Administrator

Administrator

 

 

 

              “መንግስት፤ እኔ ነኝ የአገሪቱ ደራሲ ይላል”

    ይኼንን ያለው አልበርት ካሙ ነው፡፡ አንድነት ግን በተጨባጩ አለም ሊገኝ የሚችል ነገር ሳይሆን ሲቀር፣ አርቲስቱ ተጨባጩን እውነታ በማፈራረስ ከፍርስራሹ ውስጥ የራሱን የምናባዊ አለም አንድነት እንዳለው አስመስሎ ያቀርበዋል፡፡ ይፈጥረዋል፡፡

“አንድነት በተለዋጭ አለም ይኸው እንዴት ውብ እንደሆነ” ብሎ ያቀርባል፡፡ እናም የፈጠረው አንድነት የተሳካ ከሆነ ተቀባይነት ያገኛል፡፡ የፈለገ ምናባዊ ቢሆንም ግን ፈጠራው  ቀድሞ ከነበረው የእውነታ አለም የራቀ አይሆንም፡፡ ከራቀ የሚረዳውን አያገኝም፡፡ ካላገኘ፤ አንድነቱ የቱ ጋ ነው? የሚል ጥያቄ ያስነሳል፡፡

ግን ተሳካለት እንበል፡፡ ማለትም የፈጠረው ምናባዊ ጥበብ አንድነትን በሰው እና በፈጣሪ መሀል ወይንም በሰው እና በማንነቱ … መሀል ያሉትን ቲዎሪያዊ ጥያቄዎች ሁሉ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ደፈነ፡፡ እና ምን ይከተል? ሲፈለግ የነበረው የፈጠራ ጥግ ተደረሰ ተብሎ ፍለጋው ይቆማል?

አይቆምም፡፡ የፈለገ አይነት ስኬታማ ድርሰት ቢዋቀር የሰው ልጅ የአንድነት ፍላጐት አይረካም። ደራሲው ራሱ እንኳን የመጨረሻው የውበት (አንድነት) ጥግን ነክቻለሁ ካለ በኋላ የራሱን መጨረሻ ለመብለጥ ሌላ ድርሰት ይጽፋል፡፡ ህይወቱ እስኪያከትም ድረስ ውድድሩን አይገታም። … የሚወዳደረው ከራሱ ጋር ነው፡፡ ወይንም ከራስ ወዳድነቱ ጋር፡፡

ምናልባት ጥበበኝነት ከራስ ወዳድነትም ጋር የሚጣመርበት ስፍራ ሊታየን የሚችለው እዚህ ላይ ሳይሆን አይቀርም፡፡

ማርሴል ፕሮስት፤ “In remembrance of the times past” በተባለው ዐብይ እና ትልቅ ስራው አንድነትን የፈለገበት መንገድ ወደራሱ የትዝታ አለም በመመነን ነው፡፡ ተጨባጩን አለም አፈራርሶ የእሱን ጠባብ የውስጥ ግዛት አለምን አሳክሎ በማብዛት ታላቅ ፈጠራን ሰራ፡፡ ከሰው ልጅ ጋር ራሱን “አንድ” ለማረግ የመረጠው መንገድ… የሰው ልጅን ሁሉ ወደ እሱ አተያይ በመቀየር ነው፡፡

ማርሴል ፕሮስት፤ ያደረገውን ያላደረገ ፈጣሪ በመሰረቱ የለም፡፡ የአንድነት ብቸኛ ፍቺ ነው የምንለው የሙሉኤ ኩሉው እውነታ ደራሲ (እግዚአብሔር) እንኳን… ሁሉንም ነገር የከወነው ከራሱ አልፋ እና ኦሜጋዊ አተያዩ አንፃር አይደል? የአንድነት ፍላጐት ከራስ ፍላጐት አንፃር እስከሆነ ድረስ ወደ ጠቅላይ ስምምነት የሚያደርስ ፈጠራ ሊኖር አይችልም፡፡

በዚህ ምክንያት የውበት ፍቅር፣ የእውነት ፍቅር ወይም የአንድነት ፍቅር ከራስ ወዳድነት ፍቅር ጋር ያልተከለሰበት ውበት ተሰርቶ  አያውቅም፡፡

ለምሳሌ ፍቅር ሁሉ አንድነት ነው፡፡ ወንድ እና ሴት አንድ ለመሆን ወደ ፍቅር ይገባሉ፡፡ ግን አንድነታቸው ተዋረድ አለው፡፡ በተለምዶ ወንዱ አንድ አድራጊው ሀይል ነኝ ብሎ ሊያምን ይችላል፡፡ “የእኔ ነሽ … ባለቤትሽ ነኝ” ይላታል‘ኮ አፍ አውጥቶ። የፍቅራችን የአንድነት ደራሲ እኔ ነኝ ማለቱም ነው፡፡ ነገሩ ፍቅር ነው፣ ውበት ነው፤ ግን ውበቱ የተቀረፀበት አንፃር አለው፡፡

ማን ነበረ፤ “We are too small in mind and body to possess other people without pride or to be possessed without humiliation” ያለው እንደዚያ ነው ነገሩ፡፡

ነገሩ ደግሞ ሰው የሚፈጥራቸው ጥበባዊም ይሁን መንግስታዊ አንድነቶች ውስጥ ግዙፍ እውነት ሆኖ ይገኛል፡፡ “እኔ ነኝ የሀገሪቷ ደራሲ ይላል” መንግስት፡፡ ባልዬው፤ “እኔ ነኝ የቤተሰቡ እራስ” እንደሚለው፡፡

የመጽሐፍ ደራሲውም፤ “እኔ ነኝ የድሮውን እውነታ ፈታትቼ በአዲስ መልክ ፈጥሬ ያዋቀርኩት” ይላል፡፡ በራሱ ለመኩራት ሲል ፈጠራውን የሚከውነውን ያህል የአንድነት ፍላጐትም በተፈጥሮው አድሮ ውበትን ለመጨበጥ ያነሳሳዋል፡፡ ግን “እኔ አንድነቱን ካልፈጠርኩት ሳይፈጠር ይቅር! ወይንም ቢፈጠርም ተፈጠረ ሊባል አይችልም” የሚለው ምክኒያት ዋናው የተግባሩ የመነሻ ምክንያት ሳይሆን አይቀርም፡፡

በአንድ ድርሰትም ሆነ በአንድ የመንግሥት አስተዳደር ጥንቅቅ ያለ የአንድነት ንድፍ ሊገኝ የማይችለውም ለዚህ ይመስለኛል፡፡ (ከመሰለኝ ደግሞ…!)

ህዝብና መንግስት መሀል ጭቆና የሚኖረው፣ መንግስት ራሱን እንደ ደራሲ ሲያይ ነው፡፡ መንግስትን የሚተካ ሌላ ደራሲ የሚነሳው ከበፊተኛው ድርሰት ራስ ወዳድነት ውስጥ ነው፡፡ ግን በዛው መጠን መዘንጋት የሌለበት አዲሱ ደራሲም አዲስ አንድነት ለማምጣት የሚጥረው ለህዝቡ ሲል ሳይሆን ከራሱ “Ego” (ፍላጎት) ተነስቶ ነው፡፡

ግን ማንም ደራሲ ቢመጣ፤ የቀደመውን ምናባዊ ድርሰት፣ በሌላ ምናባዊ አለም ቢለውጥ፣ ወይንም ተጨባጩን ቢሮክራሲ በሌላ አሻሻልኩ ቢል፣ ከራሱ እይታ አንፃር እስከሆነ ድረስ ጥቅሉ ውበት (አንድነት) አይጨበጥም፡፡

ባል ሚስቱ ጥላው ስትሄድ አልያም መንግስትን ህዝብ አልወድህም ሲለው…የፍቅሩ መቋረጥ ከሚቆረቁረው ይበልጥ ሚስት እሱን ትታው ሄዳ ሌላ ባል (ሌላ መንግስት) ማግኘቷ እንደማይቀር ማወቁ የስቃዩ እውነተኛ ምንጭ ነው፡፡

