Administrator

Administrator

የኢትዮጵያ ሴት ደራሲያን ማህበር ከኢትዮጵያባህል ማዕከል ጋር በመተባበር ባህላዊ ህክምናንና አገርበቀል ዕውቀቶችን በተመለከተ የተለያዩ መፃሕፍትየፃፉትን ደራሲ በቀለች ቶላን የሚዘክር ፕሮግራምባለፈው ረቡዕ በኢትዮጵያ ባህል ማዕከል አዳራሽ ያካሄደ ሲሆን በስራዎቻቸው ላይ የመነሻ ጽሑፍ ቀርቦም ውይይት ተካሂዷል፡፡ደራሲ በቀለች ቶላ የሴት ደራሲያን ማህበር አባል
እንደሆኑ ታውቋል፡፡

Saturday, 27 June 2015 09:41

የኪነት ጥግ

• ቤተሰባችን በጣም ድሃ ስለነበር እኔን
የወለደችኝ ጐረቤታችን ናት፡፡
ሊ ትሬቪኖ
• የአይጦች ውድድር ችግሩ…ብታሸንፍ እንኳ
ያው አይጥ ነህ፡፡
ሊሊቶምሊን
• በውሃ ላይ ብራመድ ኖሮ፣ ሰዎች መዋኘት
አይችልም ይሉኝ ነበር፡፡
ጆን ተርነር
• ስለእኔ የማነበውን አምኜ ብቀበል ኖሮ እኔም
ደፋርነቴን እጠላው ነበር፡፡
ዛሳ ዛሳ ጋቦር
• እውነቱ ምንድነው…በ30 ዓመታት ውስጥ
30 ፊልሞችን ሰርቻለሁ፡፡ ለ30 ዓመታትም
ሌሎችም ተጨማሪ ፊልሞችን ባለመስራቴ
ስተች ኖሬአለሁ፡፡
ደስቲን ሆፍማን
• በውብ ነገሮች መከበብ በመፈለጌ ሰዎች
“እማ ዝራው ናት!” ይሉኛል፡፡ ግን እስቲ
ንገሩኝ ማነው በዝባዝንኬ (ነገሮች) መከበብ
የሚፈልገው?
ኢሜልዳ ማርቆስ
• የዜና ዕረፍቴ ዘገባ በእጅጉ ተጋንኗል፡፡
ማርክ ትዌይን (ዜና ዕረፍቱ በጋዜጣ መዘገቡን
ሲሰማ የመለሰው
• ሥራዬን ስለወደዳችሁት የእናንተ ዕዳ አለብኝ
ማለት አይደለም፡፡
ቦብ ዳይላን
• ሆሊውድ ለመሳሳም 50ሺ ዶላር፣ ለነፍስህ
50 ሳንቲም የሚከፍሉህ ሥፍራ ነው፡፡
ማርሊን ሞንሮ
• በትያትር ዓለም የሚቆጨኝ ፊት ለፊት
ተቀምጬ ራሴን ለመመልከት አለመቻሌ
ብቻ ነው፡፡
ጆን ባሪሞር
• አንዳንዴ በጣም ጣፋጭ ከመሆኔ የተነሳ
እኔም ራሴ ሁኔታውን መቆጣጠር ይሳነኛል፡፡
ጁሊ አንድሪውስ
• ወሲብ እግዚአብሔር በሰዎች ላይ የፈጠረው
ቀልድ ነው፡፡
ቤቲ ዴቪስ
• በመድረክ ላይ ከ25ሺ ሰዎች ጋር ፍቅር
እሰራለሁ፡፡ ከዚያም ብቻዬን ወደ ቤቴ
እሄዳለሁ፡፡
ጃኒስ ጆፕሊን
• በኦሎምፒክ ሁለተኛ መውጣት ብር
ያስገኝልሃል፡፡ በፖለቲካ ሁለተኛ መውጣት
መረሳትን ያጐናፅፍሃል፡፡
ሪቻርድ ኤ.ም ኒክሰን

Saturday, 27 June 2015 09:40

የፍቅር ጥግ

• ባል የቤተሰቡ ራስ ሲሆን ሚስት ደግሞ
ራስን የሚያሽከረክረው አንገት ናት፡፡
ያልታወቀ ፀሐፊ
• ራስሽን ከመሆን የሚያደናቅፍ ግንኙነትን
አሜን ብለሽ አትቀበይ፡፡
ኦፕራ ዊንፍሬይ
• ወንዶች ሴቶችን የሚያገቡት ጨርሶ
አይለወጡም በሚል ተስፋ ነው፡፡ ሴቶች
ወንዶችን የሚያገቡት ይለወጣሉ በሚል
ተስፋ ነው፡፡ ሁለቱም ግን ማዘናቸው
አይቀርም፡፡
አልበርት አነስታይን
• በካሜራ ፊት ለበርካታ ጊዜያት ባልና ሚስት
ሆናችሁ ከተጫወታችሁ በኋላ ከካሜራ
ውጭ ባልና ሚስት ቀላል ነው፡፡
ኤሚ ያስቤክ
• ትዳር ወንድ ልጅ ሚስቱ እንደምትፈልገው
እንዲያደርግ ከሚፈቅዱ ጥቂት ተቋማት
አንዱ ነው፡፡
ሚልተን በርሌ
• ግሩም ትዳር የሚባለው እንከን የለሽ ጥንዶች
ሲገናኙ አይደለም፤ ፍፁም ያልሆኑ ጥንዶች
ከእነልዩነታቸው መኖርን ሲያጣጥሙ ነው፡፡
ዴቭ ሜዩሬር
• እውነታህ ከህልምህ የተሻለ ሆኖ እንቅልፍ
መተኛት ሲያቅትህ፣ ያኔ ፍቅር እንደያዘህ
ትገነዘባለህ፡፡
ዶ/ር ሴዩስ
• በትዳር ውስጥ ደስታን ማግኘት ሙሉ
በሙሉ የዕድል ጉዳይ ነው፡፡
Pride & Prejudice
• ሚስትህ እንድታዳምጥህ ከፈለግህ ከሌላ
ሴት ጋር አውራ፡፡ ያኔ ሁሉነገሯ ጆሮ
ይሆናል፡፡
ሲግመንድ ፍሩድ
• ቦርሳዬን ስመለከት ባዶ ሆነብኝ፡፡ ኪሶቼንም
ብፈትሽ ባዶ ሆኑብኝ፡፡ ልቤን ስመለከት ግን
አንቺን አገኘሁሽ፡፡ ያን ጊዜ ነበር ሃብታም
መሆኔን የተገነዘብኩት፡፡
ያልታወቀ ፀሐፊ
• ፍቅር አ ንድ ረ ዥም ጣ ፋጭ ህ ልም ሲ ሆን
ትዳር ከእንቅልፍ የመቀስቀሻ ደወል ነው፡፡
ምንጩ ያልታወቀ
• ስኬታማ ወንድ የሚባለው ሚስቱ ማጥፋት
ከምትችለው በላይ ገንዘብ የሚሰራ ሲሆን
ስኬታማ ሴት እንደዚያ ዓይነቱን ወንድ
ማግኘት የቻለች ናት፡፡
ላና ተርነር
• ትዳር ልክ ወደ ጦርነት እንደመሄድ ያለ
ጀብዱ ነው፡፡
ጂ. ኬ. ቼስቴርቶን
• ፍቅር፤ በትዳር ሊድን የሚችል ጊዜያዊ
እብደት ነው፡፡
አምብሮሴ ቢርስ
• ለደስተኛ የትዳር ህይወት ወንዶች ሁለት
ነገሮችን ልብ ማለት አለባቸው፡- ሲያጠፉ
በፍጥነት መናዘዝን ፣ ትክክል ሲሆኑ ዝም

