Administrator

Administrator

  የግሪካዊው ደራሲ ኒኮስ ካዛንታኪስ ”The Last Temptation of Christ“ የተሰኘ ልብወለድ መጽሐፍ ”የመጨረሻው ፈተና” በሚል በማይንጌ ወደ አማርኛ ተመልሶ ሰሞኑን ለንባብ በቃ፡፡
ኒኮስ ካዛንታኪስ በ1883 ዓ.ም. (እ.ኤ.አ) በክሪት ከተማ ተወለደ፡፡ ከአቴንስ ዩኒቨርስቲ የሕግ ዲግሪውን ካገኘ በኋላ፣ በታዋቂው ፈላስፋ ሄንሪ በርግሰን ሥር የፍልስፍና ጥናቱን በፓሪስ አካሂዷል፡፡ ሥነ ጽሑፍና አርትን ደግሞ በጀርመንና ጣልያን ተዟዙሮ አጥንቷል፡፡ ስፔን፣ እንግሊዝ፣ ሩስያ፣ ግብፅ፣ እስራኤል፣ ቻይናና ጃፓን ከተጓዘባቸውና ለተወሰኑ ጊዜያት ከቆየባቸው አገራት ውስጥ ይጠቀሳሉ፡፡ በ1945 ዓ.ም. ለአጭር ጊዜ በግሪክ የትምህርት ሚ/ር ሚኒስትር ዲኤታ በመሆን ተሾሟል፡፡ ከ1947-48 ዓ.ም. ድረስ ደግሞ በዩኔስኮ የትርጉም ቢሮን በዳይሬክተርነት መርቷል፡፡ በአጠቃላይ 30 የሚሆኑ ልብ ወለዶችን፣ ቲአትሮችንና የፍልስፍና መጽሐፎችን ጽፏል፡፡ ልብወለድ መጻፍ የጀመረው በአመሻሽ ዕድሜው ቢሆንም፣ ከ65 ዓመቱ ጀምሮ ባሉት ዘጠኝ ተከታታይ ዓመታት ስምንት የልብወለድ መጻሕፍትን ማበርከት ችሏል፡፡ ታዋቂ ከሆኑት ልብወለዶቹ መካከል፣ Zorba the Greek, The Greek Passion እና The Last Temptation of Christ (የመጨረሻው ፈተና) ይገኙበታል፡፡
በተደጋጋሚ ለሥነጽሑፍ የኖቤል ሽልማት የታጨ ቢሆንም፣ በተለይ ደግሞ በ1952 ዓ.ም. በአንድ ድምፅ ብቻ ተበልጦ ሳይሸለም ቀርቷል፡፡ ከዚህ ዓለም በሞት የተለየው በ1957 ዓ.ም. ነው፡፡ የመቃብር ሀውልቱ ላይ እንዲጻፍ አደራ ያለው ቃል፡-
“ምንም አልፈራም፣   I fear nothing
ምንም አልጠብቅም፣ I hope for nothing
ነፃ ነኝ!” የሚል ነበር፡፡ I am free.

