ ኤልክትሪካል መሃንዲሶች ማሀበር 25ኛ አመቱን በታላቅ ድምቀት ያከብራል ተብሏል።
በኤግዚቢሽኑ ከ 300 በላይ የሚሆኑ በሃገር ውስጥ ያሉና ከውጭ የሚመጡ በኤሌክትሪሲቲ ዘርፍ
፣ላይ የተሰማሩ አምራቾች አስመጪዎችና አቅራቢዎች  ከ100,000 በላይ የሚሆኑ ጎብኚዎች የሚሳተፉ ሲሆን በዝግጅቱ ላይ የተለያዩ ሲምፖዚየሞች፣ ሴሚናሮች እና ጥናታዊ ፅሁፎች ይቀርቡበታል ተብሏል።
የ3A ኢቨንትስ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ አብዱልፈታህ  አሊ እንደገለጹት በኤግዚቢሽኑ ላይ የሚሳተፉ ድርጅቶች ምርትና አገልግሎታቸውን የሚያስተዋውቁበት የሚያሳዩበት፣ በዘርፉ የካበተ ልምድ ያላቸውን መንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን በማግኘት  የልምድ ልውውጥ ለማድረግ፤ ለቀጣይ ስራ አጋርነት ለመፍጠር እንደሚያስችል እና እንደሚረዳ ገልጸዋል።


ይህን ያውቁ ኖሯል.....?

በአድዋ ተራራዎች ላይ የአንባገነኑ መሪ የቤኒቶ ሙሶሊኒ የፊት ቅርፅ ሐውልት ቆሞ እንደነበር......

በ 2ተኛ የኢጣሊያን ወረራ ዘመን በአድዋ በሱሎዳ ተራራ ፊት ለፊት ላይ በፋሺስት ወታደሮች የተገነባው ይህ ሃውልት ቁመቱ 4.80 ሜትር ከፍታ የነበረው ሲሆን ፤ የጣሊያን ወታደሮች በወቅቱ የዚህ ሐውልት በቦታው የመገንባታቸው ዋንኛው ዓላማ እና ለማስተላለፍ የፈለጉት መልዕክት:-

➻ በ 1888 ዓ.ም ላይ የደረሰባቸውን ሽንፈት በውስጣቸው ለነበረው ቁጭት እና እፍረት ማካካሻ ይሆናል ብለው በማሰብ እንዲሁም በሃጉረ አፍሪካ ለነበሩት ለሌሎቹ የቀኝ ገዢዎች የአውሮፓውያን ሃገራት የጠንካራነት ማሳያ የሞራል ማበረታቻ ምልክት ይሆናል በማለት ነበር ከ 40 ዓመት በፊት ሽንፈታቸው ከተጎነጩባት ቦታ ላይ በወርሃ የካቲት 1928 ዓ.ም ላይ ገንብተው ያቆሙት።

ሆኖም ግን አሁን ሐውልቱ በቦታው የለም ሀገራችን ከፋሺስት ጣሊያን ነፃ ከሆነች በኋላ በቦታው ምንም አይነት የሐውልቱ አሻራ እና ፍርስራሽ እንዳይኖር ተደርጎ ሊፈረስ ችሏል።

ክብርና ሞገስ ከወራሪ ነፃ ሀገር ላስረከቡን ጀግኖች አርበኞቻችን

ይህን ያውቁ ኖሯል.....?

በአድዋ ተራራዎች ላይ የአንባገነኑ መሪ የቤኒቶ ሙሶሊኒ የፊት ቅርፅ ሐውልት ቆሞ እንደነበር......

በ 2ተኛ የኢጣሊያን ወረራ ዘመን በአድዋ በሱሎዳ ተራራ ፊት ለፊት ላይ በፋሺስት ወታደሮች የተገነባው ይህ ሃውልት ቁመቱ 4.80 ሜትር ከፍታ የነበረው ሲሆን ፤ የጣሊያን ወታደሮች በወቅቱ የዚህ ሐውልት በቦታው የመገንባታቸው ዋንኛው ዓላማ እና ለማስተላለፍ የፈለጉት መልዕክት:-

➻ በ 1888 ዓ.ም ላይ የደረሰባቸውን ሽንፈት በውስጣቸው ለነበረው ቁጭት እና እፍረት ማካካሻ ይሆናል ብለው በማሰብ እንዲሁም በሃጉረ አፍሪካ ለነበሩት ለሌሎቹ የቀኝ ገዢዎች የአውሮፓውያን ሃገራት የጠንካራነት ማሳያ የሞራል ማበረታቻ ምልክት ይሆናል በማለት ነበር ከ 40 ዓመት በፊት ሽንፈታቸው ከተጎነጩባት ቦታ ላይ በወርሃ የካቲት 1928 ዓ.ም ላይ ገንብተው ያቆሙት።

ሆኖም ግን አሁን ሐውልቱ በቦታው የለም ሀገራችን ከፋሺስት ጣሊያን ነፃ ከሆነች በኋላ በቦታው ምንም አይነት የሐውልቱ አሻራ እና ፍርስራሽ እንዳይኖር ተደርጎ ሊፈረስ ችሏል።

ክብርና ሞገስ ከወራሪ ነፃ ሀገር ላስረከቡን ጀግኖች አርበኞቻችን

ከካንሰር ህመም ሁሉ በብዛት የጡት ካንሰር በአንደኛነት ደረጃ የሚታይ በሽታ ነው:: ገዳይነቱም አያጠያይቅም ምክንያቱም የጡት ካንሰር በሴቶች ላይ ለሚከሰቱት የካንሰር ሞት መንስኤ ከሳንባ ካንሰር ቀጥሎ ሁለተኛው ነው።