ብዙ የአንድነት አይነት አለ፡፡ ግን የራስ ወዳድነቱ አይነት አንድ ነው፡፡ “ሳዲስት” ከ “ማሶቺስት” ጋር አንድነት ይፈጥራሉ፡፡ ፍቅር ይመሰርታሉ፡፡ ህዝብን የሚሰድብ ደራሲን መጽሐፍ የሚገዛ፣ መሰደብ ከሚወድ ህዝብ … የገበያም ሆነ የመናበብ ትስስር ይፈጥራል፡፡ የፍቅር አይነት ነው፡፡ ሌላው ደግሞ እንክብካቤ እና ጥሩ ህይወት በምትፈልግ ሚስት እና ፍላጐቷን በሚያሟላ ባል መሀል የሚፈጠር አንድነት አለ፡፡ ግን አንድነቱ በጥል እና ባለመስማማት ይፈታል፡፡ አለመስማማት ማለት ሁለቱም የአንድነት መስራች አካሎች ራሳቸውን ማስቀደማቸው ግልፅ ሲወጣባቸው፣ አንድ የሚያደርጋቸው ነገር ሳያሳምን ሲቀር ነው፡፡

እስካሁን የተሰራው የሰው ልጅ የድርሰት መፅሐፍ ለምን አንድ ላይ ተደምሮ ትልቅ ውበት ማግኘት አልተቻለም? የሚል ጥያቄ ከመጣ መልሱ፡- የማንም የራስ ወዳድነት ንድፍ ከሌላው ጋር ቢደመር ትልቅ ራስ ወዳድነት እንጂ ትልቅ ውበት ወይንም ፍቅር አይወጣም፤ የሚል ይመስለኛል፡፡

ትልቅ ራስ ወዳዶች ትልቅ ጥበብን ይፈጥራሉ። በጥበቡ የሚስማማላቸው፣ በእነሱ እይታ መነፅር አለምን ለማየት ህዝቡ ወይንም ተደራሲያቸው እስከፈቀደላቸው ድረስ ሳይፈቅድ ሲቀር ሌላ ደራሲ የድሮውን አንድነት በራሱ አዲስ አተያይ ለውጦ እንዲያሳያቸው ይፈቅዳሉ፡፡ ሲፈቅዱ የወጣውን አውርደው የወረደውን አዲስ የአንድነት ደራሲ ያነግሳሉ፡፡

ትልቅ ራስ ወዳዶች ጥበብን ይፈጥራሉ፡፡ ራሳቸውን ከፈጣሪ፣ ከተፈጥሮ፣ ከስነምግባር ልዕለ ትርጉም ጋር ለማስተሳሰር ሲሉ፤ … ግን ለማሰር የሚሞክሩት በድርሰታቸው የደረሱትን ህዝብ ነው። ህዝብም ራስ ወዳድ ነው፡፡ ህዝብም ሰው ነው፡፡

ህዝብ ለመንግስት እንደ ሚስት ይመስላል፡፡ ባል ስልጣኑን ሲጭንባት ሚስት አሜን ብላ ትቀበላች፡፡ … ግን ጭነት ሲበዛባት ፍቅሯን (አንድነቷን) መጠርጠር ትጀምራለች፡፡ ጀምራ ከቀጠለች ባሏን ጥላ መሄዷ አይቀርም፡፡

ሚስቱ ጥላው የምትሄድ ባል፣ ህዝቡ ጥሎት የሚሄድ መንግስት ይበግናሉ፤ ይቃጠላሉ። የሚያቃጥላቸው ከህዝቡ ጋር የነበረው ፍቅር ከልባቸው አልወጣ ስለሚላቸው አይደለም፡፡ የሚያብከነክ ናቸው፡፡ ጥላ የሄደችው ሚስት ሌላ ባል ማግኘቷ እንደማይቀር በማወቃቸው ነው፡፡

በራስ ወዳድነት ላይ ተመስርተው የሚፈጠሩ አንድነቶች ሁሉ … አንድነት ሆነው የሚቆዩት ለተወሰነ ጊዜ ነው፡፡ የተወሰነው ጊዜ ሲያልቅ … ሁሉም ፈጣሪ ነን ባዮች ወደ ተራነት ይመለሳሉ። መንግስትም ይቀየራል፣ ትዳርም ይፈርሳል፣ የገነነ ድርሰትም ከመፅሐፍ መደርደሪያ ላይ ወርዶ በሌላ ግነት ይተካል፡፡ የአንድነት ፅንሰ ሀሳብ ገናና የሚሆነው … የግለሰብ ራስ ወዳድነትን መጠን ያህል ነው፡፡

 

 

 

“የሳጥናኤል ሳል ኢትዮጵያ” የህይወት ዛፍ” “ገነት” “ኢትዮጵያ” የሚል ርዕስ ያለውና በጋዜጠኛና ደራሲ ፍሰሓ ያዜ ካሳ የተጻፈው መጽሃፍ በያዝነው ሳምንት በገበያ ላይ ውሎ እየተሸጠ ይገኛል፡፡ መጽሃፉ የዓለም ሃያላን አገራትና መሪዎቻቸው በህብረት ሆነው በኢትዮጵያ ላይ ያነጣጠሩበትን ምክንያትና ዋነኛ ግባቸውን የሚተነትን ነው ያለው ደራሲው፤ 376 ገጾች እንዳሉትና በ80 ብር እየተሸጠ እንደሚገኝም ለአዲስ አድማስ ተናግሯል፡፡

ጋዜጠኛና ደራሲ ፍሰሐ ያዜ ካሳ ከዚህ ቀደም “የኢትዮጵያ የ5ሺህ ዓመት ታሪክ፣ ከኖህ እስከ ኢህአዴግ”፣ “ካልተዘመረለት እያሱ እስከተዘመረለት ኢህአዴግ” እንዲሁም “እኔና ቹ” የተሰኙ ሦስት መጽሃፍትን ለአንባቢያን አድርሷል፡፡

   ተቀማጭነቱ በአሜሪካ የሆነው ጣይቱ የባህል ማዕከል ያዘጋጀው “መንገድ” የተሰኘ የስነጽሁፍ ዝግጅት የፊታችን ረቡዕ በአዲስ አበባው አክሱም ሆቴል ትልቁ አዳራሽ እንደሚካሄድ ተገለጸ፡፡ከቀኑ በ10፡30 ሰዓት ጀምሮ በሚካሄደው በዚህ የስነጽሁፍ ዝግጅት ላይ የተመረጡ ግጥሞች፣ ወጎች፣ የፍቅር ደብዳቤና አጭር ልቦለድ የሚቀርብ ሲሆን ባለሙያዎችም በአገራችን ወቅታዊ የስነ ግጥም እንቅስቃሴ ዙሪያ ሙያዊ አስተያየት እንደሚሰጡ ይጠበቃል፡፡ የሥነጽሁፍ ቤተሰቦች የጥበብ ድግሱን በነጻ እንዲታደሙት አዘጋጆቹ ጥሪያቸውን አቅርበዋል፡፡ ጣይቱ የባህል ማዕከል፤ የአገሪቱን የስነጽሁፍ እድገት ማገዝ፣ ጥበብን ከጥበብ ወዳጆች ጋር ማገናኘት፣ ወጣት ጠቢባንን ማበረታታትና አንጋፋ የጥበብ ሰዎችን ማክበርና መዘከርን አላማው አድርጎ እየተንቀሳቀሰ እንደሚገኝም ለማወቅ ተችሏል፡፡

 

Tuesday, 26 May 2015 08:43

“ዙቤይዳ”

     3ኛው ዕትም ሊወጣ ነው ተባለ

     በደራሲ አሌክስ አብርሃም ተፅፎ በቅርቡ ለአንባቢያን የደረሰው “ዙቤይዳ” የተሰኘው የአጭር ልብወለዶች መድበል የመጀመሪያና ሁለተኛ ዕትሞች ተሸጠው ማለቃቸው ተገለፀ፡፡ ሦስተኛው እትምም ከነገ በስቲያ ለገበያ እንደሚበቃ ለማወቅ ተችሏል፡፡ መፅሐፉ በአሜሪካ ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን በዌብ ሳይት አማካኝነት እንደሚሸጥም ደራሲው ጠቁሟል፡፡ 22 ታሪኮች የተካተቱበት መጽሐፉ፤ በ59 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡

አሌክስ አብርሃም ከዚህ ቀደም “ዶ/ር አሸብርና ሌሎችም” የተባለ የአጭር ልቦለዶች መድበልና “እናት ፍቅር ሃገር” የተሰኘ የግጥም መፅሃፍ ለንባብ ማብቃቱ ይታወሳል፡፡

 

 

 