በቀድሞ አጠራር በሲዳሞ ክ/ሀገር በቡሌ ወረዳ የተወለዱት ደራሲና ጋዜጠኛ ሽፈራው መንገሻ ባደረባቸው ህመም በአገር ውስጥና በውጭ በህክምና ሲረዱ ቆይተው ባለፈው ሰኔ 12 በ75 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩ ሲሆን በነጋታው የቀብር ሥነስርዓታቸው በቅዱስ ዮሴፍ ቤ/ክርስቲያን ተፈጽሟል፡፡
ለረዥም ዓመታት በተለያዩ የመንግስት መ/ቤቶች ያገለገሉት አቶ ሽፈራው፤ በማስታወቂያ ሚ/ር ፕሬስ መምሪያ የሳምንታዊው “የዛሬይቱ ኢትዮጵያ” ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ በመሆን ለብዙ ጊዜያት ማገልገላቸው ተገልጿል፡፡
ደራሲና ጋዜጠኛው የተለያዩ መፃህፍትን ለንባብ ያበቁ ሲሆን ከእነሱም መካከል ታሪክ ጠቀሶቹ “ህግ ያልገዛውን ነፃነት ሃይል ይገዛዋል” እና “የኢትዮጵያ የታሪክ ጉዞ እስከቀዳማዊ ኃ/ሥላሴ ዘመነ መንግስት” የሚሉት ይገኙባቸዋል፡፡
“የኦሾዊት ምስጢር” የተሰኘው የትርጉም ሥራና የፊልም ባለሙያው የበቀለ ወያ ታሪክ የሆነው “የትውልድ አርአያ”ም ከሚታወቁባቸው ሥራዎቻቸው መካከል ይጠቀሳሉ፡፡ ደራሲና ጋዜጠኛ ሽፈራው መንገሻ የ3 ልጆች አባት ነበሩ፡፡

Saturday, 27 June 2015 09:27

የግጥም ጥግ

ችጋር
አላፊ፣ አግዳሚው - ወጪና ወራጁ
የሰልፍ ተክተልታይ - ወደ ‘ሚሻው ሂያጁ
ነውና ምሳሌው፡-
እሾህ ለአጣሪው -ወንጀል ለፈራጁ፡-
ምስለተሰንካዮች - የሚግበሰበሱ
እንደ ምንጭ ሲፈልቁ - እንደ ‘ኋ ሲፈሱ
ቀለብ ሰፋሪያቸው ከቶ ማነው እሱ?
ሸክሎች ተሰብስበው አፈር እየላሱ፡፡
አንድስ‘ንኳ
በመስቀል ውዥንብር - በቁርባን ቱማታ
በመሃይም ቦታ፡-
የባልቴቶች ጌታ፡-
በግዝት ቅብጥርጥር፡-
በፍታት ድንግርግር፡-
ሚስጥረ ሥላሴ፤
ግዕዝ ወቅዳሴ፡-
በሰንበቴ ጉርሻ፤
በሙት ዓመት ቁርሻ
ባለትልቅ ድርሻ፡-
ከበሮ አስደግፈው አነጣጥረው በልክ፤
ወረብ አስተማሯት ውሽማዬን ብልክ
በመቋሚያ ሽብርክ፤ ቅዳሴ የ’ንብርክ፡፡
በካሣሁን ወ/ዮሐንስ
ከአማርኛ የግጥም መድብል የተወሰደ