 ሁለት ንሥሮች ስለወደፊት ዕጣ-ፈንታቸው ይጨዋወታሉ፡፡ አንደኛው - “እኛ ንሥሮች፤ ሰዎች እንዳያጠቁን በየጊዜው እየተገናኘን መወያየት፣ መነጋገር፣ ደካማ ጎናችንን እያነሳን መፍትሔውን ማግኘት ያስፈልገናል፡፡ ስለዚህ ሁሉንም ንሥሮች ሰብስበን እንነጋገርና አንድ ዓይነት አቋም እንያዝ”
ሁለተኛው ንሥር - “በዕውነቱ በጣም ቀና ሀሳብ ነው፡፡ ሁሉም እንዲሰበሰቡ ማስታወቂያ እንለጥፍ” አለ፡፡
በዚህ ተስማምተው በዓይነቱ ልዩ ነው የሚባል (Extraordinary) አጠቃላይ ስብሰባ ጠሩ፡፡ ንሥር- ሜዳ በሚባል ሰፊ ቦታ በተባለው ሰዓት ማንም ንሥር እንዲመጣ፤ የቀረ ከመላው ንሥሮች እንቅስቃሴ ያፈነገጠ፣ ከሀዲ (Saboteur) ነው የሚል ማስጠንቀቂያም ታከለበት፡፡
በተባለው ቦታና ሰዓት የአገሩ ንሥር ሁሉ ተሰበሰበ፡፡ ‘አጀንዳው “ከዛሬ ጀምሮ ሰው እንዳያጠቃን አንድ ዓይነት አቋም ይዘን በጥንቃቄ እንድንንቀሳቀስ ይሁን፣” የሚል ነው፡፡ በመሰረቱ ሰው እኛን መናቁ ያለ ነገር ነው፡፡ ነገር ግን ማንኛውም ነገር ከትንሽ ጀምሮ ወደ ትልቅ እንደሚያድግ፣ ከቀላሉ ወደ ውስብስቡ እንደሚሄድ ካለመረዳት የሚመጣ ግብዝነት ነው፡፡ ስለዚህ ምንም አቅማችን ትንሽ ቢሆን፣ ቀስ በቀስና ከቀን ቀን ስለምንጠነክር ትንሽነት አይሰማችሁ፡፡ ብርታት ከትንንሾች ህብረት የሚመጣ ነው” አለና ንግግር አደረገ፣ ሰብሳቢው ንሥር፡፡ ሁሉም በክንፎቻቸው አጨበጨቡ፡፡ በንሥራዊ ድምጽም እልልታቸውን አሰሙ፡፡ “የንሥሮች ኅብረት ለዘለዓለም ይኑር” የሚል መፈክር በአንድነት አሰገሩ፡፡
ይህ ስብሰባ በተካሄደ በጥቂት ጊዜ ውስጥ በአንድ ጫካ ውስጥ አንድ አዳኝ ቀስትና ደጋን ይዞ ታየ፡፡ ንሥሮቹ ሁሉ እየተመካከሩ ሸሹ፡፡ አዳኙም ተናዶ ወደ መንደሩ ተመለሰ፡፡ ሌላም ቀን ለአደን መጣ፡፡ ንሥሮቹ ተጠራርተው በረሩ፡፡
አንድ ቀን ግን አዳኙ ንስሮቹ በማያውቁት አቅጣጫ ዞሮ ወደ ጫካው ገባ፡፡ ከንሥሮቹ አንዳቸውም አልጠረጠሩም፡፡ ኮሽታ ታህልም ድምጽ አልሰሙም፡፡
አዳኙ ዓልሞ ወደ አንደኛው ንሥር አነጣጠረ፡፡ ቀስቱን ስቦ ሲለቅቀው አንደኛው ንሥር ልብ ላይ ተተከለ፡፡ ንሥሩ ልቡ ላይ የተተከለው ስል ቀስት በጣም ባሰቃየው ጊዜ፣ በጣሩ ቅጽበት ወደ ኋላ ዞሮ ተመለከተ፡፡ የቀስቱን ጫፍ አየው፡፡ የቀስቱ ጭራ የተሰራው ከንስር ላባ ነው፡፡ ህመሙ በርትቶበት ሊሞት ሲል እንዲህ አለ፡-
“እኛ እራሳችን በሰጠነው መሣሪያ ስንወጋ ነው ለካ፣ ቁስሉ የበለጠ ጥልቀት የሚኖረው”
ከዚያም ለምታስታምመው ንሥር እንዲህ አላት፡-
“ከእንግዲህ ለጠላታችን አለመመቸት ማለት የራሳችንን መሳሪያ አለመስጠት ማለት ብቻ አይደለም፡፡ ይልቁንም ወደ እኛ መምጫዎቹን በሮች በሙሉ ጠንቅቆ ማወቅና መዝጋት ነው፡፡ ይህንን ለወገኖቻችን ሁሉ ንገሪ” ብሎ ትንፋሹ አበቃ፡፡