ማሞግራም የጡት ኤክስሬይ ምስል ነው። ዶክተሮች የጡት ካንሰር የመጀመሪያ ምልክቶችን ለመፈለግ ማሞግራም ይጠቀማሉ። መደበኛ ማሞግራም ዶክተሮች የጡት ካንሰርን ቀድመው ለማግኘት የሚደረግ ምርመራ ነው፣ አንዳንዴም እስከ ሶስት አመት ድረስ አስቀድሞ የጡት ካንሰርን ለማወቅ ያስችላል::

በምርመራው ወቅት በምስሉ ላይ እንደሚታየው ባለሙያው ጡትዎን በሁለት የፕላስቲክ ሳህን መሀል ያስቀምጣል. ሳህኖቹ ኤክስሬይ በሚወሰድበት ጊዜ ጡቱን ጠፍጣፋ ያደርጋሉ እናም አንዳንድ ጫናዎች እና ህመሞች ይሰማዎታል::

የጫናው ህመም መጠን በተወሰነ መልኩም ቢሆን ስለሚጨምር ይህን ምርመራ በወር አበበ ስዓት ማድረግ አይመከረጠርም:: በተጨማሪም ዲኦድራንት ወይም ሽቶ የመሳሰሉትን  ምርቶች መጠቀም በኤክስሬይ ላይ እንደ ነጭ ነጠብጣቦች በመፍጠር የምርመራውን ተዓማኒነት ስለሚቀንሱ አይመከሩም።

በእድሜ ከ40 በላይ የሆኑ ሴቶች በ1-2 አመት ልዩነት የማሞግራም ምርመራ ማድርግ ይኖርባቸዋል:: ማሞግራም ዋነኛ የቅድመ ካንሰር ምርመራ ቢሆንም ሌሎች አማራጮም መኖራቸውን መዘንጋት የለበትም:: በዳበሳ የሚደረግ የቅድመ ካንሰር ምርመራ በሀኪም ዘንድ ቀርቦ ወይም በ'ራስ በመዳበስ ገና እየጀመረ ያለ እጢ ማግኘት ሌላኛው አማራጭ ነው:: ልዩነቱ ማሞግራፊ በእጅ ላይ ለመሰማት በጣም ትንሽ የሆኑ እጢዎችን ሊያገኝ ይችላል። ይህም ማሞግራፊን ተመራጭና ተዓማኒ ያደርገዋል:: እድሜ ከ40 በታች ከሆነ የጡት አልትራሳውንድም 3ኛው አማራጭ ነው::

ታሞ ከመማቀቅ አስቀድሞ መጠንቀቅ ነውና ነገሩ ይህን የማሞግራፊ ምርመራ ማድርግ አስፈጊ ነው:: በኢትዮጵያ ቢያንስ በአዲስ አበባ ደረጃ የአገልግሎቱን ሁኔታ ለመግለፅ የክል በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ደረጃ  ክፍያው 360ብር ነው::

ይህ ምርመራ በተጨማሪም በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል እና በተለያዩ የግል ተቋማት ይሰጣል:: በእንሹራንስ በኩልም ምርመራውን በነፃ ማድረግ ይቻላል:: በአረብ ሀገር ያላቹ እህቶቼም በአቅራቢያ በሚገኝ የህክምና መእከል በመቅርብ ምርመራውን ማድርግ ጠቀሜታው የጎላ ነው::

Dr. Zerihun  Gelashe  Hailu

ከካንሰር ህመም ሁሉ በብዛት የጡት ካንሰር በአንደኛነት ደረጃ የሚታይ በሽታ ነው:: ገዳይነቱም አያጠያይቅም ምክንያቱም የጡት ካንሰር በሴቶች ላይ ለሚከሰቱት የካንሰር ሞት መንስኤ ከሳንባ ካንሰር ቀጥሎ ሁለተኛው ነው።

ማሞግራም የጡት ኤክስሬይ ምስል ነው። ዶክተሮች የጡት ካንሰር የመጀመሪያ ምልክቶችን ለመፈለግ ማሞግራም ይጠቀማሉ። መደበኛ ማሞግራም ዶክተሮች የጡት ካንሰርን ቀድመው ለማግኘት የሚደረግ ምርመራ ነው፣ አንዳንዴም እስከ ሶስት አመት ድረስ አስቀድሞ የጡት ካንሰርን ለማወቅ ያስችላል::

በምርመራው ወቅት በምስሉ ላይ እንደሚታየው ባለሙያው ጡትዎን በሁለት የፕላስቲክ ሳህን መሀል ያስቀምጣል. ሳህኖቹ ኤክስሬይ በሚወሰድበት ጊዜ ጡቱን ጠፍጣፋ ያደርጋሉ እናም አንዳንድ ጫናዎች እና ህመሞች ይሰማዎታል::

የጫናው ህመም መጠን በተወሰነ መልኩም ቢሆን ስለሚጨምር ይህን ምርመራ በወር አበበ ስዓት ማድረግ አይመከረጠርም:: በተጨማሪም ዲኦድራንት ወይም ሽቶ የመሳሰሉትን  ምርቶች መጠቀም በኤክስሬይ ላይ እንደ ነጭ ነጠብጣቦች በመፍጠር የምርመራውን ተዓማኒነት ስለሚቀንሱ አይመከሩም።

