Administrator

Administrator

     በዓለም ላይ በተደጋጋሚ ዝናን አትርፈው ተጠቃሽ ከሆኑት ተረቶች መካከል የሚከተለው ይገኝበታል። ደራሲ ገብረክርስቶስ ኃይለሥላሴ በፃፉት “የሉሲ ከዋክብትና ሌሎችም” በተሰኘው የውርስ ትርጉም የልጆች መልካም ሥነ - ምግባር መጽሐፍ፤ ያገኘነውን ለዛሬ ባጭሩ አቅርበነዋል። በድሮ ጊዜ በአራዊትና በወፎች መካከል ጦርነት ተደርጐ ነበር። የሌት ወፎች ከወፎች ጋር ተሰልፈው ተዋግተዋል። ነገር ግን በመጀመሪያው ጦርነት ወፎች ክፉኛ ተሸነፉ። የሌት ወፎች በሁኔታው ስለሰጉ በየዛፉ አንጓ ላይ ተደብቀው፣ የጦርነቱን የመጨረሻ ውጤት ተጠባበቁ። ድል አድራጊዎቹ አራዊት ወደቤታቸው ሲሄዱ፣ የሌት ወፎች ተደባልቀው አብረው ሄዱ። ትንሽ ከተጓዙ በኋላ፣ አራዊቱ ነቁባቸው (አወቁባቸው)። “ይቅርታ! እናንተ ከወፎች ወገን ተሰልፋችሁ የወጋችሁን አይደላችሁም እንዴ?” በማለት የሌት ወፎችን ጠየቋቸው። የሌት ወፎችም እንዲህ ሲሉ መለሱ።

“ኦ! በፍፁም! እኛ እኮ እንደ እናንተ ነን። ጥፍራችንንና ጥርሳችንን ብትመለከቱ ከእናንተ ጋር ተመሳሳይ ነው። ወንድማማቾች እኮ ነን። ወፎች እንዲህ እንደ እኛ አካል አላቸውን? በፍፁም! እኛ የአራዊት ወገን ነን! (አይጦች ነን!)” አራዊቱ ሁ ኔታውን ከ ሰሙ በ ኋላ ዝ ም አ ሉ። የ ሌት ወ ፎቹንም አ ብረዋቸው እ ንዲሆኑ ፈቀዱላቸው። ከአይጥ ተቆጠሩ ማለት ነው። በሌላ ጦርነት ወፎች ሲያሸንፉ፤ አይጦች ከወፎች ጋር አብረው ለመሄድ ወሰኑ። ዛሬ ደሞ ወፍ ሆኑ ማለት ነው። ሲጠየቁም፤ “እኛኮ እንደእናንተ ነን ክንፍ አለን” አሏቸው። ውሎ አድሮ ወፎችና አራዊት ሰላም ፈጠሩ። አራዊቱም የሌት ወፎቹን “ከእኛ ጋር አይደላችሁም” አሏቸው። ወፎቹም፤ “ከአራዊት ጋር ተሰልፋችሁ ወግታችሁናል። ሂዱልን እናንተ አይጦች! እነሱ ያዛልቋችሁ!” ብለው አገለሏቸው። የሌሊት ወፎች ከአራዊትም ሆነ ከወፎች ጋር መኖር ስላልተፈቀደላቸው፣ ከወፎችና ከአራዊት የተውጣጣው የጋራ ኮሚቴ “ከዚህ በኋላ፣ የሌት ወፎች ሆይ! ሌሊት በአየር ትከንፋላችሁ (ትበርራላችሁ)።

ምንም ጓደኛ አይኖራችሁም። ከእንግዲህ ከሚራመድም ሆነ ከሚከንፍ ተለይታችሁ ትኖራላችሁ” በማለት ወሰነባቸው። ስለዚህ ይኸው እስከዛሬም ድረስ የሌሊት ወፎች በጨለማ ይክነፈነፋሉ፣ በጨለማ ዋሻዎችም ውስጥ ይኖራሉ። የሌት ወፎች እንደ ወፎች ክንፍ ቢኖራቸውም በዛፎች አናትና ቅርንጫፎች ላይ አርፈው አያውቁም። ማንም ቢሆን ስለሌሊት ወፎች አፈጣጠርና ምንነት ደንታ የለውም።