***
መክረው ተመካክረው የሰሩት መንገድ ብዙ ዘመን ያስኬዳል፡፡ የሰው ቤት አያስፈርስም፡፡ የድሃ መተዳደርያ አይነፍግም፡፡ የሰው ድንበር አያስዘልልም፡፡ ማህበራዊ ምስቅልቅል አያስከትልም፡፡ ብዙ ኩርፊያ፣ ብዙ ቅያሜ አይፈጥርም፡፡ ቢሳሳቱ ስንመክር ተሳስተን ነበር፤ ያላየነው - ያላስተዋልነው ነገር ነበር ለማለት አይከብድም፡፡ ራሳችን የሰጠነው መሳሪያ ክፉኛ እንዳቆሰለን ገብቶናል ለማለት ያስችላል፡፡ መሰብሰብ፣ ሸንጎ መዋል የተለመደና የነበረ ነው፡፡ ከዚህ እሳቤ በመነሳት በሀገራችን ከጥንት እስከዛሬ በሽንጎ መምከር ክፉ-ደግ መመርመር የተዘወተረ ነው፡፡ በተለይ የኢትዮጵያ ተማሪዎችና መምህራን በዚህ ቀዳሚውን ቦታ የሚይዙ መሆናቸው አሌ አይባልም፡፡ ትምህርት ቤቶች ነጻ የውይይት መድረክ እንዲኖራቸው ብዙ ትግል ተካሂዷል፡፡ ትክክልም ይሁኑ ስህተት በጥቂቶች አነሳሽነት የሚጠሩ ምድር ሰማይ የሚደባልቁ፣ መንግስት የሚነቀንቁ፣ የአገር ዕውነት የሚናገሩ ስብሰባዎች ነበሩ፡፡ ቀስ በቀስም የጎሹት እየጠሩ፣ የጎለደፉት እየተሳሉ፣ የሻከሩት እየለሰለሱ ለሀገር ወደሚበጅ ሁነኛ ጥያቄና መፍትሔ እንዳደጉ አይተናል፡፡ አበው “መንገድና ትውልድ የማያውቅ የተጎዳ ነው” እንዲሉ መንገድ የሚያውቅ፣ በዕውቀት የታነጸ፣ ጠያቂና አስተዋይ ትውልድ ማፍራት ከየዘመኑ ይጠበቃል፡፡ ጊዜ ይጠይቃል እንጂ ፍሬ ያለው ትውልድ ይገኛል፡፡ ቀና ተመኝ ቀና እንድታገኝ ነው፡፡
ከፍተኛ የትውልድ አስተሳሰብ የምናፈልቀው የዕውቀት ምንጭ ከሆነው ት/ቤት ነው፡፡ ለት/ቤት የምንሰጠው ክብር፣ ለዕውቀት የምንጠሰው ክብር ነው፡፡ ለዕውቀት የምንሰጠው ክብር፣ ለትውልድ የምንሰጠው ክብር ነው፡፡  የትምህርት ፖሊሲዎች ጊዜ የተወሰደባቸው፣ ብዙ አዕምሮ የፈሰሰባቸው፣ ለሀገር የማደግ ተስፋን የሚጠምቁ መሆን ይገባቸዋል፡፡  ለመሻሻል እፈልጋለሁ የሚል ዕምነት ያለው ፖሊሲ - ቁራጭ፤ በሂደትና በተመክሮ ስህተት ቢያይ፣ ተከታትሎ ለማረም፤ ተሳስቼ ነበር ለማለት ድፍረት ሊኖረው ይገባል፡፡ ከእኔ እጅ በሰላም ከወጣ እንደፍጥርጥሩ በሚል ስሜት በተግባር የሚያውሉትን ወገኖች ሌላ አበሳ ውስጥ የሚከትት ከሆነ፣ ችግርን ለመፍታት ችግር ያለበት መፍትሄ እንደ መስጠት ይቆጠራል፡፡ ተመሳሳይ ሰዎች በተመሳሳይ አስተሳሰብ “ልክ ነው” ያሉት ውሳኔ ውሎ አድሮ በተግባር ሲታይ ሌላ ዕዳ ይዞ ይመጣል፡፡ በዳተኝነትም ይሁን በብልጠት እሰይ እሰይ ያሉት ሥራ፣ የማታ ማታ “ሰነፍና ገብሎ ራሳቸውን እንደነቀነቁ ይኖራሉ” የሚለውን ተረት ከማስታወስ በቀር የረባ ለውጥ አያመጣም፡፡
ትላንት የተማርንበት ት/ቤት፣ ዛሬ ተዳክሞ ላለማየት ብርቱ ጥረት ማድረግ ይጠበቅብናል፡፡ ቢያንስ ለመልካም ትዝታችን ቦታ መስጠት፣ የጠንካራን ትውልድ ምንነት ለማጤን ይጠቅማል፡፡ የሠራንበት መስሪያ ቤት ከምናውቀው ተዳክሞ ስናይ፣ የሚሰማን የቁጭት ስሜት የሀገርን መዳከም እንደሚጠቁም ለማየት የአዕምሮ አቅም ማጣት የለብንም፡፡
በተደጋጋሚ የሚወጡ መመሪያዎች፣ ማሻሻያዎች ማጠናከሪያዎች የሚፈጥሩትን እሮሮ፣ እምቢታ፣ የተቃውሞ ምላሽ መመልከት በተለይ እንደኛ ላለ አገር መሰረታዊነትና ተገቢነት አለው፡፡ ብዙ ሰው ተቃውሞ ቀርቶ፣ አልገባንም የሚለውን ጉዳይ ቆም ብሎ አለመመርመር ጎጂ ነው፡፡ ብዙ ሰው የሚያወርደውን እርግማን መናቅ የበለጠ ጎጂነት አለው፡፡ አበው “እርግማን ንግግር እየመሰለ ይገድላል፡፡ ፀበል ውሃ እየመሰለ ይምራል” የሚሉት ለዚህ መሆኑን ልብ ማለት ዋና ነገር ነው፡፡

