Administrator

Administrator

“የአዲስ አበባ ጉዶች” እና “ኢትዮጵያን ማን ይታደጋት” በሚሉት መፅሀፎቹ የሚታወቀው ጋዜጠኛና ደራሲ አቤል አለማየሁ፤ “የእኛ ሰው ገመና” የተሰኘውን ሦስተኛ መፅሀፉን በሳምንቱ መገባደጃ ላይ ለንባብ አብቅቷል፡፡ የተደበቁ እውነቶችን ምፀታዊ ወጎች፣ ማህበራዊና ወሲባዊ ጉዳዮችን የሚዳስሰው መፅሀፉ፤ በተለይም በድንግልና ንግድ፣ በሴት ሰዶማውያውን፣ በልቅ ወሲብና በደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵዊያንን አስገራሚ ገመናዎች በስፋት ያስቃኛል፡፡ ለአፍሪካ ዋንጫ ወደ ደቡብ አፍሪካ ተጉዞ የነበረው አቤል፤ በቆይታው የታዘባቸውን የሀበሻ ልጆች ገመና ዋና የመፅሃፉ ትኩረት ማድረጉን ለአዲስ አድማስ ገልጿል፡፡
በ208 ገፆች የተቀነበበውና በርካታ ማህበራዊ ርዕሰ ጉዳዮችን የሚዳስሰው መፅሀፉ፤ በ49 ብር ከ65 ሳንቲም ለገበያ ቀርቧል፡፡

በኢትዮ ፊልም ኃ/የተ/የግ/ማህበር አስተባባሪነትና ባለቤትነት የሚዘጋጀው “ጉማ ፊልም ሽልማት” የዘንድሮ ፊልሞችን በሽልማት ውድድሩ ለማካተት ምዝገባ መጀመሩን አስታወቀ፡፡ ለሁለተኛው ዙር የሚወዳደሩ የአምና ፊልሞችን ከመጋቢት 29 እስከ ሚያዚያ 3 በጣይቱ ሆቴል መዝግቦ ማጠናቀቁን የገለፀው ኢትዮ ፊልም፤ በሁለተኛው ዙር ውድድር የዘንድሮዎቹን ለማካተት ከሐምሌ 9 እስከ 16 በጣይቱ ሆቴል ምዝገባ እንደሚያካሂድና ለመመዝገብ ፍላጎት ያላቸው ፊልሞች እንዲመዘገቡ ጥሪ አቅርቧል፡፡ ምዝገባው ከቅዳሜ ከሰዓትና ከእሁድ በስተቀር በስራ ቀናት የሚካሄድ መሆኑንም ድርጅቱ በላከው መግለጫ አስታውቋል፡፡

በኢትዮ ፊልም ኃ/የተ/የግ/ማህበር አስተባባሪነትና ባለቤትነት የሚዘጋጀው “ጉማ ፊልም ሽልማት” የዘንድሮ ፊልሞችን በሽልማት ውድድሩ ለማካተት ምዝገባ መጀመሩን አስታወቀ፡፡ ለሁለተኛው ዙር የሚወዳደሩ የአምና ፊልሞችን ከመጋቢት 29 እስከ ሚያዚያ 3 በጣይቱ ሆቴል መዝግቦ ማጠናቀቁን የገለፀው ኢትዮ ፊልም፤ በሁለተኛው ዙር ውድድር የዘንድሮዎቹን ለማካተት ከሐምሌ 9 እስከ 16 በጣይቱ ሆቴል ምዝገባ እንደሚያካሂድና ለመመዝገብ ፍላጎት ያላቸው ፊልሞች እንዲመዘገቡ ጥሪ አቅርቧል፡፡ ምዝገባው ከቅዳሜ ከሰዓትና ከእሁድ በስተቀር በስራ ቀናት የሚካሄድ መሆኑንም ድርጅቱ በላከው መግለጫ አስታውቋል፡፡

