Administrator

Administrator

የማይመለሱ 4 ነገሮች፡- ከአፍ የወጣ ቃል፣ የተወረወረ ቀስት፣ ያለፈ ህይወት እና የባከነ ዕድል፡፡
የቻይናውያን አባባል
ለማቀድ መስነፍ ለመውደቅ ማቀድ ነው፡፡
የቻይናውያን አባባል
ማለም ብቻ በቂ አይደለም፤ መምታት አለብህ፡፡
የጣሊያኖች አባባል
መሬት ላይ እሾህ ከበተንክ ባዶ እግርህን አትሂድ፡፡
የጣሊያኖች አባባል
ሁልጊዜ የምትሰጥ ከሆነ ሁልጊዜ ይኖርሃል፡፡
የቻይናውያን አባባል
በአንድ እጅህ ሁለት እንቁራሪቶችን ለመያዝ አትሞክር፡፡
የቻይናውያን አባባል
የተጠበሰች ዳክዬ መብረር አትችልም፡፡
የቻይናውያን አባባል
አበቦች በያዛቸው እጅ ላይ መዓዛቸውን ይተዋሉ፡፡
የቻይናውያን አባባል
ጠብ ከፈለግህ ለጓደኛህ ገንዘብ አበድረው፡፡
የቻይናውያን አባባል
የምላስ ብዕር፣ የልብ ቀለም ውስጥ መነከር አለበት፡፡
የቻይናውያን አባባል
የአንድ ዓመት ብልጽግና ከፈለግህ እህል ዝራ፤ የ10 ዓመት ብልጽግና ከፈለግህ ዛፎች ትከል፤ የ100 ዓመት ብልጽግና ከፈለግህ ሰዎችን አልማ፡፡
የቻይናው ያን አባባል
የአንድ ሰዓት ደስታ ከፈለግህ አሸልብ፤ የአንድ ቀን ደስታ ከፈለግህ ሃብት ውረስ፤ የዕድሜ ልክ ደስታ ከፈለግህ ሰዎችን እርዳ፡፡
የቻይናውያን አባባል

ወይዘሮ ተናኘ ስዩም “የፍቅር ድንግልና” በሚል ርዕስ ፅፈው ያሳተሙት ረጅም ልብወለድ መፅሃፍ በዛሬው ዕለት ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ በአምስት ኪሎ ድህረ ምረቃ አዳራሽ ይመረቃል፡፡ በምረቃ ስነ - ስርዓቱ ላይ ደራሲ አበረ አዳሙ በመፅሃፉ ላይ ሥነ - ፅሁፋዊ ዳሰሳ ያቀርባል ተብሏል፡፡
ደራሲዋ የዕውቋ ድምፃዊት ጂጂ (እጅጋየሁ ሽባባው) እናት እንደሆኑ ታውቋል፡፡ የልቦለዱ ታሪክ ከኢጣሊያ ወረራ በፊትና በኋላ የነበረች አንዲት ወጣት ላይ የሚያጠነጥን ሲሆን የወቅቱን ባህላዊና ማህበራዊ ገፅታ ያሳያል። በ349 ገፆች የተቀነበበው “የፍቅር ድንግልና”፤ በ100 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡ 

የወጣት ፍሬዘር ዘውዴን (ቬኛ) የግጥሞችና ደብዳቤዎች ስብስብ የያዘው “የፍቅር ገፆች” የተሰኘ መድበል ካለፈው ሳምንት ጀምሮ ለንባብ በቅቷል፡፡
መፅሃፉ በ110 ገፆች 52 ግጥሞችንና 12 ደብዳቤዎችን ያካተተ ሲሆን ለአገር ውስጥ በ30 ብር፣ ለውጭ አገራት በ9.99 ዶላር እንደሚሸጥ ታውቋል፡፡

በአለማየሁ ገበየሁ የተፃፈው  “የረከሰ ፍርድ በኢትዮጵያ” የተሰኘ የአጫጭር ወጐች መፅሐፍ ለንባብ በቃ፡፡
ጭብጡን ፖለቲካዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ያደረገው መጽሐፉ፤ ታሪኮቹ በወግ መልክ  የቀረቡ ናቸው፡፡ ደራሲ አለማየሁ ገበየሁ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅትን ጨምሮ በተለያዩ ሚዲያዎች በጋዜጠኝነት መስራቱ ታውቋል፡፡
ደራሲው በእለት ማስታወሻ ደብተሩ የመዘገባቸውን አስገራሚ ሁነቶች በወግ መልክ ማቅረቡን  የጠቆመ ሲሆን መፅሃፉ በ49 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡

 ባለፈው ዓመት በአገራችን ለመጀመሪያ ጊዜ በብሔራዊ ቴአትር የተከበረው “የዓለም የቴአትር ቀን”፤ በደሴ ከተማና በኮምበልቻ እንደሚከበር በባህልና ቱሪዝም ሚ/ር የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር አስታወቀ፡፡
“ቴአትር ለማህበራዊ ለውጥ፤ ማህበራዊ ለውጥ ለቴአትር” በሚል መሪ ቃል ከዛሬ ጀምሮ ለ3 ቀናት የሚከበረውን በዓል ወሎ ዩኒቨርሲቲና የባህልና ትብብር ዳይሬክቶሬት በጋራ እንዳዘጋጁት ታውቋል፡፡
“የዓለም የቴአትር ቀን” በደሴና ኮምበልቻ በተለያዩ አዳራሾች እንደሚከበር የጠቆሙት አዘጋጆቹ፤ በየመድረኩ ቴአትሮች፣ ትውፊታዊ ድራማዎች፣ ልዩ የሙዚቃ ዝግጅቶችና ቱባ ባህልን የሚያንፀባርቁ ውዝዋዜዎች፣ የቅኔ ጉባኤ፣ መንዙማና ሌሎች ኪነ - ጥበባት ይቀርባሉ ብለዋል፡፡
“የዓለም የቴአትር ቀን” ከ1962 ዓ.ም አንስቶ በዓለም አቀፍ ደረጃ መከበር የጀመረ ሲሆን ዘንድሮ ለ53ኛ ጊዜ እንደተከበረ ተጠቁሟል፡፡

  ከ1.5 ሚ. ብር በላይ ፈጅቷል

   የጠፈር ሳይንስ ተመራማሪ የነበሩትን የሳይንቲስት ዶ/ር ቅጣው እጅጉ ህይወት የሚዳስስ የ50 ደቂቃ ዘጋቢ ፊልም በዛሬው ዕለት ከምሽቱ 12፡30 ጀምሮ በሂልተን ሆቴል ይመረቃል፡፡
“ልጃችን” የተሰኘውንና ከ1.5 ሚ. ብር በላይ ወጪ የተደረገበትን ይሄን ዘጋቢ ፊልም ሰርቶ ለማጠናቀቅ ከ2 ዓመት በላይ እንደፈጀ የዶ/ር ቅጣው እጅጉ ቤተሰቦች ጠቁመዋል፡፡ ከቦንጋ እስከ አሜሪካ ድረስ ያለውን የሳይንቲስቱን ህይወት በስፋት ይዳስሳል በተባለለት በዚህ ዘጋቢ ፊልም፤ ከዶ/ር ቅጣው ጋር ተያይዘው የሚነሱ በርካታ የተዛቡ ጉዳዮች ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል ተብሏል፡፡

የደራሲ ተስፋዬ ዘርፉ “የስደታችን ማስታወሻ” የተሰኘው መፅሃፍ በነገው ዕለት ከቀኑ 8 ሰዓት ጀምሮ ውይይት እንደሚካሄድበት ሚዩዚክ ሜይዴይ ኢትዮጵያ ገለፀ፡፡ ለውይይቱ መነሻ ሀሳብ የሚያቀርቡት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፕሬስ ኤዲተር የሆኑት አቶ ብርሃኑ ደቦጭ ሲሆኑ ውይይቱ በብሔራዊ ቤተ - መፃህፍትና ቤተ - መዛግብት ኤጀንሲ አዳራሽ እንደሚካሄድ ታውቋል፡፡ የሥነ - ፅሑፍ አፍቃሪያን በውይይቱ ላይ እንዲገኙ ሚዩዚክ ሜይዴይ ጥሪ ጋብዟል፡፡