 የፖለቲካ ሹመኞች በሙያተኞች ላይ በሚያሳድሩት ጫና የመንግሥት ሥራ እየተደናቀፈ ነው ሲሉ በተለያዩ የመንግስት ተቋማት ውስጥ የሚሰሩ ባለሙያዎቹ ለአዲስ አድማስ ተናገሩ። በብዙዎቹ የመንግስት መ/ቤቶች ሃላፊዎች ሥልጣን ላይ የሚቀመጡት በፖለቲካ ታማኝነት እንጂ በዕውቀትና በብቃት ባለመሆኑ በሙያተኞች ላይ የሚያሳድሩት ጫና ሥራውንም ባለሙያውንም እየጎዳው መሆኑንም ያስረዳሉ። እየጎዳው ነው ተብሏል፡፡
በአንድ የመንግስት መ/ቤት ውስጥ በከፍተኛ ኤክስፐርትነት የሚሰሩት ግሩም ኤሊያስ (ዶ/ር) የተባሉ ግለሰብ ለአዲስ አድማስ እንደተናገሩት፤ በመ/ቤቱ ውስጥ  በከፍተኛ ኤክስፐርትነት ቢቀጠሩም፣ በሃላፊነት የተመደበው ዋና ሥራ አስፈጻሚ የፖለቲካ ሹመኛ በመሆኑ ሙያተኞች ሥራቸውን በቅጡ መስራት አልቻሉም ብለዋል።
እንደ ኤክስፐርቱ ገለፃ፣ ለሀገር ይጠቅማል ብለን የምናጠናው ጥናት፣ የምናቅደው ስትራቴጂክ ዕቅድ በሙሉ በዋና ስራ አስፈጻሚው ውድቅ ይደረጋል። የተሻለ ሀሳብ አይቀርብም፣ የተለፋበት ጥናትና እቅድ መና ይቀራል፡፡ እኛ ግን ከፍተኛ ደሞዝ እየተከፈለን ቀጥለናል። ይህ ደግሞ ህሊና ላለው ሰው ከባድ ነው ብለዋል፤ ግሩም ኤልያስ (ዶ/ር)።
ለደህንነታቸው ሲሉ የመስሪያ ቤታቸው ስም እንዳይጠቀስ የፈለጉት እኚህ ከፍተኛ ኤክስፐርት፤ በሥራ ባልደረቦቻቸው ዘንድ በማያምኑበት ጉዳይ ሁሉ ከአለቃቸው በመቃወም የሚታወቁ ሲሆን በዚህም ሳቢያ ከአንዴም ሶስት ጊዜ በዲሲፕሊን ጥሰት የደሞዝ ቅጣት፣ ሌላ ጊዜ ደግሞ ከደረጃ ዝቅ የመደረግ ዕጣ ፈንታ እንደገጠማቸው ለአዲስ አድማስ ገልፀዋል።
ግሩም ኤርምያስ ላለፉት ዓመታት ሲሰሩ በቆዩበት መስሪያ ቤት፣ ሥራቸውን በብቃትና በትጋት ከሚሰሩ ኤክስፐርቶች  ይልቅ ለበላይ አካል ወሬ የሚያቀብሉና የሚላላኩ፣  የመስሪያ ቤቱ “ቁንጮ ሰራተኞች” ተብለው ይሸለማሉ፣ ደሞዛቸው ያድጋል ይመነደጋል፤ የደረጃ እድገትም ያገኛሉ መንግስት ይህን፤ አገርንም ህዝብንም የሚጎዳና እድገትን የሚጎትት የፖለቲካ ሹመኞች ፈላጭ ቆራጭነት በጊዜ ማስተካከል ካልቻለ፣ አገር ወደፊት መራመድ አትችልም ብለዋል። እርሳቸው በሙያቸው አገር ማገልገል ስላለባቸው ወደ ግል ተቋማት እያማተሩ መሆኑንም ገልፀዋል፡፡
ሌላው በኢትዮ ቴሌኮም በከፍተኛ ባለሙያነት የሚሰራው ዘሪሁን አማን (ስሙ ተቀይሯል) የተባለ ወጣት ኤክስፐርት በበኩሉ፤ ከደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ ዩኒቨርሲቲ ሁለተኛ ዲግሪውን ይዞ ወደ ሀገሩ መመለሱን ይናገራል። በለውጡ ሰሞን በኢትዮ ቴሌኮም የተቀጠረው ይሄው  ወጣት ባለሙያ፤ ለውጡ የመጣ ሰሞን የነበረውን ተስፋና የለውጡ መንግስት ሥልጣን በያዘ ሰሞን በአገሪቱ የተስተዋለውን መነቃቃት በመተማመን ሀገሩን ለማገልገል ወጣትነቱን፣ ትኩስ ጉልበቱንና እውቀቱን ይዞ ወደዚህ መስሪያ ቤት መግባቱን ገልጿል።
በተለይ የመሥሪያ ቤቱ ዋና ስራ አስፈጻሚ ወይዘሪት ፍሬህይወት ከተሾመች በኋላ ኢትዮ ቴሌኮም ብዙ ፈጣን ለውጦችን እንዲሁም አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን  ማስተዋወቁን የሚናገረው ወጣቱ፤ ከሃላፊዋ ስር ያሉ የፖለቲካ ሹመኞች ግን ተቋሙ የበለጠ እድገት እንዳያስመዘግብ ሙያተኞች ላይ የሚያሳድሩት ጫና ከፍተኛ ነው ይላል በምሬት። “ለሙያውና ለቴክኖሎጂው ያለኝን ቅርበትና የውጪ ተሞክሮዎችን በመጠቀም ተቋሙ የሌላው አገር ቴሌኮሙኒኬሽን የደረሰበት ደረጃ ላይ እንዲደርስ ሌት ተቀን የማደርገው ጥረት ለአለቃዬ ምቾት አይሰጠውም፣ ያለው ወጣቱ፤ ከፍተኛ ኤክስፐርት፤ ይህም በሀገሬ በሙያዬና በአጠቃላይ ባለው በሁኔታ መሰላቸትና ተስፋ መቁረጥ ውስጥ እያስገባኝ ነው ብሏል።
ወጣቱ አክሎም፤ ቢያንስ የፖለቲካ ሹመኞች የፖለቲካ ታማኝነታቸው እንዳለ ሆኖ ለሚመሩት መስሪያ ቤትና የስራ ጠባይ ቢቻል ሙያውን የተማሩና በዘርፉ እውቀት ያላቸው፣ ካልተቻለ ተቀራራቢ ሙያ ውስጥ ያሉ ቢሆኑ አገርን ከዘርፈ ብዙ ችግር መታደግ ስለሚችል መንግስት ጉዳዩን ያስብበት ጥሪ አቅርቧል።