    የ73ቱ ዓመቱን የዕድሜ ባለፀጋ የዶክተር ተስፋፅዮን ደለለ ግለ-ታሪክ የሚያስነብበው “ከሚሽግዳ እስከ ዓለም ዳርቻ (ሕይወቴ ትምህርት ቤቴ)” የተሰኘ መጽሐፍ ሰሞኑን ለንባብ በቃ፡፡ ግለ-ታሪኩን የፃፉት ራሳቸው ዶ/ር ተስፋጽዮን ሲሆኑ የአርትኦት ሥራውን ያከናወነው ገጣሚ ወንድዬ ዓሊ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል፡፡

የፖፑሌሽን ሚዲያ ሴንተር የኢትዮጵያ ተጠሪ ዶ/ር ንጉሴ ተፈራ በመጽሐፉ ጀርባ ላይ በሰጡት አስተያየት፤ “ይህ መጽሐፍ እግዚአብሔር በዶ/ር ተስፋፅዮን ህይወት ውስጥ ያደረገውን በጐ ነገር እንድታውቁ የሚረዳችሁ ብቻ ሳይሆን “‹በእኔ የህይወት ጉዞ የታየ ትርጉም ያለው ድርሻ ምንድን ነበር” ብላችሁ እንድትጠይቁ ያደርጋችኋል… ሁሉም ሊያነበው የሚገባ ቁምነገር የያዘ መጽሐፍ” ብለውታል፡፡

የመፅሐፉ አርታዒ ገጣሚ ወንድዬ አሊ በበኩሉ፤ “አተራረኩ ሲበዛ ተፈጥሮአዊ ከመሆኑ የተነሳ የጋሽ ተስፋን ረቂቅ ኩል መኳኳል፣ እንሶስላ ማሞቅ አላስፈለገኝም፤ በርኖስ ላይ ካቦርታ መደረብ ነውና፡፡” ሲል አስተያየቱን ገልጿል፡፡ በ10 ምዕራፎችና በ284 ገፆች የተቀነበበው መጽሐፉ፤ በ80 ብር እየተሸጠ ነው፡፡

   

 

 

 

Tuesday, 26 May 2015 08:20

ምሳሌያዊ አባባል

 

የአዞ ጉልበት በውሃ ውስጥ ነው፡፡

የደቡብ አፍሪካውያን አባባል

ብልህ ወፍ ጎጆዋን በሌሎች ወፎች ላባ ትሰራለች

የዚምባቡዌያውያን አባባል

ሁለት መሪዎች በአንድ ቤት ውስጥ አይጣሉም፡፡

የኡጋንዳውያን አባባል

ደካማ መሪ ጭንቅላቱ ውስጥ ሸክም ያበዛል።

የኡጋንዳውያን አባባል

መሪ ካነከሰ ሌሎችም ማንከስ ይጀምራሉ፡፡

የኬንያውያን አባባል

የመሪ የተሳሳተ እርምጃ ለተከታዮቹ ማስጠንቀቂያ ነው፡፡

የአፍሪካውያን አባባል

አገር በማስፈራሪያና በስድብ ጨርሶ አትመራም፡፡

የዛምቢያውያን አባባል

መሪ የሌለው ህዝብ ከተማ ያበላሻል፡፡

የጋናውያን አባባል

በዓለም ላይ እጅግ ኃይለኛው መሪ እንኳን በእንቅልፍ ይሸነፋል፡፡

የማላዊያውያን አባባል

አይጥን የሚገድል ዝሆን ጀግና አይባልም፡፡

የካሜሩያውያን አባባል

የመሪ ሃብቱ ህዝቦቹ ናቸው፡፡

የኮንጎአዊያን አባባል

ብቸኛ መሳሪያህ መዶሻ ከሆነ ችግሮችን ሁሉ እንደምስማር ትቆጥራቸዋለህ፡፡

የጋምቢያውያን አባባል

ውይይት ሲበዛ ወደ ፀብ ያመራል፡፡

የአይቮሪኮስት አባባል

አንበሳ ሳር ውስጥ መደበቅ አይችልም፡፡

የኬንያውያን አባባል

ሰው ረዥም ጥርስ ማብቀል ከፈለገ መሸፈኛ ከንፈር ሊኖረው ይገባል፡፡

የናይጄሪያውያን አባባል

 

የአዞ ጉልበት በውሃ ውስጥ ነው፡፡

የደቡብ አፍሪካውያን አባባል

ብልህ ወፍ ጎጆዋን በሌሎች ወፎች ላባ ትሰራለች

የዚምባቡዌያውያን አባባል

ሁለት መሪዎች በአንድ ቤት ውስጥ አይጣሉም፡፡

የኡጋንዳውያን አባባል

ደካማ መሪ ጭንቅላቱ ውስጥ ሸክም ያበዛል።

የኡጋንዳውያን አባባል

መሪ ካነከሰ ሌሎችም ማንከስ ይጀምራሉ፡፡

የኬንያውያን አባባል

የመሪ የተሳሳተ እርምጃ ለተከታዮቹ ማስጠንቀቂያ ነው፡፡

የአፍሪካውያን አባባል

አገር በማስፈራሪያና በስድብ ጨርሶ አትመራም፡፡

የዛምቢያውያን አባባል

መሪ የሌለው ህዝብ ከተማ ያበላሻል፡፡

የጋናውያን አባባል

በዓለም ላይ እጅግ ኃይለኛው መሪ እንኳን በእንቅልፍ ይሸነፋል፡፡

የማላዊያውያን አባባል

አይጥን የሚገድል ዝሆን ጀግና አይባልም፡፡

የካሜሩያውያን አባባል

የመሪ ሃብቱ ህዝቦቹ ናቸው፡፡

የኮንጎአዊያን አባባል

ብቸኛ መሳሪያህ መዶሻ ከሆነ ችግሮችን ሁሉ እንደምስማር ትቆጥራቸዋለህ፡፡

የጋምቢያውያን አባባል

ውይይት ሲበዛ ወደ ፀብ ያመራል፡፡

የአይቮሪኮስት አባባል

አንበሳ ሳር ውስጥ መደበቅ አይችልም፡፡

የኬንያውያን አባባል

ሰው ረዥም ጥርስ ማብቀል ከፈለገ መሸፈኛ ከንፈር ሊኖረው ይገባል፡፡

የናይጄሪያውያን አባባል

 

 

 

ምርጫው በአንድ ሳምንት ተራዝሟል

ከ110 ሺህ በላይ ዜጎች ወደ ጎረቤት አገራት ተሰደዋል

33 ስደተኞች በታንዛኒያ ካምፕ በኮሌራ ሞተዋል

 

    የብሩንዲ መፈንቅለ መንግስት መክሸፉን ተከትሎ የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ፔሬ ንኩሩንዚዛ ባለፈው ረቡዕ ተቃዋሚዎች ከድርጊታቸው እንዲታቀቡና ሰላም እንዲወርድ ጥሪ ቢያቀርቡም፣ ብጥብጡ ከትናንት በስቲያ በመዲናዋ ቡጁምቡራ እንደገና ማገርሸቱንና ወደሌሎች የአገሪቱ አካባቢዎች ተባብሶ መቀጠሉን ሮይተርስ ዘገበ፡፡

ፕሬዚዳንቱ ህገመንግስቱን ጥሰው ለሶስተኛ ዙር በምርጫ ለመወዳደር መወሰናቸው አግባብ አይደለም ሲሉ የተቃወሙ በርካታ ዜጎች፤ ሃሙስ ዕለት ዳግም ወደ አደባባይ ወጥተው፣ ድንጋይ በመወርወርና እሳት በማቀጣጠል የከተማዋን ጎዳና ማጥለቅለቃቸውን የጠቆመው ዘገባው፣ ፖሊስም አስለቃሽ ጭስ በመርጨትና ጥይት በመተኮስ ብጥብጡን በቁጥጥር ስር ለማዋል ሲሞክር እንደዋለ ገልጿል፡፡

ከፖሊስ በተተኮሰባቸው ጥይት የቆሰሉ በርካታ ተቃዋሚዎች እንዳሉና አንድ ወታደርም  ህይወቱ እንዳለፈ ዘገባው ጠቅሶ፣ ተቃውሞው ወደ ሌሎች የአገሪቱ አካባቢዎች መስፋፋቱንና  በፖሊስና በተቃዋሚዎች መካከል ግጭት መፈጠሩን አስታውቋል፡፡