Saturday, 27 June 2015 09:24

የፀሐፍት ጥግ

ረመዳን ወደ ገፅ 19 ዞሯል
• የአዲስ አድማስ ጋዜጣ ድረገጽን ባለፈው ዓመት በአጠቃላይ ከ80
ሚሊዮን በላይ ተመልካቾች ጎብኝተውታል፡፡
• ዘንድሮ ከጥር ወር እስከ መጋቢት አጋማሽ ባሉት ጊዜያት ብቻ ከ20
ሚሊዮን በላይ ጎብኚዎች የተመለከቱት ሲሆን በየወሩ በአማካይ
ከ6 ሚሊዮን በላይ ተመልካቾች አሉት፡፡
• እስካሁን የተጠቀሱት መረጃዎች የአገር ውስጥ ጎብኚዎችን ብቻ
የሚመለከቱ ሲሆን በተመሳሳይ ሁኔታ በአሜሪካ፣ በአውሮፓ፣
በአረብ አገራትና በሌሎች ዓለማትም በርካታ ሚሊዮን
ኢትዮጵያውያን የሚጎበኙት ተወዳጅ ድረ-ገጽ ነው!
• ሦስት ዓለም አቀፍ ተቋማት በኢትዮጵያ የሚገኙ የዜና ድረ-ገጾችን
በተለያዩ መስፈርቶች አወዳድረው፣ የአዲስ አድማስ ድረ-ገጽን
ከቀዳሚዎቹ ሦስት ድረገጾች አንዱ መሆኑን መስክረውለታል፡፡
• በአሁኑ ሰዓት ትላልቅ የሪል እስቴት ኩባንያዎች፣ዓለም አቀፍ
የሞባይል ስልክ አምራቾች፣ታዋቂ የለስላሳ መጠጥ ፋብሪካዎችና
ሌሎችም---- በድረ ገጻችን ላይ እያስተዋወቁ ይገኛሉ፡፡
እርስዎስ? ለእርስዎም ቦታ አለን!!
ድረ ገጻችንን ይጎብኙት፡ www.addisadmass.news.com
ለተጨማሪ መረጃ፡- 0911-936787
ድርጅትዎን፣ ምርትዎንና አገልግሎትዎን
በርካታ ሚሊዮኖች በሚጎበኙት
ድረ-ገጻችን ያስተዋውቁ!
• አርታኢ እና አሳታሚ በሚሉት መጠሪያዎች
መካከል ያለውን ልዩነት ለማወቅ ከፈለግህ:-
አርታኢ ረቂቅ ጽሑፎችን የሚመርጥ ሲሆን
አሳታሚ አርታኢዎችን የሚመርጥ ነው፡፡
ማክስ ሹስተር
• መጽሐፍ በኪስ ውስጥ እንደሚይዙት
የአትክልት ሥፍራ ነው፡፡
የአረቦች አባባል
• ሥነፅሁፍን በራሱ እንደ ግብ አልቆጥረውም።
አንድ ነገር የማስተላለፊያ መንገድ ነው፡፡
ኢሳቤል አሌንዴ
• ፍፅምናን ብጠብቅ ኖሮ አንዲትም ቃል
ባልፃፍኩ ነበር፡፡
ማርጋሬት አትውድ
• ረቂቅ ሃሳብ ማስፈር፣ ጥናት ማድረግ፣
ስለምትሰራው ነገር ከሰዎች ጋር ማውራት
- ከእነዚህ ውስጥ አንዳቸውም ከመፃፍ
አይመደቡም፡፡ መፃፍ መፃፍ ነው፡፡
ኢ. ኤል ዶክቶሮው
• ለመኖር ታሪኮችን መተረክ አለብህ፡፡
ዩምቤርቶ ኢኮ
• ስድስቱ የመፃፍ ወርቃማ ህጐች፡- ማንበብ፣
ማንበብ፣ ማንበብ እና መፃፍ፣ መፃፍ፣ …
መፃፍ ናቸው፡፡
ኧርነስት ጌይንስ
• ፀሐፊነት በቋንቋ መስከርን ይጠይቃል፡፡
ጂም ሃሪሰን
• ለወጣት ፀሐፍት ምክር መለገስ ቢኖርብኝ፣
ስለ ጽሑፍ ወይም ስለራሳቸው የሚያወሩ
ፀሐፊዎችን አትስሟቸው እላቸዋለሁ፡፡
ሊሊያን ሄልማን
• በኪነጥበብ ቁጥብነት ሁልጊዜ ውበት ነው፡፡
ሔነሪ ጄምስ
• ማንነትህን እስክታውቅ ድረስ መፃፍ
አትችልም፡፡
ሳልማን ሩሽዲ
• በጥያቄ እጀምራለሁ፡፡ ከዚያም መልስ
ለመስጠት እሞክራለሁ፡፡
ሜሪ ሊ ሴትል
• ባልሆነ ቦታ ኮማ መደንቀር ያስጠላኛል፡፡
ዋልት ዊትማን
• ስለራስህ እውነቱን ካልተናገርክ ስለሌሎች
ሰዎች እውነቱን ልትናገር አትችልም፡፡
ቨርጂኒያ ውልፍ
• በውስጥህ ያለ ያልተነገረ ታሪክን ከመሸከም
የበለጠ ትልቅ ስቃይ የለም፡፡
ማያ አንጄሎ

“የአቶ አንዳርጋቸው አያያዝ የአገራቱን ግንኙነት አደጋ ላይ የሚጥል ነው”
- የእንግሊዝ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፍሊፕ ሃሞንድ