 • ገዳሙን ለመታደግ 100 ሚ.ብር ያስፈልጋል


        ለአቡነ ሐራ ድንግል አንድነት ገዳም፣ በዛሬው ዕለት ከቀኑ 10  ሰዓት ጀምሮ፣ በካፒታል ሆቴል ዓለማቀፍ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃግብር የሚካሄድ ሲሆን፤ገቢው በገዳሙ ይዞታ ላይ ለሰፈሩ ነዋሪዎች ካሣ በመክፈል ይዞታውን ለገዳሙ ለማስመለስ ነው ተብሏል፡፡ የገዳሙ ገቢ ማሰባሰቢያ ኮሚቴ እንደገለጸው፤ ገዳሙን ለመታደግና ለማስፋፋት በአጠቃላይ 100 ሚሊዮን ብር ያስፈልጋል፡፡
 ገዳመ ወንያት አቡነ ሐራ ድንግል የአንድነት ገዳም፣ በ1574 የተመሰረተና የጻዲቁ አባት አቡነ ሐራ ድንግል ገድልና ገቢረ ተዓምራት የሚካሄድበት ገዳም ነው - ይላሉ የገዳሙ መነኮሳት፡፡
ከ400 ዓመት በላይ ታሪክ ያለው ይህ ትልቅ ገዳም በሰሜን ጎጃም፣ ባህርዳር ዙሪያ የሚገኝ ሲሆን፣ ጻዲቁ አቡነ ሐራ ድንግል፣ ከፈጣሪያቸው በተገባላቸው ቃልኪዳን መሠረት፣ ደዌን ሲፈውሱና ተዓምራትን ሲሰሩ የቆዩበትና አሁንም የሚሰሩበት ጥንታዊ ገዳም መሆኑን፣ የገዳሙ ገቢ አሰባሳቢ ኮሚቴ ባወጣው  መግለጫ ጠቁሟል፡፡ ይሁን እንጂ ይህ ገቢረ ተዓምር የሚሰራበት ታሪካዊ ገዳም፣ ትልቅ ችግር እንደተጋረጠበት መነኮሳቱ ተናግረዋል፡፡
“ለፈውስና ለድህነት ከመላው አገሪቱ ወደ ገዳሙ የሚመጡ ምዕመናን ድህነትና ፈውስ ካገኙ በኋላ፣ ገዳሙን ተጠግተው ቤት በመሥራት እዚያው እየኖሩ፣ ገዳሙ ይዞታውን እየተነጠቀ ከመጣበቡም በላይ፣ የገዳሙን ቅድስና የሚያረክሱ ተግባራት እየተፈጸመበት ይገኛል፡፡”  ይላል፤ የኮሚቴው መግለጫ፡፡
የገዳሙ መነኮሳት የታሪክ ዶሴና ማስረጃ ላይ ተንተርሰው እንደሚናገሩት፤ ዓጼ ዮሐንስ በነቀርሳ ተይዘው በአቡነ ሐራ ድንግል ጸበል በመዳናቸው ነበር ለገዳሙ የአንድ ሰዓት የእግር መንገድ ያህል ስፋት ያለው ቦታ ለገዳሙ የሰጡት፡፡ ደርግ ሥልጣን ሲይዝ በገዳሙ 800 የሚደርሱ መናንያን እንደነበሩ የሚያስታውሱት መነኮሳቱ፤ በወቅቱ “መሬት ላራሹ” የሚል አዋጅ በመታወጁ የገዳሙን ይዞታ አርሶ አደሮች እየተቆጣጠሩት እንደመጡና መናንያኑ ገዳሙን ጥለው መኮብለላቸውን ያስረዳሉ፡፡
በአሁኑ ወቅት በገዳሙ ይዞታ ላይ ከ250 በላይ አባወራዎች ሰፍረው እንደሚገኙ የሚገልጹት መነኮሳቱ፤ ይህን ችግር ለመቅረፍ ለመንግሥት በተደጋጋሚ አቤቱታ ካቀረቡ በኋላ፣ መንግሥት ነዋሪዎቹን አንስቶ ሌላ ቦታ ለማስፈር ፈቃደኛ ቢሆንም፣ ለነዋሪዎች ካሣ ለመክፈል በጀት እንደሌለው በመግለጽ፣ ገዳሙ ካሣውን እንዲከፍል መወሰኑን ይናገራሉ፡፡
ሆኖም የሚከፈለው ካሣ ከገዳሙ አቅም በላይ በመሆኑ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃግብር ማዘጋጀት አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል የሚለው  የገዳመ ወንያት አቡነ ሐራ ድንግል አንድነት ገዳም የገቢ ማሰባሰቢያ ኮሚቴ፤ ባለፈው ሐሙስ  በጠቅላይ ቤተክህነት አዳራሽ፣ ስለ ገዳሙ አሁናዊ ሁኔታና ስለ ገቢ ማሰባሰቢያ   መርሃ ግብሩ  ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል፡፡
በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ እንደተነገረው፣ የአማራ ክልል ካቢኔ ለገዳሙ ሁሉንም ይዞታውን ባይሆንም 60 ሄክታር የሚደርስ ቦታ እንዲመለስለት የወሰነ ሲሆን፤ ገዳሙ በበኩሉ ለአርሶ አደሮቹ የሚገባቸውን የመሬት ካሣ መክፈል ይጠበቅበታል፡፡  ይህን የመሬት ካሣ ለመክፈልና ለገዳሙ የማስፋፊያ ልማት ለማከናወን፣ ዛሬ  ቅዳሜ ሚያዝያ 19 ቀን 2016 ዓ.ም በካፒታል ሆቴል፣ በቀጥታ የቴሌቪዥን ሥርጭት፣ ከቀኑ 10 ሰዓት ጀምሮ እስከ ሌሊቱ 6 ሰዓት የሚቆይ  ዓለማቀፍ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃግብር እንደሚያካሂድ  ኮሚቴው  አስታውቋል፡፡ ለአርሶ አደሮቹ የመሬት ካሣውን ለመክፈልና የገዳሙ ይዞታ ከተለቀቀ በኋላ በሥፍራው ለሚከናወኑ ልማቶች በአጠቃላይ 100 ሚሊዮን ብር እንደሚያስፈልገው የገለጸው የገቢ አሰባሳቢ ኮሚቴው፤ በመላው ዓለም የሚገኙ የቤተክርስትያን ልጆችና የጻድቁ አቡነ ሐራ ወዳጆች በዚህ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብር ላይ በንቃትና በትጋት እንዲሳተፉ ጥሪ አቅርቧል፡፡
በአሁኑ ወቅት በገዳሙ የሚገኙ መናንያን ቁጥር 5ሺ እንደሚደርሱና በጾም ወቅት የጸበልተኛው ቁጥር ከ50 ሺ በላይ መሆኑን የጠቆመው  የገቢ አሰባሳቢ ኮሚቴው፤ እኒህን ሁሉ በአግባቡ የሚያስተናግድ በቂ መጠለያና የልማት ሥራዎች ማከናወን አስፈላጊ እንደሆነ በአጽንኦት ተናግሯል፡፡