Saturday, 06 June 2015 14:21

የፍቅር ጥግ

ፍቅር የሚያንዘፈዝፍ ደስታ ነው፡፡
ካህሊል ጂብራን
እግዚአብሄር የተሰበረ ልብ መጠገን ይችላል፡፡ ነገር ግን ስብርባሪዎቹን ሁሉ ማግኘት አለበት፡፡
ያልታወቀ ደራሲ
የትዳር ግብ ተመሳሳይ ነገር ማሰብ ሳይሆን አብሮ ማሰብ ነው፡፡
ሮበርት ሲ.ዶድስ
ሚስት ጥሩ ባል ሲኖራት ፊቷ ላይ ያስታውቃል፡፡
ገተ
አባት ለልጆቹ ማድረግ የሚችለው ትልቁ ነገር እናታቸውን መውደድ ነው፡፡
ቲዎዶር ሄስበርግ
አንዳንዴ አንድ ሰው ስናጣ መላው ዓለም ህዝብ አልባ የሆነ ይመስለናል፡፡
ላማርቲን
እግዚአብሔር የተሰበረ ልብ ላላቸው ቅርብ ነው፡፡
የአይሁዶች አባባል
ሁልጊዜ ከሚስቴ ጋር እጅ ለእጅ እንያያዛለን። ከለቀቅኋት አንድ ነገር ትገበያለች፡፡
ሄኒ ያንግማን
አብሮ መሆን ጅማሮ ነው፡፡ አብሮ መቀጠል ዕድገት ነው፡፡ አብሮ መስራት ስኬት ነው፡፡
ሔነሪ ፎርድ
በእኔ ቤት ውስጥ አለቃው እኔ ነኝ፤ የሚስቴ ሚና የውሳኔ ሰጪነት ብቻ ነው፡፡
ውዲ አለን
ትዳር ለማደግ የመጨረሻችን ምርጥ አጋጣሚ ነው፡፡
ጆሴፍ ባርዝ
ሃዘን በጊዜ ክንፍ በርሮ ይሄዳል፡፡
ዣን ዲ ላፎንቴን
አንተ በልቤ ክንፍ በርረህ ሄድክ፣ እኔን ግን ክንፍ አልባ አደረግኸኝ፡፡
ቴሪ ጉይሌሜትስ
ትዳርን ጠብቆ የሚያቆየው ሰንሰለት አይደለም፡፡ ክሮች ናቸው፡፡ ሰዎችን በአንድ ላይ ሰፍተው የሚያቆዩት በመቶዎች የሚቆጠሩ ቀጫጭን ክሮች ናቸው፡፡
ሳይሞን ሲኞሬት

Saturday, 06 June 2015 14:06

የፀሐፍት ጥግ

 አገር ተራኪዎቿን ካጣች ልጅነቷን ታጣለች፡፡
ፒተር ሃንድኬ
ከእንቅልፍ ማንቂያ ደወል ሰዓት አልፈልግም፡፡ ሃሳቦቼ ይቀሰቅሱኛል፡፡
ሬይ ብራድበሪ ደብሊው ዲ
ጥሩ የመሰለህን ነገር ለኋለኛው የመጽሐፍህ ክፍል ወይም ለሌላ መጽሐፍህ አታስቀምጠው፡፡ ሁሉንም ነገር አሁን አውጣው፡፡
አኒ ዲላርድ
ሁልጊዜ መፃፍ የምጀምረው በንፁህ ወረቀትና በቆሸሸ አዕምሮ ነው፡፡
ፓትሪክ ዴኒስ
ፀሐፍት የሚኖሩት ሁለት ጊዜ ነው፡፡
ናታሊ ጐልድበርግ
ወረቀትህን በልብህ እስትንፋሶች ሙላው፡፡
ዊሊያም ዎርድስዎርዝ
ሙሴ ዛሬ በህይወት ቢኖር ኖሮ፣ አስርቱን ትዕዛዛት ከተራራ ላይ ይዞ ይወርድና ለሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ለማሳተም መከራውን ይበላ ነበር፡፡
ያልታወቀ ደራሲ
ፀሐፊዎች የአኗኗር ዘይቤ የላቸውም፡፡ በትንሽ ክፍል ውስጥ ተቀምጠው መፃፍ ብቻ ነው፡፡
ኖርማን ሜይለር
አንድ የሆነ ሰው ካላበሸቅህ መፃፍህ ትርጉም የለውም፡፡
ኪንግስሌይ አሚስ
ጥሩ ሂስ የሚፃፍልኝ ራሴን ካጠፋሁ ብቻ ነው፡፡
ኢድዋርድ አልቢ
መጥፎ ሂስ ቁርስህን ሊያበላሽብህ ይችላል፤ ምሳህን እንዲያበላሽብህ ግን ልትፈቅድለት አይገባም፡፡
ኪንግስሌይ አሚስ
ሥነፅሁፍ ሁሉ ሃሜት ነው፡፡
ትሩማን ካፖቴ
አንድ ቀን ለመሰረቅ የሚበቃ ነገር እንደምፅፍ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡
ያልታወቀ ደራሲ
መፃፍ ቀላል ነው፡፡ ቁጭ ብለህ የደም ስርህን መክፈት ብቻ ነው፡፡
ሬድ ባርበር
ለፃፍከው ነገር ጥብቅና መቆም በህይወት የመኖርህ ምልክት ነው፡፡
ዊሊያም ዚንሰር ደብሊው ዲ