                                                              * * *

በህይወታችን፤ በተለይም በፖለቲካ ህይወታችን ውስጥ ሁለት ቦታ መርገጥ፣ ሁለት አቋም መያዝ፣ በተለይም በፈጠነ ግልብጥብጦሽ ውስጥ እንደእስስት መቀያየር፤ ማንነትን የማጣትን ያህል አደጋ አለው። በኢትዮጵያውያን ዘንድ፤ አርበኛ ነን እያሉ የባንዳ ሥራ መሥራት በታሪክም በኑሮም የእርግማን ዒላማ መሆን ነው። “ጠላትማ ምን ጊዜም ጠላት ነው አስቀድሞ መግደል አሾክሿኪውን ነው” የሚለው የፉከራና የሽለላ ግጥም ያለዋዛ አልተገጠመም። ይሄ ግጥም፤ አይጥ ነው ብለው አቅርበውት የሌሊት ወፍ ሆኖ ለሚገኘውና፤ የሌሊት ወፍ ነው ብለው ሲያቀርቡት አይጥ ሆኖ ለሚገኝ ግለ-ሰብ፤ አልፎ ተርፎም ለሚያንሿክክና ለሚያሾከሹክ ሥራዬ ተብሎ የተፃፈ ሳይሆን አይቀርም። “የአድር - ባይነት ዥውዥው መቼም ማቆሚያ የለውም” ይላል ሌኒን። ዕውነት ነው። መወዛወዙ በራሱ ቢቀር ባልከፋ። ግን ወዲህ ሲመጣ ካንዱ ሲላተም፣ ወዲያ ሲሄድ ከሌላው ሲላተም ጦሱ ለሰው መትረፉ ነው ጣጣው።

ገጣሚና ፀሐፌ - ተውኔት መንግሥቱ ለማ፤ ስለ አንድ ሚስቱ ስለምትደበድበው ባል ሲያወሱ፤ “ሰውዬውን ሚስቱ በትግል ጥላው፤ እላዩ ላይ ተቀምጣ በቡጢ ስታነግለው፤ ጐረቤት ይደርሳል። “ምነው ምን ተፈጠረ?” ይላል ጐረቤት። ይሄኔ ባል፤ የሚስቱን የበላይነትና ነውሩን አለመቀበሉን ለጐረቤቶቹ ለማስረዳት፤ “እስካሁን ከላይ ነበርኩኝ አዲስ ግልብጥ ነኝ! አዲስ ግልብጥ ነኝ!!” እያለ ጮኸ። አቶ መንግሥቱ ይሄን ጨዋታ ያመጡት፣ ባገራችን አዲስ መንግሥት መጥቶ ሁሉም “አሸወይናዬ” ማለት ሲጀምር ነው። ያኔ እንግዲህ “ስለ አዲሱ መንግሥት ለምን አትፅፉም?” ተብለው ሲጠየቁ፤ “እኔ አዲስ ግልብጥ አይደለሁማ!” ባሉበት ወቅት ነው። አዲስ ግልብጥ መሆንና በየጊዜው መገለባበጥ የአንድ ሣንቲም ሁለት ገፅታዎች ናቸው። ከለየለት አድርባይነት ተለይተው አይታዩም። ከአንድ ፓርቲ ወጥቶ ለሌላ ፓርቲ መገበር አድር ባይነት ነው። ከአንድ መንግሥት ወጥቶ ለተቃራኒው መንግሥት እጅ ሰጥቶ ማገልገልም የአድርባይነትን ትርጉም ያሟላል። ከሁሉም በላይ ግን በልብ ማመንዘር ይከፋል። ከዚህ ይሰውረን። ከሀገራችን ችግሮች አንዱ፤ “ወደቀ ሲባል ተሰበረ” ማለታችን ነው። እንዲህ ካልሆነ ሞተን እንገኛለን ብለን ስናበቃ ያ ጉዳይ ከተከወነ፤ አዲስ ቦቃ ልናወጣለት ደሞ ሌላ ፀጉር ስንጠቃ እንጀምራለን።