ሳሙኤል ጆንሰን “The chief glory of every people a rises from its authors” ይላል። (የአንድ ህዝብ ደማቅ ስምና ታሪክ ከወለዳቸው ፀሐፍትና ደራስያን ጭምር ይፈልቃል እንደማለት ነው) እውነት ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የአንድ ደራሲ የሕይወት ታሪክም የአንድ አገርና ሕዝብ ታሪክም ሲሆን አስተውለናል፡፡ የቅዱስ ያሬድ፣ የአባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ እና የመሳሰሉት ለውስጣችን ታላቅ ኃይል የሚሰጠን የፈጠራ ስራቸው ብቻ ሳይሆን የዚህች ሀገር መሰረት የሆነው የአኗኗር ዘይቤና ፈሊጣቸው ጭምር ነው፡፡
ፑሽኪን ለሩሲያ፣ ብረሽት ለጀርመን፣ ባልዛክ ለፈረንሳይ፣ ሼክስፒር ለእንግሊዝ፣ ሔሚንግዌይ ለአሜሪካ ሕዝብ የታሪኮቻቸው ምንጮች ናቸው፡፡
እነኚህ ደራሲያንና ሌሎችም ሁሉ በፈጠራቸው የሂደት ወቅት አድሏዊ ሆነው አያውቁም፡፡ ሂሳዊ የማይሆኑትና አልፎ አልፎ ሚዛናቸው የሚዛባው መፍረድ ሲጀምሩ ወይም ፍርድ ሲሰጡ ነው፡፡ ታድያ እነዚህን ሁለት የሥነ ጽሑፍ ምሰሶዎች ጠብቀው የተፃፉ ሥራዎችን ሲያስነብበን የኖረን አንድ የጥበብ ሰው አጥተናል፡፡
ሀገራችንና የጥበብ ወዳጆች የሆንን ሁሉ አንድን ዘርፈ ብዙ የጥበብ ሰው አጥተናል፡፡
ሀገራችን ባለቅኔ፣ ተርጓሚና ትሁት መምህር የሆነውን ልጇን አጥታለች፡፡
ከሁሉም ከሁሉም ታላቁን የወግ አባት አጥተናል፡፡ ወግ ለመቀመር የተፈጥሮ ችሎታውን ከዘመናዊ ትምህርት ጋር አጣምሮ የተካነን ሸጋ ደራሲ አጥተናል፡፡ ባሻው ዘውግ አሳምሮ መፃፍ የሚችል ደመና - ገላጭ ትንሽ ፈጣሪ አጥተናል፡፡
ታላቁ የወግ አባት መስፍን ሀብተማርያም ተለይቶናል፡፡
መስፍን ሀ/ማርያም የወግን ምንነት ያስተማረን ብቻ ሳይሆን በተለይ የርዕዮትንና የአብዮትን ዜማ ብቻ በውድም ሆነ በግድ እንድንጋተው በተገደድንበት በዚያን ዘመን ሆነ ዛሬ በዕውቅ የወግ ሥራዎቹ የህይወትን ጐምዛዛነትና ጫና ሊያቀልልን የጣረ የጥበብ ሰው ነው፡፡
መስፍን ሀ/ማርያም ሕይወትን፣ ተፈጥሮን፣ ኑሮንና እነዚህን የሚያጫፍሩትን ዐብይት ክስተቶች ከግለሰብ እስከ ህብረተሰብ ባለው ማንነት ዙሪያ በገሀድ የሚታዩ ድርጊቶችን በመዘርዘር፣ አካባቢያችንና ዘመናችንን በይበልጥም በሰዋዊ ማንነታችን ስንቀበለው በምንችለውና በሚያረካ ኪነታዊ ጉዞ እንድንቃኝ ያደረገ የጥበብ ጀግናችን ነው፡፡
መስፍን ሀ/ማርያም በሥነ - ወግ፤ ቋንቋችንን የፈተሸ፣ ተራ ቃላት የምንላቸውንና ልንዘነጋቸው የተቃረቡ ዘየዎችን መልሰው ነፍስ እንዲዘሩ ያደረገ የቋንቋ ጠቢብ ነው፡፡
የመስፍን ሀ/ማርያም ወጎች ሁላችንም የምናቃቸው በቋንቋቸው ማራኪና በአቀራረባቸው ሚዛናዊነት፣ በምርጥ ምሳሌያቸው፣ በምጣኔያቸውና ማዝናናት በመቻላቸው ነው፡፡ በተለይ ሥነ - ወግ ዋነኛው ባህሪይው ማዝናናት መሆኑን የምንረዳው ከመስፍን ሀ/ማርያም ጽሑፎች ነው ብንል አልተሳሳትንም፡፡