  ከዕለታት አንድ ቀን ቹዌንጌር የሚባል አንድ የቺን ልዑል ነበረ፡፡ ይህ ልዑል ቀን ጐሎበት ወደሌላ ቼንግ ወደሚባል አገር ተሰደደ፡፡ ወደ አገሩ እስኪመለስም በድህነት፤
“ካገሩ የወጣ አገሩ እስኪመለስ
ቢጭኑት አህያ ቢለጉሙት ፈረስ”
እያለ በቻይኒኛ አሳዛኝ ህይወቱን ይመራ ጀመር፡፡
አንድ ቀን በተሰደደበት አገር በቼንግ ቤተመንግሥት አጠገብ ሲያልፍ ድንገት ንጉሡ ሲወጣ ይደርሳል፡፡ ንጉሡ የዚህን ልዑል ማንነት ሳያውቅ፤
“የማን ነው ቡቱቷም! እንደነዚህ ዓይነት ሰዎች በመንገድ ላይ እንዳላይ አላልኩም?! ይሄን ጭርንቁሳም ከመንገዴ አስወግዱልኝ!” አለ፡፡
የንጉሡ ባለሟል ግን ሰውዬው ማን እንደሆነ ስለገባው፤
“ንጉሥ ሆይ! ይሄ ሰው ጊዜ ጥሎት ነው እንጂ የተከበረ ልዑል ነበር፡፡ በታላቅ አክብሮት ብንይዘው ጥሩ ይመስለኛል፡፡ ደህና ቦታ አስቀምጠንም በዐይነ - ቁራኛ ብናየው ይሻላል!” አለ፡፡
ንጉሡ ግን የዚያን ሰው ጉስቁልናና ጨብራራ ፀጉር ብቻ ነበርና የተመለከተው የቧለሟሉን ምክር ከመጤፍ ሳይቆጥር ልዑሉን ክፉኛ ሰደበው፡፡
ባለሟሉም፤ እንደገና፤
“ንጉሥ ሆይ! ግርማዊነትዎ በአክብሮት ሊይዘው ካልቻለ፣ ነገ የሚመጣውን ማናቸውንም ነገር ከወዲሁ ለመቅጨት ወይ ይሄን ሰው ማስወገድ ይኖርብዎታል!” አለና አስጠነቀቀ፡፡
ንጉሡ ግን፤
“በእንደዚህ ያለ ቆሻሻ ላይ እጄን አላሳርፍም!” ብሎ አንቋሾት ሄደ፡፡ ከጊዜ በኋላ ልዑል ወደ አገሩ ተመለሰ፡፡
ሁኔታዎች ሁሉ ተለዋወጡ፡፡ ያ ልዑል ማ ደግ እንደሆነለት፣ ማ ክፉ እንደሠራበት ያውቃል፡፡ ከሰው ሁሉ ግን ያንን ንጉሥ አልረሳውም፡፡ ስለሆነም ጦሩን ሁሉ አደራጅቶ ወደ ቼንግ ዘመተ፡፡ ስምንት ግዛቶች ያዘ፡፡ ግዛተ - መንግሥቱን አፈራረሰ፡፡ የቼንግን ንጉሥም ወደራሱ ወደ ልዑሉ አገር እንዲሰደድ አደረገ፡፡
*   *   *
ሰው ነገ ምን እንደሚሆን አይታወቅም፡፡ ዛሬ ምናምኒት አቅም የሌለው ሰው፣ ወደፊት ትልቅ ሥልጣን ያለው ሰው ሊሆን ይችላል፡፡ በህይወታችን ብዙ ነገር ልንሸከም፣ ልንረሳም እንችላለን፡፡ መናቅና መሰደብን ግን አንረሳም፡፡ ቅስም የሚያም ነገር በቶሎ ከልባችን አይወጣም፡፡ ፈረንጆች “ረዥም የማስታወስ ችሎታ ካለው እባብ ጋር አትጣላ” ይላሉ፡፡ አላስፈላጊ የሆነ ሌሎችን የማጐሳቆል ተግባር ጥቅም የለውም፡፡ ሌላው ሰው፤ ጊዜ የገፋው አንሶ እኛ ተጨምረን “የወደቀ ዛፍ ምሣር ይበዛበታል” የሚለውን ብናስዘምር የማታ ማታ፤ ለጊዜያዊ እርካታ ብለን አሁን የፈፀምነው ኋላ መዘዙ ብዙ ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ ዓለምን በተለይም አገራችንን የቂም ቀለበት መሽከርከሪያ ምህዋር አናድርጋት፡፡ አርቀን እናስብ፡፡ ሼክስፒር በሐምሌቱ፤ በፀጋዬ ገ/መድህን ብዕር ልሣን፤