ደግን ደግ ክፉን ክፉ ማለት መቻል ትልቅ ፀጋ ነው። እርግጥ፤ ዝም ማለትም ሌላው ፀጋ ነው። ቃል በማይከበርበት፣ ፕላን በወግ በማይተገበርበት አገር፣ “ካልታዘልኩ አላምንም” ማለታችን ትክክል መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ፤ ለውጥን ግን በውል ማስተዋል ተገቢ ይሆናል። “ውሃ ከዚህ ቀን እስከዚህ ቀን ድረስ ይጠፋል” ብሎ ቀድሞ ማሳወቅ፣ ውሃ አጠራቅሙ ማለት በትክክለኛ መረጃ አሰጣጥ ማመን ነው። በ ስልክም፣ በ መብራትም፣ በ ምርጫም፣ በ ሹም - ሽ ርም ወ ዘተ አ ስቀድሞ መረጃ እንድናገኝ ቢደረግ መተማመን ይበረክታል። ማንኛውም ወገናችን፤ የመከላከያ ባለስልጣን ይሁን የክልል፣ የጠቅላይ ሚኒስትር ቀራቢ ይሁን ተራ ማሪ፤ ሙስና ከፈፀመ ሙሰኛ ነው! መረጃውን ማግኘትም መብታችን ነው፡፡ በተግባር ምን ማለት እንደሆነ በየቤቱ የሆነውን መቃኘት ነው። መረጃ መስጠት የመሻሻል ምልክት መሆኑን ግን በተቀዳሚ ማድነቅ መልካምነት ነው። ተግባሩ ካረካን መልካም። ውሸት ከሆነ ግን “አርሬ አይተኸኝ ነው እንጂ እኔም ሸክላ ነበርኩ” ያለውን ጀበና በማስታወስ ቸግሮን ነው እንጂ አንታለልም ማለት ግድ ይሆናል።

“5ኛው “ደስታ ለእናቴ 2005” የእናቶች ቀን፣ ነገ በካፒታል ሆቴል ከዘጠኝ ሰዓት ጀምሮ እንደሚከበር “ሱባ 16 ኢቬንትስ” አስታወቀ፡፡ በበዓሉ ላይ ታላቅ ሥራ የሰሩ ኢትዮጵያውያን እናቶች ሽልማት እንደሚበረከትላቸውና በተለያዩ ስፍራዎች በችግር ላይ ያሉ እናቶችን ለመደገፍ እንደታሰበ ተገልጿል፡፡

በኩል ፊልም ፕሮዳክሽን የተሰራው “አይራቅ” የተሰኘ ሮማንስ ፊልም፤ ነገ በአዲስ አበባና በአዳማ ከተሞች ይመረቃል፡፡ ፊልሙ በመጪው ሰኞ በአዲስ አበባ አቤል ሲኒማ በ11 ሰዓት እንደሚመረቅም አዘጋጆቹ ጠቁመዋል፡፡ በፊልሙ ሥራ ላይ ደራሲ በሀይሉ ዋሴ (ዋጄ)፣ ፕሮዲዩሰርና ዳይሬክተር ፍቅረየሱስ ድንበሩ የተሳተፉበት ሲሆን ማህደር አሰፋ፣ ሚካኤል ሚሊዮን፣ መስፍን ኃይለየሱስ እና ሌሎችም ተውነውበታል፡

ለሦስት ወራት በተለያዩ የላቲን ዳንሶች የሰለጠኑ የቡድን ዳንሰኞች፤ ዛሬ በክለብ H2O እንደሚመረቁ የማሰልጠኛ ማዕከሉ ኃላፊ ቢ-ላቲኖ አስታወቀ፡፡ የዳንስ ተመራቂዎቹ በጠቅላላ 156 ሲሆኑ ምረቃው ለ26ኛ ጊዜ የሚካሄድ እንደሆነ ታወቋል፡፡

34ኛው ግጥም በጃዝ የፊታችን ረቡዕ ከ11፡30 ጀምሮ በራስ ሆቴል እንደሚቀርብ አዘጋጆቹ አስታወቁ፡ ገጣሚ ነቢይ መኮንን፣ አርቲስት ተፈሪ አለሙ፣ አርቲስት ግሩም ዘነበ፣ ገጣሚ በረከት በላይነህና ሌሎችም ሥራዎቻቸውን ያቀርባሉ ተብሏል፡፡ የመግቢያ ዋጋ በነፍስ ወከፍ 50 ብር ነው፡፡