በእድሜ ከ40 በላይ የሆኑ ሴቶች በ1-2 አመት ልዩነት የማሞግራም ምርመራ ማድርግ ይኖርባቸዋል:: ማሞግራም ዋነኛ የቅድመ ካንሰር ምርመራ ቢሆንም ሌሎች አማራጮም መኖራቸውን መዘንጋት የለበትም:: በዳበሳ የሚደረግ የቅድመ ካንሰር ምርመራ በሀኪም ዘንድ ቀርቦ ወይም በ'ራስ በመዳበስ ገና እየጀመረ ያለ እጢ ማግኘት ሌላኛው አማራጭ ነው:: ልዩነቱ ማሞግራፊ በእጅ ላይ ለመሰማት በጣም ትንሽ የሆኑ እጢዎችን ሊያገኝ ይችላል። ይህም ማሞግራፊን ተመራጭና ተዓማኒ ያደርገዋል:: እድሜ ከ40 በታች ከሆነ የጡት አልትራሳውንድም 3ኛው አማራጭ ነው::

ታሞ ከመማቀቅ አስቀድሞ መጠንቀቅ ነውና ነገሩ ይህን የማሞግራፊ ምርመራ ማድርግ አስፈጊ ነው:: በኢትዮጵያ ቢያንስ በአዲስ አበባ ደረጃ የአገልግሎቱን ሁኔታ ለመግለፅ የክል በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ደረጃ  ክፍያው 360ብር ነው::

ይህ ምርመራ በተጨማሪም በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል እና በተለያዩ የግል ተቋማት ይሰጣል:: በእንሹራንስ በኩልም ምርመራውን በነፃ ማድረግ ይቻላል:: በአረብ ሀገር ያላቹ እህቶቼም በአቅራቢያ በሚገኝ የህክምና መእከል በመቅርብ ምርመራውን ማድርግ ጠቀሜታው የጎላ ነው::

Dr. Zerihun  Gelashe  Hailu

የፍትሕ ሚኒስቴር የሙስና ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ ሕግ አቶ አብነትገ/መስቀል እና 3 የመሬት አስተዳደር ሰራተኞችን ጨምሮ በአምስት ግለሰቦች ላይ የሙስና ወንጀል ክስ መስርቷል።
 
አቶ አብነት ገ/መስቀል በቂርቆስ ክ/ከ ወረዳ 2 የሚገኘውን ከሼክ አላሙዲን መሀመድ ጋር የጋራ ንብረታቸው የሆነውን የ1 ሺህ 971 ካሬ ሜትር ይዞታ በ83 ሚሊየን ብር በመሸጥ ለግል ጥቅም አውለዋል በሚል በተጠረጠሩበት ወንጀል በጊዜ ቀጠሮ ችሎት ሲቀርቡ እንደነበር አና ዐቃቤ ሕግ ከፌዴራል ፖሊስ የተረከበውን የምርመራ መዝገቡን ተመልክቶ ክስ ለመመስረት የ15 ቀን ይሰጠኝ ብሎ መጠየቁን ተከትሎ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት ክስ የመመስረቻ ጊዜውን ለዐቃቤ ሕግ መፍቀዱን መዘገባችን ይታወሳል።
 
ይሁንና ዐቃቤ ሕግ ከተፈቀደለት የክስ መመስረቻ ጊዜ አስቀድሞ ዛሬ አቶ አብነትን ጨምሮ በአምስት ግለሰቦች ላይ የሙስና ወንጀል ክስ መስርቷል።
ክሱ የቀረበለት የፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ክሱን ለመመልከት ለፊታችን ዓርብ ቀጠሮ ይዟል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ አቶ አብነት ገ/መስቀል ባሳለፍነው 2015 ዓ.ም በ2 ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት የቦሌ ታወር ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ጅምር ግንባታ ያለበት 3 ሺህ 383 ካሬ ሜትር ይዞታን ያለአግባብ ባለመብት በመሆን ይዞታው ላይ ካርታ በማውጣት ከ321 ሚሊየን ብር በላይ እንዲሸጥ አድርገዋል ተብለው ከሌሎች ከመሬት አስተዳደር ሰራተኞች ጋር ተከሰው ነበር።
 
ይሁንና በአቶ አብነት ላይ ቀርበውባቸው ከነበሩ ሶስት ክሶች መካከል ሁለቱ ክሶች በችሎቱ ዳኛ ከአንድ ሳምንት በፊት እንዲቋረጡ ተደርገዋል።
(ኤፍ ቢ ሲ)
የፍትሕ ሚኒስቴር የሙስና ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ ሕግ አቶ አብነትገ/መስቀል እና 3 የመሬት አስተዳደር ሰራተኞችን ጨምሮ በአምስት ግለሰቦች ላይ የሙስና ወንጀል ክስ መስርቷል።
 
አቶ አብነት ገ/መስቀል በቂርቆስ ክ/ከ ወረዳ 2 የሚገኘውን ከሼክ አላሙዲን መሀመድ ጋር የጋራ ንብረታቸው የሆነውን የ1 ሺህ 971 ካሬ ሜትር ይዞታ በ83 ሚሊየን ብር በመሸጥ ለግል ጥቅም አውለዋል በሚል በተጠረጠሩበት ወንጀል በጊዜ ቀጠሮ ችሎት ሲቀርቡ እንደነበር አና ዐቃቤ ሕግ ከፌዴራል ፖሊስ የተረከበውን የምርመራ መዝገቡን ተመልክቶ ክስ ለመመስረት የ15 ቀን ይሰጠኝ ብሎ መጠየቁን ተከትሎ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት ክስ የመመስረቻ ጊዜውን ለዐቃቤ ሕግ መፍቀዱን መዘገባችን ይታወሳል።
 