ስብሐቲዝም የሀሳብ ውይይት የፊታችን እሁድ ሚያዝያ  20 2016 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ጀምሮ በኢትዮጵያ ቤተመዛግብት እና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት(ወመዘክር) አዳራሽ ውስጥ ይካሄዳል።

"የሕላዌ እንቆቅልሽ " የተሰኘ መጽሐፍ ነገ ይመረቃል

የደራሲ ማንደፍሮ ማሩ "የሕላዌ እንቆቅልሽ" የተሰኘ አዲስ መጽሐፍ ቅዳሜ ሚያዝያ 19 2016 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 ጀምሮ በወመዘክር አዳራሽ ይመረቃል።

በደራሲ ባየህ ንጉሴ የተዘጋጀው “ፋሽን” የተሰኘ በፋሽን እና ሞዴሊንግ ላይ ትኩረቱን ያደረገ መጽሐፍ ቅዳሜ ሚያዝያ 19/2016 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ጀምሮ የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር) አዳራሽ ጥሪ የተደረገላቸው
የጥበብ ቤተሰቦች እና እንግዶች በተገኙበት ይመረቃል ይመረቃል።በስድስት ምዕራፍ የተከፈለው መጽሐፉ ስለ ሞዴሊንግ አይነቶች፣ ሞዴል የመሆን ትሩፋቶች እና ተግዳሮቶች፣ የቁንጅና ውድድር፣ ሻምፖ እና ኮድሽነር አመራረጥ፣ ፖርትፎሊዮና ሌሎችም ዝርዝር ጉዳዮችን ይዟል።

ዘመን ባንክ የሠራተኞቹን ዕውቀትና ክህሎት ለማሳደግ፣ በዓለም  ትልቁ የኢንተርኔት የመማሪያ መድረክ ከሆነው ሊንክድኢን ሊርኒንግ ጋር የአጋርነት ስምምነት ተፈራረመ፡፡