    በደራሲ ገብረክርስቶስ ኃይለስላሴ የተዘጋጀው “የሉሲ ከዋክብትና ሌሎችም” የተሰኘ የልጆች መልካም ሥነምግባር ማስተማርያ መፅሐፍ ታትሞ ለንባብ በቃ፡ አንጋፋው ደራሲ ኃይለመለኮት መዋዕል፣ በመጽሐፉ ጀርባ ላይ በሰጠው አስተያየት፤ “በየምዕራፉ የተካተቱት ጣፋጭ ታሪኮች ለልጆችም ሆነ ለአዋቂዎች ሰፊ ትምህርት ይሰጣሉ፡፡ ግብረገባዊነትንና መልካም ዜግነትንም ያላብሳሉ” ብሏል፡፡ “ቀደም ሲል ከጓደኛቸው ጋር ያሰናዱት “ናብሊስ” የተሰኘ የመልካም ሥነምግባር መጽሐፍ፤ ከ5ኛ እስከ 8ኛ ክፍል ላሉ ተማሪዎች፣ የሥነምግባርና የሥነ ዜጋ ትምህርት ማጣቀሻ ሆኖላቸዋል” ብለዋል - ደራሲው በአዲሱ መጽሐፋቸው መግቢያ ላይ፡፡ መጽሐፉ በ30 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡ ደራሲ ገብረክርስቶስ፤ ከዚህ ቀደም “ቅንጅት ከየት ወደየት”፣ “እምዬ” የተሰኘ የረዥም ልብወለድ፣ “በፈተናና በጥረት የታጀበ ስኬት” የሚል የህይወት ታሪክ እና “መቀናጆ” የሚል ርዕስ ያለው የግጥም መድበል ለአንባቢያን አቅርበዋል፡፡

Saturday, 10 May 2014 13:11

አዳዲስ መፃህፍት

የመፅሃፉ ርዕስ - የግንኙነት ጥበብ ሥነ-ልቦናዊ ገፅታ
ደራሲ - አለማየሁ ፀሃዬ
የምረቃ ሥፍራ - የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መፃህፍት ኤጀንሲ
ሰዓት - ጠዋት 3፡30  
*            *            *
የመፅሃፉ ርዕስ - አቤቶ ኢያሱ፤ አነሳስና አወዳደቅ
ደራሲ - አጥናፍሰገድ ይልማ
የምረቃ ሥፍራ - ጣይቱ ሆቴል
ሰዓት - ከጠዋቱ 3 ሰዓት
*            *            *
የመፅሃፉ ርዕስ - ሁለት ሶስት መልክ
ደራሲ - ሮዝ መስቲካ
ጭብጥ - እርግዝናና ልጅ ማሳደግ
የምረቃ ሥፍራ - ብርሃን ባህላዊ መዝናኛ ማእከል
ሰዓት - ከጠዋቱ 4 ሰዓት
*            *            *
የመፅሃፉ ርዕስ - የሙስና ወንጀልና የክርክር ሥነ-ሥርአት
ደራሲ - አበበ አሳመረ
ጭብጥ - ሙስናና የክርክር ስነ-ስርአቶች
ዋጋ - 59 ብር ከ 90

ህገወጥ መድሃኒቶችን ለመቆጣጠር የሚያስችል መሣሪያ ለጤና ጥበቃ ሚ/ር አበርክቷል
በህክምና፣ በመድሃኒትና በኬሚካል ዘርፍ አዳዲስ ምርቶችን በማቅረብ የሚታወቀውና ዋና መ/ቤቱ በጀርመን አገር የሆነው መርክ የተሰኘው ድርጅት በኢትዮጵያ ሥራ ጀመ፡፡ ይህ በአዲስ አበባ ከተማ የተከፈተው አዲስ ድርጅት ሱዳንን፣ ኢትዮጵያንና ፈረንሳይኛ ተናጋሪ የሆኑ የአፍሪካ አገሮችን የሚየገለግልና በቀጠናው የመጀመሪያው ማዕከል ነው ተብሏል፡፡
ድርጅቱ በትሮፒካል አካባቢዎች እምብዛም ትኩረት ባልተሰጣቸውና እንደ ቢልሀርዚያ ያሉ አደገኛ በሽታዎችን ለማስወገድ በሚደረገው ጥረት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚኖረውም የድርጅቱ ሃላፊዎች ከትናንት በስቲያ በሸራተን አዲስ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ አስታውቀዋል፡፡
ድርጅቱ በመሠረተው የዓለም አቀፍ ፋርማ ሄልዝ ፈንድ ፕሮግራም ስር ሁለት አነስተኛ ላብራቶሪዎች ለጤና ጥበቃ ሚ/ር ያበረከተ ሲሆን መሣሪያዎቹ ህገወጥና የጥራት ደረጃቸውን ያልጠበቁ መድሃኒቶችን ለመቆጣጠር የሚያስችሉ መሆናቸውም ተገልጿል፡፡
መርክ በጀርመን አገር በ1968 ዓ.ም ጀምሮ የሚሰራ በህክምና፣ በመድሃኒትና በኬሚካል ዘርፍ የተሰማራ አንጋፋ ኩባንያ ነው፡፡