ይሁንና ዐቃቤ ሕግ ከተፈቀደለት የክስ መመስረቻ ጊዜ አስቀድሞ ዛሬ አቶ አብነትን ጨምሮ በአምስት ግለሰቦች ላይ የሙስና ወንጀል ክስ መስርቷል።
ክሱ የቀረበለት የፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ክሱን ለመመልከት ለፊታችን ዓርብ ቀጠሮ ይዟል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ አቶ አብነት ገ/መስቀል ባሳለፍነው 2015 ዓ.ም በ2 ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት የቦሌ ታወር ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ጅምር ግንባታ ያለበት 3 ሺህ 383 ካሬ ሜትር ይዞታን ያለአግባብ ባለመብት በመሆን ይዞታው ላይ ካርታ በማውጣት ከ321 ሚሊየን ብር በላይ እንዲሸጥ አድርገዋል ተብለው ከሌሎች ከመሬት አስተዳደር ሰራተኞች ጋር ተከሰው ነበር።
 
ይሁንና በአቶ አብነት ላይ ቀርበውባቸው ከነበሩ ሶስት ክሶች መካከል ሁለቱ ክሶች በችሎቱ ዳኛ ከአንድ ሳምንት በፊት እንዲቋረጡ ተደርገዋል።
(ኤፍ ቢ ሲ)

የውጭ ሀገር ገንዘቦችን በማተም እና የተለያዩ ማዕድኖችን በመያዝ ወንጀል የተከሰሱት የፀሐይ ሪል ስቴት ጀነራል ማናጀርን ጨምሮ 9 የውጭ ሀገር ዜጎች ያቀረቡት የዋስትና ጥያቄ ውድቅ ተደረገ።

ፍርድ ቤቱ የተከሳሾቹን የዋስትና ጥያቄና የዐቃቤ ሕግ የመቃወሚያ ክርክሮችን መርምሮ የዋስትና ጥያቄያቸውን ውድቅ ያደረገው።

የዋስትና ጥያቄያቸውን ውድቅ ያደረገው የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ልደታ ምድብ 8ኛ የገቢዎችና ጉሙሩክ ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ነው።

በቀረበባቸው ተደራራቢ ክስ ላይ የዋስትና ጥያቄያቸው ውድቅ ከተደረገባቸው ተከሳሾች መካከል የፀሐይ የሪል ስቴት መስራች፣ ባለድርሻ እና ስራ አስኪያጅ ቺያን ኩዊን ጨምሮ ዘጠኝ የውጭ ሀገር ዜጋ የሆኑ ተከሳሾች ናቸው።

የፍትህ ሚኒስቴር የኢኮኖሚ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ ሕግ በተከሳሾቹ ላይ የወንጀል ተሳትፎ ጠቅሶ ተደራራቢ ሰባት ክሶችን በየድርሻቸው አቅርቦባቸው ነበር።

በተለይም ባቀረበው በ1ኛ ክስ ላይ ከአንደኛ እስከ ስድስተኛ ተከሳሾች ላይ ብቻ በቀረበው ክስ ላይ እንደተመላከተው የወንጀል ህግ አንቀፅ 32 ንዑስ ቁጥር 1/ሀ እና አንቀጽ 356 ላይ የተደነገገውን በመተላለፍ ተከሳሾቹ ፀሀይ ሪል ስቴት ኃ/የተ/የግ/ማህበር ውስጥ 11ኛ ፎቅ ላይ በሚገኘው ቤት ውስጥ ከነሃሴ 24 ቀን 2015 ዓ. ም እስከ ጳጉሜ 1 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ ሀሰተኛ ገንዘብ ለመስራት የሚያገለግሉ መሳሪያዎች፣ የተለያዩ ኬሚካሎች እና ወረቀቶች በመጠቀም ሀሰተኛ የአሜሪካ ዶላር፣ ዩሮ፣ የእንግሊዝ ፓውንድ፣ የቻይና ይዋን እና የሌሎች የተለያዩ ሀገራት ገንዘቦችን አመሳስለው በማተም ላይ እያሉ እጅ ከፍንጅ ተይዘዋል የሚል ክስ ቀርቧል።

በሁለተኛው ክስ ደግሞ የወንጀል ህጉ አንቀፅ 32/ንዑስ ቁጥር 1/ሀ እናአንቀጽ 371 ንዑስ ቁጥር 2 ላይ የተደነገገውን በመተላለፍ፣ በሚኖሩበት ቤት ውስጥ ገንዘቦች ለመስራት የሚያገለግሉ፣ 2 የብር ማተሚያ ማሽን እና የተለያዩ ኬሚካሎች ማለትም በጀሪካን፣ በጠርሙስ፣ በብልቃጥ እና በበርሜል ባለ 500 ኖት ሀሰተኛ ዩሮ ለመስራት የተዘጋጀ 60 ሚሊየን 750 ሺህ ብር የሚገመት ነጭ ወረቀት ብዛት በነጠላ 121 ሺህ 500 ዩሮ እና 42 ሚሊየን 400 ሺህ ዶላር የሚገመት ሀሰተኛ ዶላር ለመስራት የተዘጋጀ ባለ 100 ኖት 424 ሺህ አረንጓዴ ወረቀት የተገኘባቸው መሆኑን ዐቃቤ ህግ ጠቅሷል።