ለሳምንታት በቀጠለው የብሩንዲ ግጭት የሞቱ ሰዎች ቁጥር ከ20 በላይ መድረሱንና ግጭቱን በመሸሽ ወደ ጎረቤት አገራት ሩዋንዳ፣ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ እና ታንዛኒያ የተሰደዱ የአገሪቱ ዜጎች ቁጥርም ከ110 ሺህ በላይ መድረሱን የጠቆመው ዘገባው፣ በታንዛኒያ የካጉንጋ ስደተኞች ካምፕ ከሚገኙ 70 ሺህ ያህል ብሩንዲያውያን መካከል 33 ያህሉ በካምፑ ውስጥ በተከሰተ የኮሌራ ወረርሽኝ መሞታቸውን አክሎ ገልጿል፡፡

በዘንድሮው ምርጫ ለመሳተፍ መወሰናቸው ተቃውሞ ያስነሳባቸው ፕሬዚዳንት ንኩሩንዚዛ፤  ውሳኔያቸውን እንዲቀይሩ ከዜጎቻቸውና ከውጭ ሃይሎች ጫና ቢደረግባቸውም፣ እወዳደራለሁ በሚለው አቋማቸው የፀኑ ሲሆን በሚቀጥለው ሳምንት ሊካሄድ የታሰበውን ምርጫ በአንድ ሳምንት በማራዘም ሰኔ አምስት ቀን እንዲከናወን መወሰናቸው ታውቋል፡፡

በሌሉበት የተቃጣባቸው መፈንቅለ መንግስት መክሸፉን ተከትሎ ፕሬዚዳንት ንኩሩንዚዛ ድርጊቱን የመሩ ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር ያዋሉ ሲሆን፣ ግለሰቦቹ ህዝብን በማበጣበጥና አብዮት በማነሳሳት ወንጀል ተከሰው በአገሪቱ የጦር ፍርድ ቤት ቅጣት ይጣልባቸዋል መባሉን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡

ምርጫው በአንድ ሳምንት ተራዝሟል

ከ110 ሺህ በላይ ዜጎች ወደ ጎረቤት አገራት ተሰደዋል

33 ስደተኞች በታንዛኒያ ካምፕ በኮሌራ ሞተዋል

 

    የብሩንዲ መፈንቅለ መንግስት መክሸፉን ተከትሎ የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ፔሬ ንኩሩንዚዛ ባለፈው ረቡዕ ተቃዋሚዎች ከድርጊታቸው እንዲታቀቡና ሰላም እንዲወርድ ጥሪ ቢያቀርቡም፣ ብጥብጡ ከትናንት በስቲያ በመዲናዋ ቡጁምቡራ እንደገና ማገርሸቱንና ወደሌሎች የአገሪቱ አካባቢዎች ተባብሶ መቀጠሉን ሮይተርስ ዘገበ፡፡

ፕሬዚዳንቱ ህገመንግስቱን ጥሰው ለሶስተኛ ዙር በምርጫ ለመወዳደር መወሰናቸው አግባብ አይደለም ሲሉ የተቃወሙ በርካታ ዜጎች፤ ሃሙስ ዕለት ዳግም ወደ አደባባይ ወጥተው፣ ድንጋይ በመወርወርና እሳት በማቀጣጠል የከተማዋን ጎዳና ማጥለቅለቃቸውን የጠቆመው ዘገባው፣ ፖሊስም አስለቃሽ ጭስ በመርጨትና ጥይት በመተኮስ ብጥብጡን በቁጥጥር ስር ለማዋል ሲሞክር እንደዋለ ገልጿል፡፡

ከፖሊስ በተተኮሰባቸው ጥይት የቆሰሉ በርካታ ተቃዋሚዎች እንዳሉና አንድ ወታደርም  ህይወቱ እንዳለፈ ዘገባው ጠቅሶ፣ ተቃውሞው ወደ ሌሎች የአገሪቱ አካባቢዎች መስፋፋቱንና  በፖሊስና በተቃዋሚዎች መካከል ግጭት መፈጠሩን አስታውቋል፡፡

ለሳምንታት በቀጠለው የብሩንዲ ግጭት የሞቱ ሰዎች ቁጥር ከ20 በላይ መድረሱንና ግጭቱን በመሸሽ ወደ ጎረቤት አገራት ሩዋንዳ፣ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ እና ታንዛኒያ የተሰደዱ የአገሪቱ ዜጎች ቁጥርም ከ110 ሺህ በላይ መድረሱን የጠቆመው ዘገባው፣ በታንዛኒያ የካጉንጋ ስደተኞች ካምፕ ከሚገኙ 70 ሺህ ያህል ብሩንዲያውያን መካከል 33 ያህሉ በካምፑ ውስጥ በተከሰተ የኮሌራ ወረርሽኝ መሞታቸውን አክሎ ገልጿል፡፡

በዘንድሮው ምርጫ ለመሳተፍ መወሰናቸው ተቃውሞ ያስነሳባቸው ፕሬዚዳንት ንኩሩንዚዛ፤  ውሳኔያቸውን እንዲቀይሩ ከዜጎቻቸውና ከውጭ ሃይሎች ጫና ቢደረግባቸውም፣ እወዳደራለሁ በሚለው አቋማቸው የፀኑ ሲሆን በሚቀጥለው ሳምንት ሊካሄድ የታሰበውን ምርጫ በአንድ ሳምንት በማራዘም ሰኔ አምስት ቀን እንዲከናወን መወሰናቸው ታውቋል፡፡

በሌሉበት የተቃጣባቸው መፈንቅለ መንግስት መክሸፉን ተከትሎ ፕሬዚዳንት ንኩሩንዚዛ ድርጊቱን የመሩ ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር ያዋሉ ሲሆን፣ ግለሰቦቹ ህዝብን በማበጣበጥና አብዮት በማነሳሳት ወንጀል ተከሰው በአገሪቱ የጦር ፍርድ ቤት ቅጣት ይጣልባቸዋል መባሉን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡

 

 

 

 

 

 

   የምዕራብ አፍሪካ አገራት ፕሬዚዳንቶች ከሁለት ዙር በላይ በስልጣን ላይ እንዳይቆዩ ለማድረግ ታልሞ የቀረበውን የስልጣን ገደብ የሚያስቀምጥ ክልላዊ የስምምነት ሃሳብ፣ የአገራቱ መሪዎች ውድቅ እንዳደረጉት ቢቢሲ ዘገበ፡፡

የአገራቱ መሪዎች ባለፈው ማክሰኞ በጋና መዲና አክራ ባካሄዱት የኮሜሳ ክልላዊ ስብሰባ ላይ፣ በሃሳቡ ዙሪያ መምከራቸውንና ለጊዜው ሃሳቡን ውድቅ ማድረጋቸውን የጠቆመው ዘገባው፣ ከሁለት ዙር በላይ በስልጣን ላይ በቆዩ መሪዎች በመመራት ላይ ያሉት ቶጎ እና ጋምቢያ የስልጣን ዘመን ገደቡን አጥብቀው እንደተቃወሙት ገልጿል፡፡ አብዛኞቹ የምእራብ አፍሪካ አገራት በህገ-መንግስቶቻቸው አንድ ፕሬዚዳንት ከሁለት ዙር በላይ በስልጣን ላይ መቆየት እንደማይችል ቢደነግጉም፣ በተቃራኒው ከዚህ ገደብ አልፈው በስልጣናቸው የሚቆዩ መሪዎች አሉ ብሏል ዘገባው፡፡

አንዳንድ የምእራብ አፍሪካ አገራት መሪዎች በጉዳዩ ዙሪያ በሰጡት አስተያየት፣ እያንዳንዱ አገር የየራሱ የሆነ የተለያየ የፖለቲካ አውድ ውስጥ የሚገኝ እንደመሆኑ፣ በሁሉም አገራት ላይ ተፈጻሚ የሚሆን አንድ አይነት ህግ መተግበር አግባብ አይደለም ብለዋል፡፡  