   የእንግሊዝ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፊሊፕ ሃሞንድ የሞት ፍርድ ተፈርዶባቸው በኢትዮጵያ በእስር ላይ የሚገኙት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ የሚገኙበት ሁኔታና አያያዛቸው፣ በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን ግንኙነት አደጋ ላይ የሚጥል ነው ሲሉ ለኢትዮጵያ መንግስት ማስጠንቀቂያ መስጠታቸውን ዘ ጋርዲያን ዘገበ፡፡
አቶ አንዳርጋቸው የቆንስላ ድጋፍ ማግኘት በማይችሉበት ወይም ይግባኝ የመጠየቅ መብት ባላገኙበት ሁኔታ በግልጽ በማይታወቅ ስፍራ ከሰው ተነጥለው ለብቻቸው መታሰራቸውን ያወገዙት ውጭ ጉዳይ ሚነስትሩ፣ የኢትዮጵያ መንግስት በግለሰቡ ጉዳይ ላይ አፋጣኝ ማሻሻል እንዲያደርግ ጠይቀዋል፡፡
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፊሊፕ ሃሞንድ ባለፈው ረቡዕ ከኢትዮጵያው አቻቸው ከዶክተር ቴዎድሮስ አድሃኖም ጋር በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ጉዳይ ዙሪያ በስልክ ባደረጉት ውይይት፣ ግለሰቡ እስሩን በህግ ለመቃዎም ዕድል ባላገኙበት ሁኔታ ከሰው ተነጥለው ላለፈው አንድ አመት በእስር ላይ መቆየታቸው ያሳስበኛል ብለዋል፡፡
አቶ አንዳርጋቸውን በየጊዜው ለመጎብኘት የምንችልበት ሁኔታ እንዲመቻችልን ተደጋጋሚ ሙከራ ብናደርግም፣ የኢትዮጵያ መንግስት ቃል ከመግባት ባሻገር ተገቢ ምላሽ ሊሰጠን አለመቻሉ አሳዝኖኛል ያሉት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ፣ የኢትዮጵያ መንግስት በተደጋጋሚ ላቀረብነው ጥያቄ ምላሽ አለመስጠቱ ተቀባይነት የለውም፣ በግለሰቡ ጉዳይ ዙሪያ ይህ ነው የሚባል መሻሻል አለመታየቱም ትልቅ ስፍራ የምንሰጠውን የሁለቱ አገራት የሁለትዮሽ ግንኙነት አደጋ ላይ የሚጥል ነው ሲሉ ለዶ/ር ቴዎድሮስ መናገራቸውንም ዘ ጋርዲያን ዘግቧል፡፡የእንግሊዝ የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር፣ ለአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ እና ለቤተሰባቸው የሚያደርገውን
የቆንስላ ድጋፍ ለወደፊትም እንደሚቀጥል ሃሞንድ ተናግረዋል፡፡የአቶ አንዳርጋቸው ጠበቃ ቤን ኩፐር በበኩላቸው፤ የእንግሊዝ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ግለሰቡ ከሰው ተነጥለው መታሰራቸውንና መጎብኘት እንዳለባቸው በማረጋገጥ እስሩን መቃወሙ አስደስቶናል፣ ይሄም ሆኖ የእንግሊዝ መንግስት አቶ አንዳርጋቸው ከእስር ተለቀው ወደ እንግሊዝ በመመለስ ከቤተሰቦቻቸው ጋር የሚገናኙበትን ሁኔታ እንዲያመቻችልን እንጠይቃለን ማለታቸውንም ዘገባው ጠቁሟል፡፡ የተመድ የስቃይ ጉዳዮች ምርመራ ልዩ ባለሙያ ጁዋን ሜንዴዝ በበኩላቸው፤ የአቶ አንዳርጋቸው ፅጌን አያያዝ በተመለከተ ምርመራ በማድረግ ላይ እንደሚገኙ
ለሁለቱም አገራት መንግስታት ማስታወቃቸውን ጋዜጣው ጠቁሟል፡፡

 ህጋዊ መታወቂያ ወይም የጉዞ ሰነድ አልያዙም ተብሏል
- የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከአ/አ ስንነሳ ህጋዊ ሰነድ ነበራቸው ብሏል

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአየርላንድ ርዕሰ መዲና ደብሊን በኩል ወደ አሜሪካ ሎሳንጀለስ የጀመረውን አዲስ በረራ ለማስመረቅ ባለፈው ቅዳሜ ከአዲስ አበባ በመነሳት ባደረገው ጉዞ፣ ተሳታፊ የነበሩ 7 ኢትዮጵያውያን መንገደኞች፣ አውሮፕላኑ ደብሊን አውሮፕላን ማረፊያ ላይ ሲያርፍ ወደ ኢሚግሬሽን ክፍሉ አምርተው ጥገኝነት መጠየቃቸውን አይሪሽ ኢንዲፔንደንት ትናንት ዘገበ፡፡ሁለት ህጻናትን ጨምሮ ጥገኝነት የጠየቁት 7 መንገደኞች በአየር ማረፊያ ጣቢያው ሲደርሱ ምንም አይነት መታወቂያ ወይም የጉዞ ሰነዶችን አልያዙም ነበር ያለው ዘገባው፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቃል አቀባይ ግን፣ በአውሮፕላኑ ውስጥ የነበሩ ተሳፋሪዎች በሙሉ ከአዲስ አበባ ሲነሱ ህጋዊ ሰነዶችን ይዘው ነበር፣ ስለ ጥገኝነት ጠያቂዎቹ የግል ጉዳይ ግን አስተያየት መስጠት አንፈልግም ብለዋል፡፡
አየር መንገዱ ላለፉት ከ40 በላይ አመታት ወደ አውሮፓ አገራት በረራ ሲያደርግ መቆየቱን ያስታወሱት ቃል አቀባይዋ፣ የምናጓጉዘው የተሟላ ህጋዊ የጉዞ ሰነድና ተገቢ ቪዛ ያላቸውን መንገደኞች ብቻ ነው ሲሉ መናገራቸውንም ዘገባው ገልጧል፡፡አንድ የአገሪቱ የህግ ክፍል ቃል አቀባይም የተለያዩ አገራት መንገደኞች በደብሊን አየር ማረፊያ ጣቢያ ሲደርሱ ጥገኝነት መጠየቃቸው የተለመደ የዘወትር ክስተት ነው፣ ባለፈው አመት ብቻ 221 መንገደኞች ለትራንዚት አርፈው ጥገኝነት ጠይቀዋል ብለዋል፡፡