የዘመን ባንክ የሰው ሀብት ምክትል ዋና ኦፊሰር አቶ ታከለ ዲበኩሉ ስለ ስምምነቱ ሲገልጹ፤ “ዘመን ባንክ ለሰራተኞቹ ቀጣይነት ያለው የመማርና የሙያ እድገት ባህልን ለማሳደግ ቁርጠኛ ነው። ከሊንክድኢን ለርኒንግ ጋር ያደረግነው ስምምነት፣ ይህንን ቁርጠኝነት የሚያጎላ ከመሆኑም በላይ ሠራተኞቻችን በፋይናንስ ዘርፉ የሚጠይቀውን ችሎታ፣ እውቀትና ክህሎት እንዲያሳድጉ የሚረዳ ነው፡፡" ብለዋል፡፡

የሊንክድኢን ታለንት ሶሉዩሽን ዋና ኃላፊ ማቲው ግሬይ በበኩላቸው፤ ”ከዘመን ባንክ ጋር ያደረግነው ስምምነት የሰራተኞቹን የክህሎትና የእውቀት ክፍተቶችን ለማሟላት እድሉን የሚሰጠን ከመሆኑም በላይ ሊንክድኢን ለርኒንግ በአፍሪካ ተመራጭ የክህሎት ልማት መድረክ ሆኖ  መቀጠሉን ስለሚያሳይ እጅግ ተደስተናል። የዘመን ባንክ የሰው ሃብት ስትራቴጂ በቀጣይ አመታት ይበልጥ እንዲጎለብትና ውጤታማ እንዲሆን አብረን እንሰራለን።" ብለዋል፡፡