አስተያየት ሰጪዎች በበኩላቸው፤ የፕሬዚዳንቶችን የስልጣን ዘመን ቆይታ በክልላዊ ደረጃ በህግ መገደብ የሚለው ሃሳብ በስብሰባው ላይ ራሱን የቻለ የመወያያ አጀንዳ ሆኖ መቅረቡ እንደ አንድ የለውጥ ምእራፍ የሚታይ ነው ብለዋል፡፡ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የምእራብ አፍሪካ ተወካይ የሆኑት ሞሃመድ ኢብን ቻምፓስ  እቅዱን እንደሚደግፉት ገልጸው፣ ሃሳቡ የተጠነሰሰው የቡርኪናፋሶው ፕሬዚዳንት ብሌስ ኮምፓዎሬ ባለፈው አመት የአገሪቱን ህገመንግስት አንቀጽ በማሻሻል ለሶስተኛ ዙር በስልጣን ላይ ለመቆየት ያልተሳካ ሙከራ ማድረጋቸውን ተከትሎ እንደሆነ አስታውሰዋል፡፡

በአገራቱ መሪዎች ላይ የስልጣን ገደብ ለማስቀመጥ ታስቦ የተዘጋጀው ይህ እቅድ፤ ተጨማሪ ውይይት እንዲደረግበት መሪዎቹ ስምምነት ላይ መድረሳቸውን ያስታወቀው ዘገባው፣ የቶጎው ፕሬዚዳንት ፋኦሪ ጋሲንግቤ ለሶስተኛ፣ የጋምቢያው ፕሬዚዳንት  ያህያ ጃሜህ ደግሞ ለአራተኛ ዙር የስልጣን ዘመን አገራቱን እየመሩ እንደሚገኙም ጠቁሟል፡፡

   የምዕራብ አፍሪካ አገራት ፕሬዚዳንቶች ከሁለት ዙር በላይ በስልጣን ላይ እንዳይቆዩ ለማድረግ ታልሞ የቀረበውን የስልጣን ገደብ የሚያስቀምጥ ክልላዊ የስምምነት ሃሳብ፣ የአገራቱ መሪዎች ውድቅ እንዳደረጉት ቢቢሲ ዘገበ፡፡

የአገራቱ መሪዎች ባለፈው ማክሰኞ በጋና መዲና አክራ ባካሄዱት የኮሜሳ ክልላዊ ስብሰባ ላይ፣ በሃሳቡ ዙሪያ መምከራቸውንና ለጊዜው ሃሳቡን ውድቅ ማድረጋቸውን የጠቆመው ዘገባው፣ ከሁለት ዙር በላይ በስልጣን ላይ በቆዩ መሪዎች በመመራት ላይ ያሉት ቶጎ እና ጋምቢያ የስልጣን ዘመን ገደቡን አጥብቀው እንደተቃወሙት ገልጿል፡፡ አብዛኞቹ የምእራብ አፍሪካ አገራት በህገ-መንግስቶቻቸው አንድ ፕሬዚዳንት ከሁለት ዙር በላይ በስልጣን ላይ መቆየት እንደማይችል ቢደነግጉም፣ በተቃራኒው ከዚህ ገደብ አልፈው በስልጣናቸው የሚቆዩ መሪዎች አሉ ብሏል ዘገባው፡፡

አንዳንድ የምእራብ አፍሪካ አገራት መሪዎች በጉዳዩ ዙሪያ በሰጡት አስተያየት፣ እያንዳንዱ አገር የየራሱ የሆነ የተለያየ የፖለቲካ አውድ ውስጥ የሚገኝ እንደመሆኑ፣ በሁሉም አገራት ላይ ተፈጻሚ የሚሆን አንድ አይነት ህግ መተግበር አግባብ አይደለም ብለዋል፡፡  

አስተያየት ሰጪዎች በበኩላቸው፤ የፕሬዚዳንቶችን የስልጣን ዘመን ቆይታ በክልላዊ ደረጃ በህግ መገደብ የሚለው ሃሳብ በስብሰባው ላይ ራሱን የቻለ የመወያያ አጀንዳ ሆኖ መቅረቡ እንደ አንድ የለውጥ ምእራፍ የሚታይ ነው ብለዋል፡፡ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የምእራብ አፍሪካ ተወካይ የሆኑት ሞሃመድ ኢብን ቻምፓስ  እቅዱን እንደሚደግፉት ገልጸው፣ ሃሳቡ የተጠነሰሰው የቡርኪናፋሶው ፕሬዚዳንት ብሌስ ኮምፓዎሬ ባለፈው አመት የአገሪቱን ህገመንግስት አንቀጽ በማሻሻል ለሶስተኛ ዙር በስልጣን ላይ ለመቆየት ያልተሳካ ሙከራ ማድረጋቸውን ተከትሎ እንደሆነ አስታውሰዋል፡፡

በአገራቱ መሪዎች ላይ የስልጣን ገደብ ለማስቀመጥ ታስቦ የተዘጋጀው ይህ እቅድ፤ ተጨማሪ ውይይት እንዲደረግበት መሪዎቹ ስምምነት ላይ መድረሳቸውን ያስታወቀው ዘገባው፣ የቶጎው ፕሬዚዳንት ፋኦሪ ጋሲንግቤ ለሶስተኛ፣ የጋምቢያው ፕሬዚዳንት  ያህያ ጃሜህ ደግሞ ለአራተኛ ዙር የስልጣን ዘመን አገራቱን እየመሩ እንደሚገኙም ጠቁሟል፡፡

 

 

 

 

 

 

       አንድ በራሪ መኪና 566 ሺህ ዶላር ተተምኗል

 

      በርካታ ቁጥር ያላቸው የመኪና አምራች ኩባንያዎች በራሪ መኪናዎችን በማምረት ቀድመው ለገበያ ለማቅረብ ብርቱ ፉክክር ውስጥ እንደሚገኙና መኪኖቹ በሁለት አመት ጊዜ ውስጥ ለገበያ ይቀርባሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ሲኤንኤን ዘገበ፡፡

በአውቶሞቲቭ ኢንዱስትሪው ዘርፍ መሰረታዊ ለውጥ ይመጣበታል ተብሎ በሚነገርለት የበራሪ መኪናዎች ፈጠራ ፉክክር ውስጥ ቴራፉጊያ፣ ኤሮሞቢልና ሞለር ኢንተርናሽናልን ጨምሮ በርካታ የተለያዩ አገራት የመኪና አምራች ኩባንያዎች እየተፎካከሩ እንደሚገኙ ዘገባው ጠቁሟል፡፡

የአሜሪካው ቴራፉጊያ ኩባንያ  በራሪ መኪናዎችን በሁለት አመታት ጊዜ ውስጥ አምርቶ ለገበያ ለማቅረብ እየተዘጋጀ እንደሚገኝ የጠቆመው ዘገባው፣ ኩባንያው ከ100 በላይ ደንበኞቹ የግዢ ትዕዛዝ እንደተሰጠውና ከፊል ክፍያ እንደተፈጸመለት አመልክቷል፡፡

የስሎቫኪያው ኤሮሞቢል በበኩሉ፤ በ2017 መጀመሪያ ላይ የበራሪ መኪኖችን ዲዛይን ለማጠናቀቅና ከገዢዎች ትዕዛዝ ለመቀበል ያቀደ ሲሆን የግዢ ጥያቄ ከደንበኞቹ በመቀበል ላይ የሚገኘው የኔዘርላንዱ ፓል-ቪ ኩባንያም በ2017 አጋማሽ መኪኖቹን ለደንበኞቹ ለማስረከብ አቅዶ እየሰራ ይገኛል፡፡

ኩባንያዎቹ በሚያመርቷቸው በራሪ መኪኖች ትርፋማ እንደሚሆኑ ቅንጣት ታህል ጥርጣሬ ባይኖራቸውም፣ ከመንገድ ደህንነት ጋር የተያያዙና የአጭር ጊዜ ግቦቻቸውን ከማሳካት የሚገቷቸው በርካታ እንቅፋቶች ሊገጥሟቸው እንደሚችሉ እየተነገረ ነው፡፡

በራሪ መኪኖቹ በመንገድ ላይ በአግባቡ መንቀሳቀስ መቻላቸውንና ደህንነታቸውን ለመፈተሸ የሚደረጉላቸውን በርካታ ፈተናዎች ማለፍ እንደሚጠበቅባቸው የጠቆመው ዘገባው፤ ከየአገራቱ መንግስታት አስፈላጊውን የአቪየሽን፣ የመንገድና የትራንስፖርት ፈቃዶችን የማግኘቱ ጉዳይም ረጅም ጊዜን ሊወስድባቸው እንደሚችል እየተነገረ መሆኑን ገልጿል፡፡ ኩባንያዎቹ ለማምረት ያሰቧቸው በራሪ መኪኖች ዲዛይንና ለገበያ የሚያቀርቡበት  የመሸጫ ዋጋቸው የተለያየ ነው፡፡ የመኪኖቹ አማካይ ዋጋ 300 ሺህ ዶላር እንደሚደርስ ዘገባው ጠቁሞ፣ የፓል-ቪ ኩባንያ ዋና ስራ አስፈጻሚ ዲንጊ ማኔዝ፣ ኩባንያቸው አንዷን በራሪ መኪና የሚሸጥበት ከፍተኛው ዋጋ 566 ሺህ ዶላር እንደሚሆን መናገራቸውን አክሎ ገልጿል፡፡