በተጨማሪም 16 ሚሊየን 150 ሺህ የሚገመት ነጭ የዶላር ወረቀት፣ የተለያየ ነጭ ዱቄት፣ አንዱ እሽግ በውስጡ 500 ወረቀት የያዘ 32 እሽግ በብር ቅርፅ የተቆራረጡ ወረቀቶች፣ በአልሙንየም የተጠቀለለ በገንዘብ ቅርፅ የተቆረጠ ጥቁር ቀለም ያለው ወረቀት፣ 28 እሽግ አንዱ 500 የያዘ የገንዘብ መስሪያ ወረቀት፣ እንዲሁም ገንዘብ ለመስራት የሚያገለግሉ መስሪያና መሳርያዎች ይዘው በፀጥታ አካላት በተደረገ ክትትል ይዘውት የተገኙ መሆኑን ዐቃቤ ሕግ ጠቅሶ ሀሰተኛ ነገሮችን ለመስራት የሚያገለግሉ መስሪያ እና መሳሪያዎች መያዝ ወንጀል ክስ አቅርቦባቸዋል።

3ኛ ክስ ደግሞ በ1ኛ ተከሳሸ ላይ ብቻ የቀረበ ሲሆን÷ በዚህም የወንጀል ህግ አንቀፅ 359 ስር የተደነገገውን በመተላለፍ በጳጉሜን 1 ቀን 2015 ዓ.ም በተደረገው ፍተሻ ሀሰተኛ የሆኑ ባለ 100 የገንዘብ ብዛቱ 297 ሺህ 400 የአሜሪካ ዶላር፣ ባለ 50 የገንዘብ ብዛቱ 36 ሺህ 250 የእንግሊዝ ፓውንድ፣ ባለ 500 ዩሮ 62 ሺህ የሆነ፣ እና ባለ 200፣ 650 ሺህ 600 ዩሮ፣ እንዲሁም ባለ 1 ሺህ 567 የቻይና ዩዋን ይዞ የተገኘ መሆኑ ተጠቅሶ ተከሳሹ ላይ ሀሰተኛ ገንዘብ ይዞ መገኘት ወንጀል ክስ ቀርቧል።

በሌላ በኩል በአንደኛ ተከሳሽ ላይ በሌላኛው በቀረበበት 5ኛ ክስ ላይ ደግሞ ተከሳሹ ማዕድን የመያዝ ፍቃድ ሳይኖረው ክብደቱ 108 ነጥብ 43 እና 51 ነጥብ 88 ግራም የሚመዝን ኦፓል የተፈጥሮ ማዕድን እና 4 ነጥብ 99 ግራም የሚመዝን ኳርትዝ እንዲሁም 77 ነጥብ 71 ግራም የሚመዝን አጌት የተፈጠሮ ማዕድን እና 104 ነጥብ 59 ግራም የሚመዝን ማግኔታይት የተፈጥሮ ማዕድን ይዞ የተገኘ መሆኑ በክሱ ተጠቅሶ ፍቃድ ሳይኖረው የተፈጥሮ ማዕድን መያዝ እና የአዋጁን ድንጋጌዎች መተላለፍ ወንጀል ክስ መቅረቡ ይታወሳል።

በተለይም አንደኛ ተከሳሽ በኮንትሮባንድ ወንጀል ክስ የቀረበበት ሲሆን÷ ሌሎቹ ማለትም ከ2ኛ እስከ 9ኛ ተራ ቁጥር የተጠቀሱት ተከሳሾች ላይ ደግሞ የፀና የመኖሪያ ፍቃድ ሳይኖር በሀገር ውስጥ መኖር ወንጀል ክስ ቀርቧል።፡

በአጠቃላይ ተከሳሾቹ ላይ የቀረበባቸው ተደራራቢ የወንጀል ክስን በችሎት እንዲደርሳቸው ተደርጓል ማንነታቸውም ተረጋግጧል።

ከ1 እስከ 6 ኛተራ ቁጥር የተጠቀሱ ተከሳሽ ጠበቆች የአንደኛ ተከሳሽ የልብ ህመምተኛ መሆናቸውንና ቋሚ አድራሻ እንዳላቸው ጠቅሰው የዋስትና መብት እንዲፈቀድ ጠይቀዋል ነበር።

በተጨማሪም ከ2 እስከ 6ኛ ተራ ቁጥር የተጠቀሱት ደንበኞቻቸውን በሚመለከት የቀረበባቸው ክስ ከ7 ዓመት በላይ የማያስቀጣ የወንጀል ድንጋጌ መከሰሳቸውን ጠቅሰው የዋስትና መብት ጥያቄ አንስተዋል።

በዐቃቤ ሕግ በኩል ደግሞ ተከሳሾቹ ከተከሰሱበት ተደራራቢ ክስ የቀረበባቸው እና ቋሚ አድራሻ የሌላቸው ከመሆኑ አንጻር ቢወጡ የዋስትና ግዴታቸውን አክብረው ሊቀርቡ አይችሉም ሲል በመቃወም ተከራክሯል።

የሰበር ሰሚ ችሎት ተደራራቢ ክሶችን በሚመለከት በልዩነት ዋስትናን ሊያስከለክል ስለሚችል ድንጋጌዎች በማብራራት በመከራከር ተጠርጣሪዎቹ ማረሚያ ቤት እንዲወርዱ ጠይቋል።