- የፊሊፒንሳውያንን ያህል አሜሪካን የሚወድ የለም
- አሜሪካን በመጥላት የዮርዳኖስ ህዝቦች ይመራሉ

አሜሪካን በተመለከተ ያላቸውን አመላካት ለመለካከት ታስቦ በ39 የተለያዩ የዓለማችን አገራት ላይ የተሰራ አንድ ጥናት፣ ኢትዮጵያውያን አሜሪካን በመውደድ 3ኛ ደረጃ እንደያዙ መረጋገጡን ዘ ቢዝነስ ኢንሳይደር ዘገበ፡፡ፒው ሪሰርች ሴንተር የተባለው የምርምር ተቋም በሰራው በዚህ ጥናት፣ አሜሪካን አጥብቀው
በመውደድ ቀዳሚዎቹ የፊሊፒንስ ዜጎች ሲሆኑ፣ ጋናውያንና ኢትዮጵያውያን ይከተላሉ ብሏል፡፡በጥናቱ ከተካተቱ ፊሊፒንሳውያን መካከል 85 በመቶው አሜሪካን እንደሚወዱ ሲናገሩ፣ በጋና 83 በመቶ፣ በኢትዮጵያ ደግሞ 75 በመቶ የሚሆነው ህዝብ ለአሜሪካ ፍቅር እንዳለው ለማወቅ ተችሏል፡፡አሜሪካን በመውደድ ከሰሃራ በታች ያሉ የአፍሪካ አገራት ህዝቦች ቀዳሚውን ስፍራ እንደሚይዙ የጠቆመው ጥናቱ፣ አብዛኞቹ የአውሮፓ፣ የእስያና የላቲን አሜሪካ አገራት ህዝቦችም ለአሜሪካ በጎ አመለካከት እንዳላቸው ማረጋገጡን ጠቁሟል፡፡
በአንጻሩ ደግሞ አሜሪካን በመጥላት የዮርዳኖስ ህዝቦች ቀዳሚ ሆነው ተገኝተዋል፡፡ በጥናቱ ከተካተቱ የአገሪቱ ዜጎች 83 በመቶ ያህሉ አሜሪካን እንደማይወዱ ተናግረዋል፡፡ በሁለተኛ ደረጃ አሜሪካን የሚጠሉት ደግሞ ሩስያውያን ሲሆኑ በተለይ  ከቅርብ አመታት ወዲህ አሜሪካን የሚጠሉ ሩስያውያን ቁጥር እየጨመረ መምጣቱንም ጥናቱ አረጋግጧል፡፡