 

       አንድ በራሪ መኪና 566 ሺህ ዶላር ተተምኗል

 

      በርካታ ቁጥር ያላቸው የመኪና አምራች ኩባንያዎች በራሪ መኪናዎችን በማምረት ቀድመው ለገበያ ለማቅረብ ብርቱ ፉክክር ውስጥ እንደሚገኙና መኪኖቹ በሁለት አመት ጊዜ ውስጥ ለገበያ ይቀርባሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ሲኤንኤን ዘገበ፡፡

በአውቶሞቲቭ ኢንዱስትሪው ዘርፍ መሰረታዊ ለውጥ ይመጣበታል ተብሎ በሚነገርለት የበራሪ መኪናዎች ፈጠራ ፉክክር ውስጥ ቴራፉጊያ፣ ኤሮሞቢልና ሞለር ኢንተርናሽናልን ጨምሮ በርካታ የተለያዩ አገራት የመኪና አምራች ኩባንያዎች እየተፎካከሩ እንደሚገኙ ዘገባው ጠቁሟል፡፡

የአሜሪካው ቴራፉጊያ ኩባንያ  በራሪ መኪናዎችን በሁለት አመታት ጊዜ ውስጥ አምርቶ ለገበያ ለማቅረብ እየተዘጋጀ እንደሚገኝ የጠቆመው ዘገባው፣ ኩባንያው ከ100 በላይ ደንበኞቹ የግዢ ትዕዛዝ እንደተሰጠውና ከፊል ክፍያ እንደተፈጸመለት አመልክቷል፡፡

የስሎቫኪያው ኤሮሞቢል በበኩሉ፤ በ2017 መጀመሪያ ላይ የበራሪ መኪኖችን ዲዛይን ለማጠናቀቅና ከገዢዎች ትዕዛዝ ለመቀበል ያቀደ ሲሆን የግዢ ጥያቄ ከደንበኞቹ በመቀበል ላይ የሚገኘው የኔዘርላንዱ ፓል-ቪ ኩባንያም በ2017 አጋማሽ መኪኖቹን ለደንበኞቹ ለማስረከብ አቅዶ እየሰራ ይገኛል፡፡

ኩባንያዎቹ በሚያመርቷቸው በራሪ መኪኖች ትርፋማ እንደሚሆኑ ቅንጣት ታህል ጥርጣሬ ባይኖራቸውም፣ ከመንገድ ደህንነት ጋር የተያያዙና የአጭር ጊዜ ግቦቻቸውን ከማሳካት የሚገቷቸው በርካታ እንቅፋቶች ሊገጥሟቸው እንደሚችሉ እየተነገረ ነው፡፡

በራሪ መኪኖቹ በመንገድ ላይ በአግባቡ መንቀሳቀስ መቻላቸውንና ደህንነታቸውን ለመፈተሸ የሚደረጉላቸውን በርካታ ፈተናዎች ማለፍ እንደሚጠበቅባቸው የጠቆመው ዘገባው፤ ከየአገራቱ መንግስታት አስፈላጊውን የአቪየሽን፣ የመንገድና የትራንስፖርት ፈቃዶችን የማግኘቱ ጉዳይም ረጅም ጊዜን ሊወስድባቸው እንደሚችል እየተነገረ መሆኑን ገልጿል፡፡ ኩባንያዎቹ ለማምረት ያሰቧቸው በራሪ መኪኖች ዲዛይንና ለገበያ የሚያቀርቡበት  የመሸጫ ዋጋቸው የተለያየ ነው፡፡ የመኪኖቹ አማካይ ዋጋ 300 ሺህ ዶላር እንደሚደርስ ዘገባው ጠቁሞ፣ የፓል-ቪ ኩባንያ ዋና ስራ አስፈጻሚ ዲንጊ ማኔዝ፣ ኩባንያቸው አንዷን በራሪ መኪና የሚሸጥበት ከፍተኛው ዋጋ 566 ሺህ ዶላር እንደሚሆን መናገራቸውን አክሎ ገልጿል፡፡

 

 

 

 

 

 

 

ይህ ታሪክ በሩሲያ የተፈፀመ ታሪክ ነው፡፡ በአበሽኛ እንተርከዋለን …. በቀድሞው ዘመን አንድ የ80 ዓመት አዛውንት እሥር ቤት ይገባሉ አሉ፡፡ ከዚያም፤ ታሣሪው ሁሉ እንደሚሆነው ለምርመራ ተጠርተው፤ “ወንጀለኛ ነዎት ይመኑ!” ይባላሉ፡፡

“ወንጀለኛ አይደለሁም” ይላሉ አዛውንቱ፡፡

“ሌላ ነገር ሳይከተል ቢያምኑ ይሻልዎታል!” ይላል መርማሪው፤ በከባድ የማስፈራራት ድምፅ።

“ያልሆንኩትን ነኝ ብዬ አላምንልህም!” ይላሉ በቁርጠኝነት፡፡ መርማሪው በከፍተኛ ንዴት ማጅራታቸውን እያዳፋ ወደ ማረፊያው ክፍል ይወስዳቸውና ባልተወለደ አንጀቱ፣ የበላ የጠጣውን ያህል ይደበድባቸዋል፡፡ አዛውንቱ ደም በደም ይሆናሉ፡፡ እግራቸው መራመድ እስከሚያቅታቸው ደረስ ይተለተላል፡፡

በኋላም፤ ወደ እሥር ቤቱ አምጥተው ይወረውሯቸዋል፡፡ እሥር ቤት የተቀበላቸው አንድ ወጣት ወዳጃቸው፤

“አባቴ ምነው እንዲህ ጎዱዎት? እኛን ወጣቶቹን እንኳን እንዲህ አልደበደቡንም’ኮ?” ሲል ይጠይቃቸዋል፡፡

አዛውንቱም የሚከተለውን ወግ ይነግሩታል፡፡

“በአንድ ወቅት የዐርብ ስቅለት ዕለት ፆመኛው ሁሉ ወደቤተስኪያን ሄዶ በሚሰግድበት ወቅት ለቄሱ በፆሙ ወቅት የተሳሳተውን ይናገራል፡፡ ወይም ይናዘዛል፡፡ ቄሱም በቄጤማ ቸብ እያደረጉ እንደስህተቱ መጠን የሚሰግደውን ቁጥር ይሰጣሉ፡፡ ሐጢያቱን ለማስተሰረይ፡፡

አንዱ - “በፆም ተሳስቼ በልቻለሁ” ይላቸዋል፡፡

ቄሱ - በቄጤማው ይመቱትና፤

“ሃያ ስገድ” ይሉታል፡፡

ሌላው - “አባቴ፤ ሰው ተሳድቤአለሁ” ይላል፡፡

ቄሱ - “ሰላሳ ስገድ” ይሉታል፡፡ ደሞ ሌላው ይመጣል፤

“አባቴ፤ በፆሙ ወቅት ከአልጋው ወድቄያለሁ ይላቸዋል” ቄሱም በቄጠማው መታ ያደርጉትና

“ስልሳ ስገድ!” ይሉታል፡፡

በመጨረሻ አንድ ፈርጠም ያለ ጎልማሳ ይመጣና ወደ ጆሮአቸው ጠጋ ብሎ፣ በዝቅተኛ ድምፅ፤

“አባቴ፤ ይቅር ይበሉኝ፤ ከሚስትዎ ጋር ተሳስቼ ተኝቻለሁ” ይላቸዋል፡፡

ቄሱም ከመቅፀበት የብረት መቋሚያቸውን ብድግ ያደርጉና አናቱን ይሉታል!!