ሌሎቹ ከ7ኛ እስከ9ኛ ተራ ቁጥር የተከሰሱ በኤሌክትሪክ ባለሙያ እና ሁለት እግር ኳስ ተጫዋች ነን ያሉ የላይቤሪያና የጊኒ ዜግነት ያላቸው ተከሳሾችን በሚመለከት በችሎት የተገኙ ጠበቃ ድጋፍ ለማድረግ በማስፈቀድ ተከሳሹ በቱሪስት ቪዛ ሀገር ውስጥ በገቡ በሁለት ሳምንታቸው በፀሐይ ሪል ስቴት በሄዱበት መያዛቸውን ጠቅሶ ቪዛና ፓስፖርት ያላቸው መሆናቸውን በማመላከት ከሀገር እንዳይወጡ እግድ ተጥሎ የዋስትና መብታቸው እንዲከበር ጥያቄ ቀርቦ ክርክር ተደርጎበት ነበር።

የግራ ቀኙን ክርክር የመረመረው ችሎቱ ተከሳሾቹ ላይ የቀረበው ተደራራቢ ከባድ ወንጀል መሆኑን ተከትሎ ቢወጡ ተመሳሳይ ድርጊት ላይ ሊሳተፉና ቋሚ አድራሻ ስለሌላቸው የዋስትና ግዴታቸውን አክብረው ላይቀርቡ ይችላሉ የሚለውን ግምት በመያዝና እንዲሁም ዋስትና ሊገደብ የሚችሉባቸው የሰበር ሰሚ ችሎት ያስቀመጣቸው የድንጋጌ ነጥቦች በምክንያትነት በመጥቀስ የተከሳሾቹን ዋስትና ጥያቄ አለመቀበሉን አብራርቷል።

የዋስትና ጥያቄያቸው ውድቅ የተደረገባቸው ተከሳሾች ጉዳያቸውን በማረሚያ ቤት ሆነው እንዲከታተሉ በማለት ከቀጠሮ በፊት የሚቀርብ የክስ መቃወሚያ አስተያየትና የዐቃቤ ሕግ መልስን መርምሮ ብይን ለመስጠት ለህዳር 4 ቀን 2016 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።

ኤፍ ቢ ሲ

  አንድ ንጉሥ ወደ አደንም ሲሄድ፣ ወደ አደባባይም ሲወጣ፣ ወደ ዙፋን ችሎትም ብቅ ሲል፣ ወደ ጦር ሜዳም ሲጓዝ እንደ ቀኝ እጁ የሚያየውና  እንደ ሰው አክብሮ የሚያኖረው አንድ ፈረስ ነበረው። ይህ ፈረስ በንግሥና ዘመኑ ያልተለየውና ፍፁም ባለውለታው ነበር። ስለዚህም ምን ላድርግለት ብሎ ሌት-ተቀን ሲያስብ ቆይቶ በመጨረሻ አንደ ሀሳብ አገኘ። ይህ ፈረስ ቋንቋ ቢማር እንደልብ ሊያጫውተውና ሊያናግረው እንደሚችል ታየው። ንጉሡ የሚጠላው ግን በአዋቂነቱ ምንም ዓይነት ወጥመድ ያለበት ጥያቄ ቢጠይቀው መልስ የማያጣ በመሆኑ የሚያናድደውን ሊቅ አዋቂ ምሁር አስጠርቶ እንዲህ አለው፡-


“እንደምታውቀው ይሄ ፈረሴ ባለውለታዬ ነው። በመጣምርና በመረሸት አስጊጬ፣ ገላውን በየእለቱ አሳጥቤ፣ ተገቢ የመኖሪያ ስፍራ ሰጥቼ፣ መኖሪያው እንዳይጓደል ተጠንቅቄ፣ እንደሰው አቅርቤና አክብሬ ይዤዋለሁ። ሆኖም እሱ የእኔን ንግግር ባለማወቁ፣ ቋንቋ ለቋንቋ ልንግባባ አልቻልንም። እኔ የእሱን ቋንቋ ልማር እንዳልል አንተም አስተማሪያዬ ራስህ ቋንቋውን ስለማታውቅ ማን ያስተምረኛል? ስለዚህ የሚሻለው አንተ ለፈረሴ ቋንቋ ብታስተምረው ነው። የፈለግኸውን እርዳታና የተመቻቸ ሁኔታ እንዲኖርህ  አደርግልሃለሁ። ታዲያ ይህ ኃላፊነት የዋዛ ኃላፊነት እንዳይመስልህ። በመሆኑም ከአሁን ጀምሮ እስከ አምስት ዓመት ድረስ ይህ ፈረስ ቋንቋ እንዲማር አድርግ። ያ ሳይሆን ቢቀር ግን ትገደላለህ!” አለው።