   ሰሞኑን ‹‹የዳኛቸው ሐሳቦች›› በሚል ርዕስ ያሳተምኩትን መጽሀፍ ተከትሎ በየቦታው አቧራ ተነስቶ ከርሟል፡፡ በርካቶችም የአቧራውን ጭስ ብቻ በመከተል ተቧድነዋል፡፡ እኔም እውነታው ብዙ ነገር ስለሚያናጋ ይህንን ጽሁፍ እስከምጽፍበት ጊዜ ድረስ አተካራ ውስጥ ላለመግባት ሞክሬያለሁ። በሌላ በኩል ከእውነታውና ከምጠብቀው ፍጹም የተቃረነ ነገር ስለገጠመኝ መደናገጤን መሸሸግ አይቻለኝም። ለዶክተር ዳኛቸው የነበረኝ አክብሮት፣ ያልተፈተሸ ፍቅር ብሎም አሁን ያሉበት ሁኔታም መልስ ከመስጠት እንድቆጠብ ካደረጉኝ ምክንያቶች ውስጥ ይጠቀሳሉ፡፡ ይሁን እንጂ ዝምታዬ አንዳንድ ሰዎችን ወደ ገደል ሲመራም አስተውያለሁ፡፡ ከዶክተር ዳኛቸው ጋርም አሁን ባለበት ሁኔታ በንግግር መግባባት አልቻልንም፡፡ በመሆኑም ነገሩ የህልውና ጉዳይ እየሆነና በሚያስደነግጥ ሁኔታ መልኩን እየቀየረ ስለመጣ በአቧራው ጭስ የተሸፈነውን እውነት
ለመገላለጥና ለተሰነዘሩብኝ እጅግ ሰቅጣጭ ውንጀላዎች መልስ ለመስጠት እግረ መንገዴንም በአንባቢዎቼ ላይ የተጋረዱትን ብዥታዎች ለማጥራት ስል ይህን ጽሁፍ ለማዘጋጀት ተገድጃለሁ፡፡ዛሬ ላይ ለውዝግብ የተዳረገው መጽሀፌን አስመልክቶ በግልጽ ከተናገርኩኝ አንድ ዓመት ከስድስት ወር አለፈው፡፡ ረቡዕ ታህሳስ 16 ቀን 2006 ዓ.ም በወጣችው “ኢትዮ-ምህዳር” ጋዜጣ ላይ ‹‹በዳኛቸው ላይ የተሰነዘረ መርህ አልባ ትችት›› በሚለው ጽሁፌ ውስጥ በሚከተለው መልኩ ነበር የስራዬን መጠናቀቅ የገለጽኩት፡- ‹‹... ዶ/ር ዳኛቸው ተነቦ የማያልቅ መጽሀፍ ነው፣ በሀሳቦቹ ውስጥም የኢትዮጵያን ችግሮች ማየትና መመርመር ይቻላል፣ ታሪክንም ሆነ ፍልስፍናን ጠንቅቆ ያውቃል፣... በግል ተነሳሽነት ሀሳቦቹን መርምሬ በመጽሀፍ መልክ እያዘጋጀኋቸው እገኛለሁ፡፡ ሌላው ወገን ደግሞ ከፈለገ ተቃራኒውን ሀሳብ አንስቶ በምክንያት መሞገት ይችላል፡፡... ›› ከላይ
የጠቀስኩት ጽሁፍ ለህትመት በበቃበት ቀን የዕለቱ ጽሁፌን ዶ/ር ዳኛቸውን ጨምሮ በዙሪያው የነበሩ ፕሮፌሰሮችና ወዳጆቹ በጣም እንደወደዱትና ከመጽሀፌ ጋር በተያያዘ ይፋ ያደረግሁት ነገርም እንዳስደሰታቸው ዳኛቸው እራሱ በደስታ ስሜት ውስጥ እንዳለ ነበር ደውሎ የነገረኝ፡፡ በወቅቱ እኔ ከአዲስ አበባ ውጪ ስለነበርኩ በተደጋጋሚ የተገናኘነው በስልክ ነበር፡፡ ጽሁፉንም በኢሜል እንድልክለት ጠይቆኝ ልኬለታለሁ፡፡ በቅርቡም ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከተባረረ በኋላ ለኢሳት ሰጥቶት የነበረውን ቃለ መጠይቅ እንዳስደምጠው በጠየቀኝ መሰረት፤ ይዤለት እቤቱ ሄድኩና ተገናኘን፡፡ ፕሮግራሙንም ይዤለት የሄድኩት በኮምፒውተሬ ነበር። ሰምቶ እንደጨረሰም እዛው በተቀመጥንበት ከኮምፒውተሩ ላይ ለህትመት ዝግጁ የሆነውን ስራ በጋራ እያሳለፍንና እያወራንበት አየነው፡፡ አይቶ እንደጨረሰም ካልተሳሳትኩኝ የአምቦ ዩኒቨርሲቲ መምህር የሆነ ወዳጁ ጋር ይደውልና እጅግ በተገረመ ስሜት ውስጥ ሆኖ ‹‹ስማ እንጂ... ያ ጉደኛ ልጅ አንዴት አድርጎ መሰለህ መጽሀፉን የሰራው! ... የሚገርም ነው መቼም እልሀለው፤ ስንገናኝ አወራሀለሁ....›› ነበር ያለው፡፡ እነዚህን ሁለት ማሳያዎች ዳኛቸው ከመጽሀፌ መውጣት ጋር ተያይዞ ከሰጠው ሀሳብ ጋር አነጻጽሩት፡፡ እነዚህን ነጥቦች የማነሳቸው ዳኛቸው ለሰጠው አስተያየትም ሆነ አብዛኞቻችሁ ለምታነሱት ጥያቄ ምላሽ እንዲሰጥልኝ እንጂ እኔ በግሌ የዳኛቸው ሀሳቦች ላይ ትንታኔም ሆነ ትችት ለመስራት የግዴታ እሱ ማየትና መፍቀድ አለበት ብዬ አላምንም፡፡ ምክንያቱም ብዙዎች መጽሀፉን ሳያነቡ ከድምዳሜ
ላይ እንደደረሱት መጽሀፉ የእሱ ሃሳቦች ስብስብ ሳይሆን በዳኛቸው ሀሳቦች ላይ ትንታኔ የሚያቀርብ
ነው፡፡ ይህንንም ዘግየት ብዬ በአስረጂ ማሳያ እመለስበታለሁ፡፡መጽሀፉ ገበያ ላይ ሊውል አንድ ቀን እስኪቀረው ድረስም አንድም ተቃውሞ ከዶክተሩ ተቀብዬ አላውቅም፡፡ መጽሀፉ ሊወጣ አንድ ቀን ሲቀረው ዳኛቸው ጋ ሁኔታውን ልነግረው ስደውል ደሴ መሆኑን ነገረኝ፡፡ እኔም የመጽሀፉ ህትመት መጠናቀቁን ላበስረው እንደደወልኩኝ ስገልጽለት፤ ‹‹ልጅ መሐመድ ባለፈው ሳምንት የቀጠርኩህ እኮ በጉዳዩ ላይ እንድናወራ ነበር፤... ፐብሊሸሬ ኮንሰርን አለው፤ ብናወራ ጥሩ ነበር፤...›› ካለኝ በኋላ በነጋታው እንደሚመለስ ገለጸልኝ፡፡ እኔም መጽሀፉን እቤት ይዤለት እንደምመጣ ከተነጋገርን በኋላ በሰላም ተለያየን፡፡ በነጋታውም ዶክተር ደወለና ‹‹ ፐብሊሸሬ ኮንሰርን አለው፤ ደጋግሞ እየደወለልኝ ነው ›› ሲል ከሌላው ጊዜ ጠንከር ባለ ድምጸት አወራኝ፡፡ እኔም በዚህ ስራ ላይ የሱ አሳታሚን የሚያሳስበው ነገር እንደሌለ ስገልጽለት፣ ‹‹እንዴት