“ዛሬ ለወግ ያደረግሺው፣ ወይ ለነገ ይለምድብሻል
ልማድ ፊት እንዳሳዩት ነው፣ ወይ ይጠፋል ወይ ያጠፋል”…ይለናል፡፡ እንደወግ የምናደርገውን ነገር ሁሉ እንመርምር፡፡ አንድም፤ ማታለልና ማጭበርበር የደህንነት -ማጣት፣ የሥጋት እናት ነው ይሏልና አበው፡፡ ደረጃው ይለያይ እንጂ ራስን አደጋ ላይ መጣል መሆኑን ለአፍታም አለመዘንጋት ብልህነት ነው፡፡
ለሀገራችን ፖለቲካ ብቻ ሳይሆን ለአጠቃላይ ህይወታችን፤ አንድ ተረት እጅግ ጠቃሚ ፋይዳ አለው፡፡ ይኸውም፤ “ዋናው መንገድ ቢጠፋብህ፣ መጋቢ መንገድ ፈልግ” የሚለው ነው፡፡ በሀገራችን የትግል ሂደት ውስጥ ዋናው መንገድ የጠፋበት በርካታ ጊዜ እንደነበረ የኖረና የታዘበ ሁሉ ያውቀዋል፡፡ አማራጭ መንገድ ወይም አማራጭ ዕቅድ (Plan B- እንዲሉ) የሌለው ሰው፤ ዓለም ባንድ ጊዜ የጨለመበት ይመስለዋል፡፡ “ከእንግዲህ መሄጃ መራመጃ የለም፤ ሁሉ ነገር አበቃለት” ይላል፡፡ ሌላው ቀርቶ ግን ዋናው መንገድ በዕድሳት ላይ ቢሆንስ? ብሎ እንኳ ማሰብምኮ ያባት ነው፡፡ ከሁሉ ቀዳሚው ነገር ግን ለራስ የዝግጅት ጊዜ መስጠት መሆኑን ከልብና ጥንቅቅ ባለ ሁኔታ አጢኖ መጓዝ ነው፡፡ የሚመጣውን አምስት ዓመት መንገድ  ከአሁኗ ሰዓት መጀመር ተገቢ ነው፡፡ ዋናና መጋቢ መንገዶችን በቅጡ መለየት ከአሁኑ ነው፡፡ ጊዜ የማያላላው ሰንሰለት የለም ይባላል፡፡ የለውጥ ህግ ብቻ ይቀራል እንጂ ሁሉም ነገር ይለወጣል፡፡ ስለዚህ በፅንዓት መቀጠል ይገባል፡፡ አገር በአንድ ጀንበር እንዳልተገነባች ሁሉ፣ ለውጥም በአንድ ጀንበር አይመጣም፡፡ ለውጥ አዳጊ ሂደት መሆኑን ምኔም አለመርሳት ነው፡፡ ቀና ውድድርና ፉክክር፣ የፖለቲካ ንግግርና ክርክር በማድረግ አስተሳሰብን መለወጥ የአንድ ሰሞን የቴሌቪዥን ፍጆታ አይደለም፡፡ ቻይናዎች፤
“ዕቅድህ የዓመት ከሆነ ሩዝ ዝራ፡፡
ዕቅድህ የአምስት ዓመት ከሆነ ባህርዛፍ ትከል
ዕቅድህ የዘለዓለም ከሆነ ግን ልጅህን አስተምር!”
ይላሉ፡፡ የሁልጊዜ ሥራችን ህዝብን ማስተማር መሆን አለበት፡፡ ከአሁኗ ደቂቃ ጀምሮ፡፡ በዚህ የፖለቲካ መማር ማስተማር ሂደት ውስጥ እንቅፋት አያጋጥመንም ማለት አይደለም፡፡ መስዋዕትነት የለበትም ማለት አይደለም፡፡ እንኳን የፖለቲካ መንገድ ተራውም ህይወት እንኳ በእሾክ በአረንቋ የተሞላ መሆኑን አለመዘንጋት ነው፡፡ “አገጭህን ይዞ የሚለምንህ፣ እምቢ ብትል በጥፊ ሊልህ” የሚለው ተረትም እዚህ ውስጥ እንደሚካተት አለመዘንጋት ብልህነት ነው!