ሰውዬም፤ “ምነው አባቴ! ሰውን ሁሉ በቄጤማ ሲጠበጥቡ እኔን በብረት መቋሚያ መቱኝ?” አላቸው፡፡

ቄሱም፤

 “ሰው ሁሉ እንደየሐጢያቱ ይጠበጠባል!” አሉት ይባላል፡፡

                                             *        *      *

ህዝብ የሚደግፈውንም ሆነ የሚቀጣውን ፓርቲ ያውቃል፡፡ ያም የልማታችንን ወይም የጥፋታችንን፤ የመታመናችንን አሊያም ተአማኒነት የማጣታችንን መጠን ያሳየናል፡፡ እነሆ፣ ምን ያህል ህዝብ ውስጥ የመግባታችንንና ምን ያህልም ልቡ ውስጥ እንዳደርን፤ ውጤታችንን በአንድ ጀንበር የሚወሰንበት ሰዓት ጋ ደርሰናል፡፡ የምርጫ ካርድ የህዝብ ኃይል ነው፡፡ የትኛውንም ፓርቲ በስሜት ሳይሆን በነቃ አዕምሮ የሚመርጥ ህዝብ የነገ ዕጣ ፈንታውን ዛሬ የወሰነ ነው፡፡ “ህዝቡ የፈለገውን ፓርቲ መምረጥ ካልቻለ ፓርቲው የፈለገውን ህዝብ ይምረጥ” ይላል ብሬሽት፡፡ የተዛባ የምርጫ ሁኔታን ሲጠቁመን ነው፡፡ ስለሆነም እንጠንቀቅ፡፡ ህዝብ የሚመርጠውን በልቡ ይዞ የሚኖር ነው፡፡ የልቡን በእጁ ካርድ ማሳየቱ አይቀርም፡፡ የበደልነው፣ ያጠፋነው ነገር ካለ በምጫው ይመሰክርብናል፡፡ ይቀጣናል፡፡ ጥፋት አጥፍተን የጥፋቱን ማርከሻ ይቅርታ መጠየቅ ወይንስ ሌላ ማምለጫ ዘዴ መፈለግ? ለሚለው ጥያቄ በየዘመኑ ያየነው በአብዛኛው ጥፋትን በጥፋት ለመሻር ሲሞከር አይተናል፡፡ ሳኦ ሳኦ የተባለ የቻይና መሪ በጥንት ጊዜ “ዓለም ከሚክደኝ ዓለምን ብክድ ይሻለኛል” በሚል መርህ አንዱን የጦር አዛዡን ገድሎ የሱ ጥፋት ነው ጦሬን ለዚህ ያበቃው፤ ብሏል ይባላል፡፡ ሰበብ ወይም ማምለጫ ዘዴ (Scapegoat) ለጊዜው እንጂ ለዘለቄታው አይበጅም፡፡ ይህን የተገነዘበ ህዝብ የታደለ ነው፡፡ ጨውን ከአሞሌ፣ ወመቴን ከአለሌ፣ ጨለሌን ከጮሌ የሚለይ ዐይን ሊኖር ይገባል፡፡ “አስመሳይ ተራማጅ” ይባል የነበረው በድሮው ጊዜ በዋዛ አይደለም፡፡ “ቁልቋል የወደቀው ቅርንጫፍ ሲያበዛ ነው” የሚለውን ተረት ልብ-ማለት ተገቢ ነው፡፡ ልንፈጥር የምንፈልገውን ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት እንወቅ፡፡ እንመንበት፡፡ በተግባር እንደምናውለው እርግጠኛ እንሁን፡፡

“ዕውር አይናማ ተሸክሞ የምናይበት ሥርዓት አንፈልግም” ይሉ ነበር የግሪክ አበው፡፡ እኛም አንፈልግም፡፡ የሚመራን ዐይናማ መሆን አለበት፡፡ በእርግጠኝነት አገሩን የሚያይና የሚወድ መሆን አለበት፡፡ የተፃፈውን የሚያከብር መሪ ያሻናል፡፡ የተፃፈው መለወጥ ካለበት ደግሞ በግትርነት አይለወጥም የማይልና ለውጥንና መለወጥን የማይፈራ መሆን ይኖርበታል፡፡ ከሁሉም በላይ በራስ መተማመንን የህልውናው መሠረት ያደረገ ሊሆን ይገባል፡፡

ከእስከዛሬው ምርጫ ትምህርት ያገኘን ከሆነ ከማናቸውም መጭበርበርና ማጭበርበር ነጻ እንወጣለን፡፡ ከታዛቢ አድልዎ እንድናለን፡፡ “ከላም አለኝ በሰማይ” የሥልጣን መቋመጥ፣ በዚያም ከሚፈጠር መተረማመስ እንገላገላለን፡፤ ዲሞክራሲ የልመና ድርጎ ይመስል ለእነገሌ ይሄን ያህል የፓርላም ወንበር፣ ለእነእገሌ ይሄን ያህል፤ እያልን ሻሞ ብለው ለራሳቸው እንደወሰዱት ሰው እንዳንሆን እንጠነቀቃለን፡፡ በመላው አፍሪካ ተከስቶ ስናይ እንደከረምነው ዓይነት ምርጫ፤ ብሶት የሚጉረመረምበት እንዳይሆን፣ ኖረን አልነበርንም የምንልበት እንዳንሆን፤ ብርቱ ጥረት እናደርጋለን፡፡

ምርጫ፤ መሰረታዊ የዲሞክራሲ ባህል ነው፡፡ “አረረም መረረም ማበሬን ተወጣሁ” ይላሉ አበው፡፡ ምርጫ በየአምስት ዓመቱ እየተሻለው እንዲመጣ እንመኝ፡፡ ለዓለም አቀፍ ፍጆታ (International Consumption) ብለን ሳይሆን ለራሳችን ህዝብ ፍጆታ እናስብ፡፡ መንገዳችን የሚቃናው ሁላችንም እንደምንሄድበት አድርገን መጥረግ ስንችል ነው፡፡ ለዚሁም ትምህርታችንን ይግለጥልን!

ከግል ጥቅማችን፣ ከፓርቲያችን ጥቅም ወይም ከሌላ ከማናቸውም ወገናዊ ጥቅም ውጪ አገራችንን ብቻ አስበን የምንጓዝ ከሆንን ምርጫ የተቀደሰ ይሆናል፡፡ ይህ ሳይሆን በተቃራኒው ሐጢያት የሠራንበት ሂደት ከሆነ፤ “ሰው ሁሉ እንደየሐጢያቱ ይጠበጠባል” የሚለው ብሒል ዛሬም ባይሆን ነገ በጭራሽ መድረሱ የማይቀር ሐቅ ይሆናል!  

 

ይህ ታሪክ በሩሲያ የተፈፀመ ታሪክ ነው፡፡ በአበሽኛ እንተርከዋለን …. በቀድሞው ዘመን አንድ የ80 ዓመት አዛውንት እሥር ቤት ይገባሉ አሉ፡፡ ከዚያም፤ ታሣሪው ሁሉ እንደሚሆነው ለምርመራ ተጠርተው፤ “ወንጀለኛ ነዎት ይመኑ!” ይባላሉ፡፡

“ወንጀለኛ አይደለሁም” ይላሉ አዛውንቱ፡፡

“ሌላ ነገር ሳይከተል ቢያምኑ ይሻልዎታል!” ይላል መርማሪው፤ በከባድ የማስፈራራት ድምፅ።

“ያልሆንኩትን ነኝ ብዬ አላምንልህም!” ይላሉ በቁርጠኝነት፡፡ መርማሪው በከፍተኛ ንዴት ማጅራታቸውን እያዳፋ ወደ ማረፊያው ክፍል ይወስዳቸውና ባልተወለደ አንጀቱ፣ የበላ የጠጣውን ያህል ይደበድባቸዋል፡፡ አዛውንቱ ደም በደም ይሆናሉ፡፡ እግራቸው መራመድ እስከሚያቅታቸው ደረስ ይተለተላል፡፡

በኋላም፤ ወደ እሥር ቤቱ አምጥተው ይወረውሯቸዋል፡፡ እሥር ቤት የተቀበላቸው አንድ ወጣት ወዳጃቸው፤

“አባቴ ምነው እንዲህ ጎዱዎት? እኛን ወጣቶቹን እንኳን እንዲህ አልደበደቡንም’ኮ?” ሲል ይጠይቃቸዋል፡፡

አዛውንቱም የሚከተለውን ወግ ይነግሩታል፡፡

“በአንድ ወቅት የዐርብ ስቅለት ዕለት ፆመኛው ሁሉ ወደቤተስኪያን ሄዶ በሚሰግድበት ወቅት ለቄሱ በፆሙ ወቅት የተሳሳተውን ይናገራል፡፡ ወይም ይናዘዛል፡፡ ቄሱም በቄጤማ ቸብ እያደረጉ እንደስህተቱ መጠን የሚሰግደውን ቁጥር ይሰጣሉ፡፡ ሐጢያቱን ለማስተሰረይ፡፡