ነው የማይመለከተው፤ የኔን ስብስብ እኮ ላሳትመው ነው›› ሲለኝ ‹‹እና ምን ችግር አለው? የኔ ስብስብ ስራ አይደል፤ አንተ አታውቀውም እንዴ?›› አልኩት፡፡ ‹‹ነው እንዴ! ስብስብ ነው ብለውኝ እኮ ነው›› ብሎ ሲለኝ እንደዛ በማሰቡና ሌሎችን በማመኑ ቅሬታዬን ገልጬለት ስልኩ ተዘጋ፡፡ ልብ አድርጉ! እንግዲህ እዚህ ሀገር ጠልፎ የሚጥለው ብዛቱ! መጽሀፉ ገና እኔ እጅ እንኳን ሳይገባ ስብስብ ስራ ነው እያሉ የሚያወሩ ነበሩ፡፡ መጽሀፉ እንደወጣም እቤቱ ሄጄ አስቀምጬለት ወጣሁ፡፡ መጽሀፉን ወደቤት ተመልሶ ገና ሳያገኘው አሁን የምንሰማውን ቅሬታ በዛኑ ዕለት ማታ መሰማት ጀመረ፡፡ ስለብቃቴ፣ መጽሀፌ መዉጣት፣... ያወደሱ አንደበቶች ወደዘለፋ ለመቀየር ጊዜና ማስተዋል አላስፈለጋቸውም፡፡ መጽሀፉን ሳያነቡ ወቀሳውን የሚያስተጋቡት ሌሎችም ነበሩ፡፡ ከዓመት በፊት የታወጀን እውነታ ካለማንበብ የተነሳ አለማወቅ አንድ ነገር ሆኖ ሳለ አሁንም መጽሀፉን ሳያነቡ በቲፎዞነት የተሰለፉ በርካቶች ነበሩ፡፡ በዚሁ አጋጣሚ በማስተዋል ውስጥ ሆናችሁ እኔንም ሆነ ሌሎችን ለማረጋጋት አስተውሎቱ የነበራችሁ ጥቂት የፌስቡክ መንደር ታዳሚዎች የምር ክብር ይገባችኋል፡፡ በቲፎዞነት ዓለም ውስጥ ለዋተታችሁ አብዛኞች ደግሞ ማስተዋልና ልቦናን ከክብር ጋር
ተመኘሁ!የጠሉትን መውረስ!ዳኛቸው አጥብቆ የሚነቅፋቸውን የስርዓቱ ተግባራት ለመፈጸም ጊዜ አልፈጀበትም። በኔው ስራ እኔኑ ከመጠየቅ ይልቅ ምርጫው ያደረገው ጀርባዬን ማጥናት ነበር፡፡ የጠላቸውንና የጠረጠራቸውን ሁሉ ከኔ ጋር ያጣብቃቸዋል፡፡ በውል እንኳን ከነመፈጠራቸው የማላውቃቸውን ሰዎች ስም እየጠራ ከጀርባህ እነከሌ ስላሉ እውነቱን አውጣ ማለቱን ተያያዘው፡፡ ከመጽሀፌ ጋር በተያያዘ ለተፈጠረው
ውዝግብ ዋነኛ ማጠንጠኛውም ይሄው ነጥብ ይመስለኛል፡፡ አንዳንዶችም ለክብራቸው በማይመጥን መልኩ መሰሉን የመሸታ ቤት ሀሜት ሰምተው፣ በአደባባይ የግለሰቦችን ክብር የሚነካና በወንጀልም ጭምር ሊያስጠይቃቸው የሚችል ጽሁፍ ጽፈዋል፡፡ የዚህ ከጀርባዬ የሌለን ሰው የመፈለጉ ሽኩቻ በግላዊ ፀብ፣ በፖለቲካዊ ጥንስስ፣ በማፊያዎቹ ኣሳታሚዎች ፍላጎት፣... ወዘተ ሊሆን ይችላል፡፡ እርግጠኛ ስላልሆንኩኝ ከጀርባ ስላለው ነገር አላወራም። የምፈልገው እከሌን እንጂ አንተን አይደለም፣ እናም መስክር፣ ... አይነት የፍረጃ ተግባሮች ሲተቹ የኖሩትን ስርዓት መንገድ መከተል ይመስላል፡፡ አስራት አብርሀምን እንኳን ካወቅሁት አንድ ወር አይሞላኝም፤ ግንኙነታችንም እሱ በሚካፈልበት ኤግቢሽን ላይ መጽሀፎቼን ለአንባቢም ሆነ ለነጋዴዎች እንዲሸጥልኝ ከማድረግ የዘለለ አይደለም፡፡ ሌላው ከነመፈጠራቸው የማላውቃቸው ሰዎች ስም እየተጠራልኝ ‹‹ከኋላህ አሉ!.. እራስህን ነጻ አውጣ... ሞኝ አትሁን...›› ዓይነት ማስፈራሪያ አዘል ንግግሮችም በጣም አስገራሚ ነበሩ። ከዚህም በላይ ለመጥቀስ የማይመቹ ዝርዝር ጉዳዮች እየተነሱ በማላውቀውና በማልጠብቀው አሳዛኝ ጉዳይ ውስጥም ተዘፍቄ ነው የከረምኩት፡፡ አስራትም ሆነ የሚጠሩልኝ ሰዎች የዶክተሩ እንጂ የኔ ወዳጆች አይደሉም፡፡ ከላይ ካነሳሁት ተግባር ጋር የሚመሳሰለው ዶክተሩ በዚሁ ጋዜጣ ላይ ‹‹መሐመድ ይቅርታ ጠይቆኛል...›› በሚል ያነሱት ነጥብ ነው፡፡ ዶክተሩን ወደ አደባባይ ያወጣቸውና ተቀባይነትም ያስገኘላቸው ከብርቱካን እስር ጋር ተያይዞ ይህንን የይቅርታ ጠይቆኛል አባዜ፣ በከፍተኛ ሁኔታ
ማውገዛቸውና ጠንካራ አስተያየትም ማቅረባቸው ነበር፡፡ ከሰሞኑ ግን ዶክተሩ ይህንኑ ተግባር እንደልጄ አይሀለው በሚሉኝ እኔ ላይ በከፍተኛ ጭካኔ ተግባራዊ አድርገውታል፡፡ መመስገንና መሸለም ሲገባኝ በከፍተኛ ሁኔታ የሞራል ኪሳራ የሚያደርሱ ጽሁፎችና ወሬዎች ሲያናፍሱ ከቆዩና በኋላም ክስ መስርተው ሲያበቁ በወጉ እንኳን ባልተስማማንበት የአንድ ቀን ግንኙነት ይቅርታ ጠይቆኛል አሉ፡፡ እኔ ዶክተሩን አስቀይሜ ይቅርታ ብጠይቃቸው እንኳን ካለን ቀረቤታ አንጻር እሳቸውን ደረት አስነፍቶ በአደባባይ የሚያስፎክር፣ የኔንም አንገት የሚያስደፋ አይደለም። የነበረውን ሁኔታ በግልጽ ላስቀምጠው፡፡ እኔና ዳኛቸው ከውዝግቡ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በአካል የተገናኘነው ባለፈው ሳምንት ረቡዕ ስድስት ኪሎ አካባቢ ካለ አንድ ግሮሰሪ ውስጥ ነበር፡፡