Saturday, 10 May 2014 12:32

ውሀና ጠቀሜታዎቹ

ከመተኛትዎ በፊት አንድ ብርጭቆ ውሃ ይጠጡ፡፡ ስትሮክን እና የልብ ህመምን ለመከላከል ይረዳዎታልና
ጠዋት ከእንቅልፍዎ እንደተነሱ 2 ብርጭቆ ውሃ ከጠጡ ውስጣዊ የሰውነት አካላትዎን ለማነቃቃት ያግዝዎታል፡፡
ሻወር ከመውሰድዎ በፊት አንድ ብርጭቆ ውሃ የሚጠጡ ከሆነ ከፍተኛ የደም ግፊትን ለመከላከል ይጠቅሞታል፡፡
ከምግብ በፊት አንድ ብርጭቆ ውሃ መጠጣት ለምግብ መንሸራሸር ይረዳል
ምግብ ከመመገብዎ 30 ደቂቃ በፊት በቂ ውሃ ይጠጡ፡፡ ብዙ ባለመመገብ የሰውነት ክብደትዎን ለመቀነስ እንዲችሉ ያግዞታል፡፡

የጓደኛዎን ወይም የጐረቤትዎን የፌስቡክ “ፓስወርድ” ለማግኘትና ገመናውን ወይም ሚስጥሯን መበርበር ይፈልጋሉ?

ቀላል ነው፡፡ አንድ መስመር በማትሞላ ጽሑፍ የልብዎን ማድረስ ይችላሉ፡፡ አንድ ደቂቃ አይፈጅም፡፡ “ኮፒ” ከዚያ

“ፔስት” ማድረግ ብቻ ነው ከእርስዎ የሚጠበቀው። ከሁለት ሰዓት በኋላ፤ የጓደኛዎ ወይም የጐረቤትዎ ፓስወርድ እጅ

ይገባል…
በኢንተርኔት የተሰራጨው መልዕክት አጭርና ግልጽ ነው፡፡ በዚሁ መልዕክት የተማረኩ ብዙ ህንዳዊያን ወጣቶች በሁለት

አቅጣጫ የሚመነዘር ትርጉም እንዳለው ልብ አላሉትም፡፡ የሰዎችን ፓስወርድ በቀላሉ መስረቅ ትችላለህ - ይሄ አንደኛው

ትርጉም ነው፡፡ ሌሎች ሰዎች ያንተን ፓስወርድ በቀላሉ መስረቅ ይችላሉ፡፡ ይሄንን ሁለተኛ ትርጉም ልብ ለማለት ጊዜና

ፍላጐት ያልነበራቸው በሺ የሚቆጠሩ ህንዳዊያን፤ የጓደኞቻቸውን ወይም የስራ ባልረቦቻቸውን ገመና ለመበርበር

ቸኩለዋል። እውነትም ነገርዬው ቀላል ነው - “ኮፒ - ፔስት”… “ኮፒ - ፔስት”
በእርግጥም፤ ያቺ አንድ መስመር የማትሞላ ፅሁፍ የዋዛ አይደለችም፡፡ ፓስወርድ ለመስረቅ ተብላ የተቀመመች ናት፡፡

ግን…እዚህ ላይ ነው፤ ታሪኩ ድንገት የሚታጠፈው - “ሰርፕራይዝ” እንደሚባለው፡፡
“ኮፒ - ፔስት” ቀላል ቢሆንም፤ ኮምፒዩተራቸው ምን እያደረገ እንደሆነ አያውቁም። ፓስወርድ እየተሰረቀ ቢሆንም፤