ምሁሩም፡-
“ንጉሥ ሆይ እርስዎ የፈለጉት እንዲሆን ማድረግና እርስዎን ማስደሰት ተገቢ መሆኑን አምናለሁ። እንዳሉኝም አደርጋለሁ። በአምስት ዓመት ጊዜ ውስጥ ፈረስዎ በእኛ ቋንቋ እንዲናገር አደርገዋለሁ” ሲል ቃል ገባ።
ንጉሡ በዚሁ አሰናበቱት።
ያ ሊቅ ምሁር ከንጉሡ እንደተለየ ከአንድ ብልህ ወዳጁ ጋር  ይገናኛል።  ለዚህ ወዳጁ ለንጉሡ ስለገባው ቃል አጫወተው። ወዳጁም፡-
“ሰማህ ወይ እንደዚህ ያለ እብደት እንዴት ትፈጽማለህ? ፈረስ ቋንቋ ሲማር ያየኸው የት አገር ነው? ንጉሥ አስደስታለሁ ብለህስ እንዴት አንገትህን ለሰይፍ ታመቻቻለህ? ከእንዳንተ ያለ ሊቅ  አዋቂ ይህንን አልጠብቅም” ይለዋል።
ሊቁ እንዲህ ሲል መለሰ፡-
“ወዳጄ እኔም አስቤበታለሁ። የንጉሡን ትዕዛዝ የተቀበልኩት ለምን መሰለህ? በእኛ አገር  እስከ አምስት ዓመት ድረስ የሚሆነው ምን ይታወቃል? ወይ ንጉሡ ይሞታሉ። ወይ እኔ እሞታለሁ። ወይ ፈረሱ ቋንቋ ይማር ይሆናል!”
***
በነሲብና በአቦ ሰጡኝ፣ ተስፋ በመቁረጥና ንጉሥ ለማስደሰት ብሎ ከህሊናው ውጭ የማይሆነውን ይሆናል የሚል የተማረ ዜጋ አይጣል ነው። እንዲህ ያለው ምሁር የሀገር እዳ እንጂ የሀገር መድህን አይደለም። አገራችን እንኳን የነሲብና የ”ጥንቆላ” መላምት ተጨምሮባት እንዲያውም እንዲያው ናት። የዛሬ ሃያ ዘጠኝ ዓመት ግድም አንድ ለብዙ ጊዜ ውጭ ሀገር የቆዩ ኢኮኖሚስት አዛውንት “የሀገራችን ኢኮኖሚ ሁኔታ ምን ይመስለዎታል?” ሲል አንድ ወጣት ቢጠይቃቸው፤ “አይ ልጄ እንዲያው ባጠቃላይ ይሕቺ ሀገር‘ዲካርቴ’ ገብታለች ለማለት ይቻላል።” ብለው ነበር። እውነቱን ተናግሮ የመሸበት ማደር ነው የአዛውንቱ ጨዋታ። ምሁራን በሹመት ከተደለሉ፣ ግለኝነት ካጠቃቸውና የዘለቄታውን ሳይሆን የእለት የእለቱን ብቻ የሚያዩ ከሆነ፣ “ፈረሱ ቋንቋ ይማር ይሆናል” ከማለት የተሻለ ሚና አይኖራቸውም። ተደናግረው ከማደናገር፣ በአእምሮአቸውም፣ በአካላቸውም፣ ሙስናውስጥ ተዘፍቀው፣ አሉ እየተባሉ ቢንከላወሱ፣ “አያድን ጋሻ ቂጥ ያስወጋል” እንዲሉ፣ ለሀገርም ለህዝብም ሳይበጁ መቅረታቸው ነው።


አልበርት ካሙ እንዳለው፤ “ምሁር ማለት አዕምሮው ለራሱ ዘብ የሚቆምለት ሰው ነው። መልካም ራዕይ ያላቸው ምሁራን ለሀገር ያስባሉ። ለህዝብ ይቆረቆራሉ። ይህን ለመፈጸም ከሁሉ አስቀድመው ለአካዳሚው ህብረተሰብ ሰብዕናና መብት መከበር ያስባሉ። ለሙያ ክብር ይቆማሉ። እንዲያም ቢባል ለሙያቸው ተቀዳሚነትና ህልውና ማሰብ ብቻውን አያጸድቅም። የሙያቸው ህልውና መታወቁ ዋና ጠቀሜታው በተግባር ሥራ ላይ አውለውት እራሳቸው ተጠቅመው ህብረተሰባቸውን ሲያገለግሉበት ነው። ያኔ ለሀገር የሚበጅ እሴት ይሆናሉ። ለሙያ መታመን ታላቅ ህሊናዊ ኃላፊነት ነውና በማናቸውም መንገድ ቀዳሚውና ክብሩ ጉዳይ እሱ ነው። ከዚሁ ጋር ተያይዞ ሊመጣ የሚችል ተጠቃሽ አደጋ ግን አለ- የሙያ- ተአብዮ (Intellectual Arrogance)። የሁሉ ዳኛ የሁሉ ችግር ፈቺ እኔ ነኝና አንቱ በሉኝ፤ እንደመካኒክ ሻንጣ ተሸክማችሁኝ ዙሩ። ለሁሉ ችግር እኔ ነኝ መፍቻው፤ ሁሉ ሀገር እኔ ልሂድ፤ ሁሉ ሀሳብ ከኔ ይምጣ የማለት አባዜ ሲጠናወት ደግሞ ይብስ ይጎዳል። በተደጋጋሚ የተከሰተው ዛሬም ያልጠፋ ቀንደኛ ችግራችን ነው።


ሌላው በሰራው ድንገት ብቅ ብሎ ሹመት ሽልማቱን ልቋደስ ማለቱም ሌላ ጣጣ ነው። በፖለቲካው ትግል አንፃርም ቢሆን በልባዊነትና በልባምነት የደከመው እያለ “የለውጥ አርበኛ” መሆን፣ የ”ለውጥ ሐዋርያ” መሆን፣ “አዲስ ግልብጥ” መሆን፣ “የነቃ የበቃ” ካድሬ መሆን፣ ጮማ ምሁር ነኝ ከማለት (Crean of the intelligentia) ጋር በእብሪት ሊተሳሰር ሲሞክር አደጋው የዛኑ ያህል የግለኝነት ጥንስስ እንዳለበት አመላካች ነው። “አርሶ እህል ያደረሰ መቆፈሪያ ግድግዳ ላይ ሲሻጥ፣ ግድግዳ ላይ የነበረ ማንኪያ ምግብ ላይ ይቆማል” እንደሚለው የወላይታ ተረት መሆኑ ነው።