ግንኙነታችንም ከሳቸው በተነሳ ጥያቄ መሰረት ሚስጥራዊ እንዲሆን ብንስማማም በወቅቱ ያነሳናቸውን ጉዳዮች በተዛባ መንገድ እያነሱ ዛሬም ድረስ በስልክ የሚረብሹኝ ሰዎች አሉ፡፡ በወቅቱ ስንገናኝ የነበረው ሁኔታ ሚዲያው ላይ በሚራገበው መጠን ብዙም ውጥረት የበዛበት አልነበረም፡፡ በሂደት ሁለታችንም በሚያግባባን አንድ ነጥብ ላይ ማውራት ስላልቻልን ስሜቴ መረበሹ አልቀረም፡፡ ሆኖም ግን የምናወራው እንደ አባትና ልጅ ነበር፡፡ በኋላም በደረሰብኝ ነገር ሁሉ ስሜቴ ክፉኛ እንደተጎዳ፣ አስካሁን ከደረሰብኝ ጉዳት የባሰ ነገር በክሱም ቢሆን እንደማይገጥመኝ፣ ስራውንም ለገንዘብ ብዬ እንዳልሰራሁት፣ ወዘተ ካስረዳሁ በኋላ በዶክተሩ ፍላጎት እንዲወሰኑ ሁለት አማራጮችን አቀረብኩኝ። የመጀመሪያው አማራጭ እስካሁን የተበተነው መጽሀፍ የተበደርኩትንና መጽሀፉን ያሳተምኩበትን ወጪ ብቻ ከሸፈነ ቀሪዎቹን መጽሀፎች እንዲሰበሰቡ የሚል ሲሆን፤
ሁለተኛው አማራጭ መጽሀፉን ደግሞ የማሳተም ፍላጎት እንደሌለኝና አሁን የታተመው ግን ከኛ ቁጥጥርም ጭምር ዉጪ በመሆኑ ተሸጦ እንዳለቀ ለኔ የሚደርሰኝን ገንዘብ አምጥቼ ለዶክተር ልሰጥና፣ እሳቸውም በገንዘቡ ላይ የፈለጉትን ውሳኔ እንዲያሳልፉ የሚል ነበር፡፡ ይህንን በልመና ጭምር የታገዘውን አማራጭ ሳቀርብ አሁን የተፈጠረው አተካራ ማናችንንም እንደማይጠቅመን በማስረዳት ጭምር ነበር፡፡ በዚህ ላይ ለመወሰንም ለአርብ ጠዋት ቀጠሮ ይዘን ተሰነባበትን፡፡ የነበረው ነገር ይህ ነው፡፡ ገና ባልተቋጨ ጉዳይ ላይ ነው እንግዲህ “ይቅርታ ጠየቀኝ” በሚል መግለጫ የሰጡት። ታዲያ የቀጠሯችን ቀን አርብ ሲመጣ ከሳቸው በስልክ የደረሰኝ ውሳኔ ሳይሆን ቀደም ብዬ ከላይ ያነሳሁት የተጠናከረ ፍረጃ ነበር፡፡ ሌላውን ለማጥቃት እኔን መግደልም እንዴት
ምክንያታዊ እንደሚሆን አልገባኝም። እውነታውን በማስረጃ ለሚዲያው ፍጆታም ሆነ ሽያጭ ከኔ ይልቅ የዳኛቸው ፊት ገጽ ላይ መውጣት ሚዛን እንደሚደፋ እርግጥ ነው፡፡ ለዚህም ይመስላል ከሰንደቅ ውጪ የትኛውም ሚዲያ ዘገባውን ሲሰራ ወደኔ በመደወል እውነታውን ለማጣራት ያልሞከረው፡፡ ባለፈው ሳምንት በወጣው የአዲስ አድማስ ዜና ላይም ዶክተር ዳኛቸው የመጽሀፉ 95 ከመቶ የሚሆነው ሀሳብ ከሳቸው እንደተወሰደ ተናግረዋል፡፡ የሆነው ሆኖ አንባቢ በእውነታው መካከል ያለውን ልዩነት አይቶ፣ የራሱን ፍርድ ይስጥ፤ እኔ ግን እውነታውን በቁጥር አስደግፌ ላስፈር፡፡ መጽሀፌ 236 ገጾች አሉት፡፡ በነዚህ ገጾች ውስጥ የዶክተሩ ሀሳቦች አስፈላጊ በሆኑበት ቦታ ላይ በሩብ፣ በግማሽ እና በሙሉ ገጽ ላይ እንደወረዱ የሰፈሩባቸው ቦታዎች አሉ፡፡ እነዚህ እንደወረዱ የተጠቀምኳቸው የዶክተሩ ሀሳቦች ተደማምረው ወደ 76 ያህል ገጽ ናቸው፡፡ ልብ አድርጉ 236 ገጽ ካለው መጽሀፍ ውስጥ 76 ገጽ ምን ያህል ፐርሰንት እንደሚሆን አስቡት፤ ወደ 32 ከመቶ ገደማ ነው፡፡ ከዚህ በቀጥታ የዶክተሩን ሀሳብ እንደወረደ ካሰፈርኩበት 76 ገጽ ውስጥ ደግሞ ወደ 30 ያህል ገጽ የሚሆነው ከኔው ጋር የቃለምልልስ ቆይታ በነበራቸው ወቅት የሰጡኝ ሀሳብ ነው፡፡ በተቀረው ገጽ ላይ የሰፈሩት ሀሳቦች የኔው ትንታኔዎች፣ ማብራሪያዎች እና አቶ ጌታቸውን ጨምሮ የሌሎች ሰዎች አጋዥ ስራዎች ናቸው፡፡ ይህንን ቁጥር እሳቸው ካሉት 95 ከመቶ ጋር ማነጻጸር ነው እንግዲህ፡፡ ይህንኑ እውነታ በሌላ ተጨባጭ ማስረጃ ለማስቀመጥ ያህል ሌላ ማሳያ ላምጣ፡፡ በመጽሀፉ እስከ 27ኛው ገጽ ድረስ የሳቸውን ሀሳብ እንደወረደ የተጠቀምኩት ሁለት ቦታ ላይ ከራሴው ጋር ካደረጉት ቆይታ ውስጥ ነው፡፡ ሽፋኑም ተደምሮ በገጽ ሲገመት አንድ ገጽ ከግማሽ ነው፡፡ ... ከገጽ 30 እስከ 35 ድረስ አንድ ቦታ ላይ ሩብ ገጽ ያህል ከ “ኢትዮጵያን ማን ይታደጋት” ላይ በቀጥታ ተወስዶ የሰፈረ ሀሳብ አለ፡፡... እንዲህ አድርገን ስንደምረውና በተለይም ከብርቱካን ጋር በተያያዘ የጻፉት ጽሁፍ፣ ለሰራሁት ትንታኔ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ አብዛኛው ክፍል በመግባቱም ጭምር ነው ከላይ የጠቀስኩትን ያህል ቁጥር የመጣው፡፡ በመጨረሻም ከአንደኛው ገጽ ያልዘለለ ንባብና በስማ በለው በቲፎዞነት መሰለፍ ውጤቱን አደገኛ ያደርገዋል፡፡ መጽሀፉን ማንበብ ብቻ ወደትክክለኛው መንገድ ደርሰናል፡፡ አንብቦ ስራው አይረባም ማለት ይቻላል፡፡ ድምዳሜውን ለአንባቢያኑ መተው ይሻላል፡: በተረፈ ግን በቀሪ አተካራዎች ላይ ገብቶ መዋጀቱ ትንሹ እድሜዬ ሳይሆን በልበሙሉነት
የምናገርለት የሞራል ልዕልናዬ አይፈቅድልኝም፡፡ እውነቱ ይህ ነው! ትዕግስትም፣ ዝምታም፣
አክብሮትም ልክ አለው!!