ከሌላ ሰው ተሰርቆ እየመጣላቸው አይደለም፡፡ ከሁለት ሰዓት ጥበቃ በኋላ ምን እንደሚፈጠር ለማየት ነው የሚጠብቁት።

የራሳቸው ኮምፒዩተር፤ የራሳቸውን የፌስቡክ ፓስወርድ አፈላልጐ ለማግኘት፤ ከዚያም ያንን ፓስወርድ ወደሌላ ሰው

አድራሻ ለመላክ ትንሽ ጊዜ ያስፈልገዋል፡፡ ለካ፣ የሌላ ሰው ፓስወርድ ለመስረቅ ሳይሆን፣ የራሳቸው ፓስወርድ እንዲሰረቅ

ነው በፈቃደኝነት የተባበሩት፡፡ “አጭር ምጥን ብላ የተቀመመችና የተራቀቀች ስርቆት” ይሉሃል እንዲህ ነው፡፡ አንድ ሰው

የሆነ ጊዜ ላይ የፈጠራትና ያሰራጫት ዘዴ ናት፡፡ ከዚያ በኋላማ የሆነ ቦታ ሆኖ፣ በጥቂት ሰዓታት ውስጥ በሺ የሚቆጠሩ

የፌስቡክ ፓስወርዶች በአድራሻው እየተላኩ ፓስወርዶችን መሰብሰብ ነው፡፡
ከጥቂት ወራት በፊትም በተመሳሳይ የማታለያ ዘዴ የፓስወርድ ስርቆት እንደተካሄደ የገለፀው ገልፍ ኒውስ እንደሚለው፤

100ሺ ያህል የፌስቡክ ደንበኞች ፓስወርድ ተሰርቆባቸዋል፡፡ ቁምነገሩ ግን፤ እበላለሁ ሲሉ መበላት፤ እነጥቃለሁ ሲሉ

መነጠቅ ይኖራልና እንጠንቀቅ የሚል ነው፡፡
ከሰሞኑ ከወደ ፊሊፒንስ የወጣውም ጉድ ጥንቃቄ ያስፈልገዋል፡፡ በፌስቡክ አለም፤ ማን ምን እንደሆነ በእርግጠኛነት

ለማወቅ ያስቸግራል። ለዚያም ነው፤ በእውነተኛው አለም በሰው ፊት የማንናገራቸውና የማናደርጋቸው ነገሮች፤ በፌስቡክ

አለም ለመናገርና ለማድረግ ብዙዎች የሚደፋፈሩት። ስኮትላንዳዊው ታዳጊ፣ በፌስቡክ የአንዲት ቆንጅዬ ፎቶ በማየት

ተማርኮ ነው ጓደኝነት (ግንኙነት) የጀመረው፡፡ ብዙም ሳይቆይ የግል ወሬ ማዘውተር መጣ፡፡ ፎቶዎችን ተራ ፎቶ ሳይሆን

ከላይም ከታችም አጋልጠው የሚያሳዩ ፎቶዎችን ተለዋውጠዋል። መኝታ ቤት ውስጥ በወሲብ ጊዜ የሚያጋጥሙ አይነት

ወሬዎችንም ለምደዋል፡፡
ይሄ ሁሉ የሆነው በአጭር ጊዜ ውስጥ ነው፡፡ ለታዳጊው ስኮትላንዳዊ ሰማይ ምድሩ የተገለባበጠበትም በአጭር ጊዜ

ውስጥ ነው። “ገንዘብ ካላመጣህ፤ ያ ሁሉ ያወራነውን ነገር በኢንተርኔት በፌስቡክ እለቀዋለሁ” የሚል ማስፈራሪያ

ደረሰው፡፡
“በጓደኝነት የፌስቡክ ግንኙነት የፈጠረው፤ ቆንጅዬ ፎቶ በማየት ከተማረከላት ሴት ጋር አይደለም፡፡ ሰዎችን

በማስፈራራት ገንዘብ ከሚዘርፉ የፌስቡክ ማፍያዎች ወጥመድ ውስጥ አስገብተውታል፡፡
የተጠየቀውን ገንዘብ ቢከፍል እንኳ አይለቁትም። በማፍያዎቹ ወጥመድ ተይዘው በማስፈራሪያ ገንዘብ የከፈሉ በርካታ

የፊሊፒንስ ወጣቶች፤ በአንድ ጊዜ አልተገላገሉም፡፡ እንደገና ገንዘብ እንዲያመጡ ይጠየቃሉ፡፡ ብዙዎቹ ሦስት አራቴ

ከከፈሉ በኋላ ነው፤ ማስፈራሪያው ማብቂያ እንደሌለው ገብቷቸው ለፖሊስ የተናገሩት፡፡ የፊሊፒንስ ፖሊስ ወደ 60

ገደማ የፌስቡክ “ማፊያዎችን” በመያዝ ሰሞኑን ፍ/ቤት አቅርቧል፡፡