የሀገር ጉዳይ ያገባኛል የሚል ምሁር ችግሯን መጋራት፣ መፍትሔዋን መፈለግና ማፋለግ ከሁሉም በላይ ደግሞ ሙያን ለመለገስ ንፉግ አለመሆን ይኖርበታል።  መማር አዲስ ነገርን ለመቀበልም ሆነ ለመስጠት አዕምሮን መግራት ነው። የታነጸ አዕምሮ ያለው ዜጋ ችግሮችን አስቀድሞ የመረዳት፣ መፍትሔዎችንም ፈጥኖ የመሰንዘር ብቃት ይኖረዋልና ለሀገር ጉዳይ ምሁሩ ቅርበት አለው የሚባልበት ሁነኛ ምክንያቱ ይህ ነው። እንጂ አካዳሚክ አባ-ወራነት ብቻውን የሀገሩ “ባለቤት”፣ የሕዝቡ “ጌታ” አያደርግም። የአካዳሚ መሳፍንትነት (Accadamic aristocracy) ወደ ማንአለብኝነት ስርዓት እንጂ ወደ ጤናማ ዲሞክራሲያዊ የእውቀት አምባ አያመራም። ከሁሉም በላይ ከምሁሮቻችን የሚጠበቀው ከስንዝር ወዲያ ክንድ ማሳየት ነው። የቅርቡን ዳገት ሳይሆን ከጀርባው ያለውን ገደል  ወይም ሜዳ መጠቆም  ነው። በነቢብ የሚነገረው በገቢር ምን ይሆናል ብሎ መተርጎም ነው። ሁሌም አንድ እርምጃ ቀድሞ የያዝነው መንገድ ወዴት ያደርሰናል ማለት ነው።


“የአህያ ጆሮ ቆሟል ዝናብ ይመጣል” ከሚል ግምት እንድንላቀቅ ማገዝ ነው። “ንፋስ በዛ ትልቅ ሰው ይሞታል” ከሚል መላ ምት ወጥተን ትክክለኛውን የአየር ጸባይ የመገመት፣ የህብረተሰብ ሳይንስን መሰረት ያደረገ ትንተና የመጠቀም  መላ እንድንጨብጥ ማመላከት ነው።
ለምሳሌ የዩኒቨርስቲው የወደፊት ራዕይና እጣ ፈንታ ምንድን ይሆን፣ የክልል ፖለቲካና  የሊብራሊዝም ዝምድና ከየት ወዴትስ (Cause, process and effect) ምንድን ነው፣ “ዳሩ ሲነካ መሐከሉ ዳር ይሆናል” ማለት ለስልጣነ- መንበሩ ያለው ትርጓሜ ምንድን ነው? ወዘተ የሚሉትን ሐሳቦች የሚያሳይ አብይ ትንተናና ፋና ወጊ ሐሳብ መስጠት እንጂ በትናንሽ ስልጣን ኮርቻ ዙሪያ ተቀምጦ በጉዳይ አስፈጻሚነት ከአፍንጫ ያልራቀ ወይም እስከ አፍንጫም ያልደረሰ አስተያየት ቢሰጡ፣ “ይሄ ሳር ፍለጋ ዱባ ለመስረቅ ነው” ከማሰኘቱ ሌላ  የምሁር ንፍቀ ክበብ ደንብና ወግ አይሆንም።

“ምሁር የማስጠንቀቂያ ደወል ነው” እንዲል መጽሐፉ፤ በእውቀቱ የሕብረተሰብ ቃፊርነቱን ማሳየት ይገባዋል። እንቅስቃሴ- አልባ መሆን (Non-Dinamic) ወይ በምቾት ከመስባት፣ ወይ በወሬ ከመትባትና ከመተበት አሊያም ያለውሉ ፖለቲካ ውስጥ ገብቶ ከማረጥረጥ ያለፈ ሚና አይኖረውም። ይሄው እንዳይበቃው ይህንኑ ለመሸፈን ሲል ስሜን ያስነሳል ለሚለው አንዳች ረብ- የለሽ ጉዳይ ዙሪያ አውሎ ነፋስ ማስነሳትን ስራዬ ብሎ ይያያዛል። “የመቀመጥ ብዛት የደረቀ ቁስል ያስፍቃል” ይሏል ይሄ ነው። ይሄ በሁሉ ሰፈር፣ በሁሉም ካምፕ፣ በሁሉም ጎራ፣ በመጤው፣ በፖለቲከኛው፣ በባለሙያው ዘንድ መታየቱ ጉዳዩን የበለጠ አሳሳቢ ያደርገዋል። ኋላ አቧራው መሬት ሲወርድና ንፋሱ ሲቆም ከተቀመጠበት ፎቀቅ ያላለ ምሁር መኖሩ ይፋ መሆኑ አይቀርም። ሕዝቡም እንደፈረደበት እንደዘፋኙ
“ቃልሽን ያንቆርቁረው በቀለመ-ወርቁ
እኔ አንቺን ስጠብቅ እየተኙ ነቁ”
በማለት ወቅታዊ ጥሪውን ማቅረቡን ይቀጥላል። ምሁራን ንፉግ አይሁኑ። ብዙ ጾመው ብዙ አስጹመውናልና።

Page 9 of 678