አንዱ - “በፆም ተሳስቼ በልቻለሁ” ይላቸዋል፡፡

ቄሱ - በቄጤማው ይመቱትና፤

“ሃያ ስገድ” ይሉታል፡፡

ሌላው - “አባቴ፤ ሰው ተሳድቤአለሁ” ይላል፡፡

ቄሱ - “ሰላሳ ስገድ” ይሉታል፡፡ ደሞ ሌላው ይመጣል፤

“አባቴ፤ በፆሙ ወቅት ከአልጋው ወድቄያለሁ ይላቸዋል” ቄሱም በቄጠማው መታ ያደርጉትና

“ስልሳ ስገድ!” ይሉታል፡፡

በመጨረሻ አንድ ፈርጠም ያለ ጎልማሳ ይመጣና ወደ ጆሮአቸው ጠጋ ብሎ፣ በዝቅተኛ ድምፅ፤

“አባቴ፤ ይቅር ይበሉኝ፤ ከሚስትዎ ጋር ተሳስቼ ተኝቻለሁ” ይላቸዋል፡፡

ቄሱም ከመቅፀበት የብረት መቋሚያቸውን ብድግ ያደርጉና አናቱን ይሉታል!!

ሰውዬም፤ “ምነው አባቴ! ሰውን ሁሉ በቄጤማ ሲጠበጥቡ እኔን በብረት መቋሚያ መቱኝ?” አላቸው፡፡

ቄሱም፤

 “ሰው ሁሉ እንደየሐጢያቱ ይጠበጠባል!” አሉት ይባላል፡፡

*        *      *

ህዝብ የሚደግፈውንም ሆነ የሚቀጣውን ፓርቲ ያውቃል፡፡ ያም የልማታችንን ወይም የጥፋታችንን፤ የመታመናችንን አሊያም ተአማኒነት የማጣታችንን መጠን ያሳየናል፡፡ እነሆ፣ ምን ያህል ህዝብ ውስጥ የመግባታችንንና ምን ያህልም ልቡ ውስጥ እንዳደርን፤ ውጤታችንን በአንድ ጀንበር የሚወሰንበት ሰዓት ጋ ደርሰናል፡፡ የምርጫ ካርድ የህዝብ ኃይል ነው፡፡ የትኛውንም ፓርቲ በስሜት ሳይሆን በነቃ አዕምሮ የሚመርጥ ህዝብ የነገ ዕጣ ፈንታውን ዛሬ የወሰነ ነው፡፡ “ህዝቡ የፈለገውን ፓርቲ መምረጥ ካልቻለ ፓርቲው የፈለገውን ህዝብ ይምረጥ” ይላል ብሬሽት፡፡ የተዛባ የምርጫ ሁኔታን ሲጠቁመን ነው፡፡ ስለሆነም እንጠንቀቅ፡፡ ህዝብ የሚመርጠውን በልቡ ይዞ የሚኖር ነው፡፡ የልቡን በእጁ ካርድ ማሳየቱ አይቀርም፡፡ የበደልነው፣ ያጠፋነው ነገር ካለ በምጫው ይመሰክርብናል፡፡ ይቀጣናል፡፡ ጥፋት አጥፍተን የጥፋቱን ማርከሻ ይቅርታ መጠየቅ ወይንስ ሌላ ማምለጫ ዘዴ መፈለግ? ለሚለው ጥያቄ በየዘመኑ ያየነው በአብዛኛው ጥፋትን በጥፋት ለመሻር ሲሞከር አይተናል፡፡ ሳኦ ሳኦ የተባለ የቻይና መሪ በጥንት ጊዜ “ዓለም ከሚክደኝ ዓለምን ብክድ ይሻለኛል” በሚል መርህ አንዱን የጦር አዛዡን ገድሎ የሱ ጥፋት ነው ጦሬን ለዚህ ያበቃው፤ ብሏል ይባላል፡፡ ሰበብ ወይም ማምለጫ ዘዴ (Scapegoat) ለጊዜው እንጂ ለዘለቄታው አይበጅም፡፡ ይህን የተገነዘበ ህዝብ የታደለ ነው፡፡ ጨውን ከአሞሌ፣ ወመቴን ከአለሌ፣ ጨለሌን ከጮሌ የሚለይ ዐይን ሊኖር ይገባል፡፡ “አስመሳይ ተራማጅ” ይባል የነበረው በድሮው ጊዜ በዋዛ አይደለም፡፡ “ቁልቋል የወደቀው ቅርንጫፍ ሲያበዛ ነው” የሚለውን ተረት ልብ-ማለት ተገቢ ነው፡፡ ልንፈጥር የምንፈልገውን ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት እንወቅ፡፡ እንመንበት፡፡ በተግባር እንደምናውለው እርግጠኛ እንሁን፡፡

“ዕውር አይናማ ተሸክሞ የምናይበት ሥርዓት አንፈልግም” ይሉ ነበር የግሪክ አበው፡፡ እኛም አንፈልግም፡፡ የሚመራን ዐይናማ መሆን አለበት፡፡ በእርግጠኝነት አገሩን የሚያይና የሚወድ መሆን አለበት፡፡ የተፃፈውን የሚያከብር መሪ ያሻናል፡፡ የተፃፈው መለወጥ ካለበት ደግሞ በግትርነት አይለወጥም የማይልና ለውጥንና መለወጥን የማይፈራ መሆን ይኖርበታል፡፡ ከሁሉም በላይ በራስ መተማመንን የህልውናው መሠረት ያደረገ ሊሆን ይገባል፡፡

ከእስከዛሬው ምርጫ ትምህርት ያገኘን ከሆነ ከማናቸውም መጭበርበርና ማጭበርበር ነጻ እንወጣለን፡፡ ከታዛቢ አድልዎ እንድናለን፡፡ “ከላም አለኝ በሰማይ” የሥልጣን መቋመጥ፣ በዚያም ከሚፈጠር መተረማመስ እንገላገላለን፡፤ ዲሞክራሲ የልመና ድርጎ ይመስል ለእነገሌ ይሄን ያህል የፓርላም ወንበር፣ ለእነእገሌ ይሄን ያህል፤ እያልን ሻሞ ብለው ለራሳቸው እንደወሰዱት ሰው እንዳንሆን እንጠነቀቃለን፡፡ በመላው አፍሪካ ተከስቶ ስናይ እንደከረምነው ዓይነት ምርጫ፤ ብሶት የሚጉረመረምበት እንዳይሆን፣ ኖረን አልነበርንም የምንልበት እንዳንሆን፤ ብርቱ ጥረት እናደርጋለን፡፡

ምርጫ፤ መሰረታዊ የዲሞክራሲ ባህል ነው፡፡ “አረረም መረረም ማበሬን ተወጣሁ” ይላሉ አበው፡፡ ምርጫ በየአምስት ዓመቱ እየተሻለው እንዲመጣ እንመኝ፡፡ ለዓለም አቀፍ ፍጆታ (International Consumption) ብለን ሳይሆን ለራሳችን ህዝብ ፍጆታ እናስብ፡፡ መንገዳችን የሚቃናው ሁላችንም እንደምንሄድበት አድርገን መጥረግ ስንችል ነው፡፡ ለዚሁም ትምህርታችንን ይግለጥልን!

ከግል ጥቅማችን፣ ከፓርቲያችን ጥቅም ወይም ከሌላ ከማናቸውም ወገናዊ ጥቅም ውጪ አገራችንን ብቻ አስበን የምንጓዝ ከሆንን ምርጫ የተቀደሰ ይሆናል፡፡ ይህ ሳይሆን በተቃራኒው ሐጢያት የሠራንበት ሂደት ከሆነ፤ “ሰው ሁሉ እንደየሐጢያቱ ይጠበጠባል” የሚለው ብሒል ዛሬም ባይሆን ነገ በጭራሽ መድረሱ የማይቀር ሐቅ ይሆናል!