የእነዚህ ኮርሶች ወጪ ሙሉ በሙሉ በዘመን ባንክ የተሸፈነ ሲሆን፤ የባንኩ ሠራተኞች ሥልጠናውን  በነፃ እንደሚያገኙ  ታውቋል፡፡

ኢንጂነር ቢጃይ ናይከር ግማሽ ሚሊዮን (500ሺህ) ብር፣
ድምፃዊ ዳዊት ፅጌ 100ሺ ብር በመስጠት ጀምሯል ደጋግ ኢትዮጵያውያኖች የአቅማችሁን በማድረግ የትዕግስት ሶስት መንታ ልጆች የአይን ብርሃናቸው እንዲመለስ የበኩላችንን እናድርግ።
ሼር በማድረግ እንጀምር!
አካውንታቸው ይህው እባካችሁ
ሼር አድርጉት
* СВЕ 1000622473872
* Dashen Bank 5563671317021
* Abyssinia bank 91613069
* ኦሮሚያ ኅብረት ስራ ባንክ 1023500172828
* አዋሽ ባንክ 013471254339600
ትግስት ካሳ ቀፀላ
ስልክ
* 0911868306
* 0911137097
go fund me
ይህን ሼር ማድርግ መልካም ነገር መስራት ነውና እባካችሁ ሼር አድርጉላቸው
• ገዳሙን ለመታደግ ቅዳሜ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃግብር ይካሄዳል
ገዳመ ወንያት አቡነ ሐራ ድንግል የአንድነት ገዳም በ1574 የተመሰረተና የጻዲቁ አባት አቡነ ሐራ ድንግል ገድልና ገቢረ ተዓምራት የሚካሄድበት ገዳም ነው - ይላሉ የገዳሙ መነኮሳት፡፡
ከ400 ዓመት በላይ ታሪክ ያለው ይህ ትልቅ ገዳም በሰሜን ጎጃም፣ ባህርዳር ዙሪያ የሚገኝ ሲሆን፣ ጻዲቁ አቡነ ሐራ ድንግል፣ ከፈጣሪያቸው በተገባላቸው ቃልኪዳን መሠረት፣ ደዌን ሲፈውሱና ተዓምራትን ሲሰሩ የቆዩበትና አሁንም የሚሰሩበት ጥንታዊ ገዳም መሆኑን፣ የገዳሙ ገቢ አሰባሳቢ ኮሚቴ ያወጣው መግለጫ ይጠቁማል፡፡
ይሁን እንጂ ይህ ገቢረ ተዓምር የሚሰራበት ታሪካዊ ገዳም፣ ትልቅ ችግር እንደተጋረጠበት መነኮሳቱ ተናግረዋል፡፡
“ለፈውስና ለድህነት ከመላው አገሪቱ ወደ ገዳሙ የሚመጡ ምዕመናን ድህነትና ፈውስ ካገኙ በኋላ፣ ገዳሙን ተጠግተው ቤት በመሥራት እዚያው እየኖሩ፣ ገዳሙ ይዞታውን እየተነጠቀ ከመጣበቡም በላይ፣ የገዳሙን ቅድስና የሚያረክሱ ተግባራት እየተፈጸመበት ይገኛል፡፡” ይላል፤ የኮሚቴው መግለጫ፡፡
የገዳሙ መነኮሳት የታሪክ ዶሴና ማስረጃ ላይ ተንተርሰው እንደሚናገሩት፤ ዓጼ ዮሐንስ በነቀርሳ ተይዘው በአቡነ ሐራ ድንግል ጸበል በመዳናቸው ነበር ለገዳሙ የአንድ ሰዓት የእግር መንገድ ያህል ስፋት ያለው ቦታ ለገዳሙ የሰጡት፡፡ ደርግ ሥልጣን ሲይዝ በገዳሙ 800 የሚደርሱ መናንያን እንደነበሩ የሚያስታውሱት መነኮሳቱ፤ በወቅቱ “መሬት ላራሹ” የሚል አዋጅ በመታወጁ የገዳሙን ይዞታ አርሶ አደሮች እየተቆጣጠሩት እንደመጡና መናንያኑ ገዳሙን ጥለው መኮብለላቸውን ያስረዳሉ፡፡
በአሁኑ ወቅት በገዳሙ ይዞታ ላይ ከ250 በላይ አባወራዎች ሰፍረው እንደሚገኙ የሚገልጹት መነኮሳቱ፤ ይህን ችግር ለመቅረፍ ለመንግሥት በተደጋጋሚ አቤቱታ ካቀረቡ በኋላ፣ መንግሥት ነዋሪዎቹን አንስቶ ሌላ ቦታ ለማስፈር ፈቃደኛ ቢሆንም፣ ለነዋሪዎች ካሣ ለመክፈል በጀት እንደሌለው በመግለጽ፣ ገዳሙ ካሣውን እንዲከፍል መወሰኑን ይናገራሉ፡፡
ሆኖም የሚከፈለው ካሣ ከገዳሙ አቅም በላይ በመሆኑ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃግብር ማዘጋጀት አስፈላጊ ሆኖ አግኝቶታል የሚሉት የገዳመ ወንያት አቡነ ሐራ ድንግል አንድነት ገዳም የገቢ ማሰባሰቢያ ኮሚቴ አባላት፤ ዛሬ ከቀኑ 9 ሰዓት ላይ በጠቅላይ ቤተክህነት አዳራሽ ስለ ገዳሙ አሁናዊ ሁኔታና ስለገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብሩ ሊቃነ ጳጳሳት፣ የገዳሙ መነኮሳት፣ የቤተክህነት አባቶችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡
በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ እንደተነገረው፣ የአማራ ክልል ካቢኔ ለገዳሙ ሁሉንም ይዞታውን ባይሆንም 60 ሄክታር የሚደርስ መሬት እንዲመለስለት የወሰነ ሲሆን፤ ገዳሙ በበኩሉ ለአርሶ አደሮቹ የሚገባቸውን የመሬት ካሣ መክፈል ይጠበቅበታል፡፡
ይህን የመሬት ካሣ ለመክፈልና ለገዳሙ የማስፋፊያ ልማት ለማከናወን፣ የፊታችን ቅዳሜ ሚያዝያ 19 ቀን 2016 ዓ.ም በካፒታል ሆቴል፣ በቀጥታ የቴሌቪዥን ሥርጭት፣ ከቀኑ 10 ሰዓት ጀምሮ እስከ ሌሊቱ 6 ሰዓት የሚቆይ ዓለማቀፍ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃግብር እንደሚያካሂድ ኮሚቴው አስታውቋል፡፡
ለአርሶ አደሮቹ የመሬት ካሣውን ለመክፈልና የገዳሙ ይዞታ ከተለቀቀ በኋላ በሥፍራው ለሚከናወኑ ልማቶች በአጠቃላይ 100 ሚሊዮን ብር እንደሚያስፈልገው የገለጸው የገቢ አሰባሳቢ ኮሚቴው፤ በመላው ዓለም የሚገኙ የቤተክርስትያን ልጆችና የጻድቁ አቡነ ሐራ ወዳጆች በዚህ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብር ላይ በንቃትና በትጋት እንዲሳተፉ ጥሪ አቅርቧል፡፡
በአሁኑ ወቅት በገዳሙ የሚገኙ መናንያን ቁጥር 5ሺ እንደሚደርሱና በጾም ወቅት የጸበልተኛው ቁጥር ከ50 ሺ በላይ መሆኑን የጠቆሙት የገቢ አሰባሳቢ ኮሚቴ አባላቱ፤ እኒህን ሁሉ በአግባቡ የሚያስተናግድ በቂ መጠለያና የልማት ሥራዎች ማከናወን አስፈላጊ እንደሆነ በአጽንኦት ተናግረዋል፡፡
ለገዳሙ ድጋፍ ማድረግ የሚሹ ወገኖች፡-
በንግድ ባንክ የሒሳብ ቁጥር፡- 1000610362463
በአባይ ባንክ የሒሳብ ቁጥር፡- 9221111060954312
እንዲሁም የዶላር ሒሳብ ቁጥር፡- 634110814 መለገስ ይችላሉ ተብሏል፡፡
Page 1 of 703