ማዝናናት ሲባል ፈገግ ማስደረግን፣ ማሣቅን የሚያጠቃልል ቢሆንም ከዚህ በዘለለ የመስፍን ሃ/ማርያም ወጐች በተራነት የማይጠበቅ ት.ግ.ር.ም.ት፣ የማይረሳ አድናቆትና “እንዲህ ነው ለካ” የሚያሰኝ የመንፈስ ደስታ እያላበሱንና እነዚህንም ዘና ባልንበት እያዋዙ፣ ዘና ባልንበት ቁምነገሮችን አሾልከው እየወረወሩ፣ ነፍስና ስጋችንን እያጫወቱ፣ ለብዙ ዘመን ያሸጋገሩን ናቸው፡፡
ተውኔት የቤተ-መቅደስና የቤተ መንግስት ዜና መዋዕል ዘጋቢ ብቻ ከመሆን ታላቋ ፊቷን ወደ ዝቅተኛው የሕብረተሰብ ሕይወት እንድታዞር ፋና ወጊውን ሥራ የፈፀሙ እንዳሉ ሁሉ፣ መስፍን ሀ/ማርያም በተለይ በተለይ በሥነ - ወግ ስራዎቹ የድሐውን ሕዝብ ጓዳ - ጐድጓዳ በርብሮ፣ የድሀ ወገናችንን ወግና - ታሪኩን ደስታና - ሀዘኑን ሕይወትና - ሞቱን በቅርበት እንድንረዳ ያጋዘን የዘመናችን የወግ አባት ነው።
ከሁሉም ከሁሉም የወግ አባቱ መስፍን ሃ/ማርያም፣ ጥበብን - እምነቱ፣ ጥበብን ትሁት ተሰጥኦው…ጥበብን ለይስሙላ ተሳልሟት ያለፈ፣ ገባ - ወጣ እያለ የጐበኛት ሳይሆን በጥበብ ፍቅር ወድቆ (ላይፈታት ተክሊል ደፍቶ) ላይፈታት ቁርባን፣ ቃል ኪዳን ቋጥሮ - ሳይፈታት፣ እድሜ ህይወቱን የሰዋላት ሰው ነው፡፡
መስፍን ሀ/ማርያም በ1937 ዓ.ም ከአባቱ ከአቶ ሀ/ማርያም ሞገስና ከእናቱ ከወ/ሮ ደስታ አየለ ተወልዶ ባለፈው እሁድ በ69 ዓመቱ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል፡፡ ጋሽ መስፍን ከ1ኛ እስከ 7ኛ ክፍል ድረስ ሞጆ አንደኛና መለስተኛ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት፣ ከ8ኛ ክፍል ጀምሮ የ2ኛ ደረጃ ትምህርቱን እስካጠናቀቀበት ቀን ድረስ በአንቦ እንዲሁም ከ1958 ዓ.ም እስከ 1962 ዓ.ም በቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ዩኒቨርሲቲ በኢትዮጵያ ቋንቋዎችና ሥነ - ጽሑፍ የመጀመሪያ ዲግሪውን የማዕረግ ተሸላሚ ሆኖ አጠናቋል፡፡
ጋሽ መስፍን በ1964 ዓ.ም ባህር ተሻግሮ ካናዳ ቫንኩቦር በሚገኘው በብሪቲሽ ኮሎምቢያ ዩኒቨርሲቲ ልቦለድን፣ ኢ-ልቦለድን፣ ተውኔትንና ሥነ - ግጥምን የጥናቱ ትኩረት በማድረግ “በፈጠራ ሥነ ጽሑፍ” (creative writing) የማስተርስ ዲግሪውን በ1966 ዓ.ም አግኝቷል፡፡
ጋሽ መስፍን ሀ/ማርያም በሥራው ዓለም ለ3 ዓመታት በኤርትራ በተለይ በአስመራና በምፅዋ የአማርኛ ቋንቋን አስተምሯል፡፡
ከ1963-1976 በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቋንቋዎች ጥናት ተቋም የተለያዩ የሥነ - ጽሑፍ ኮርሶችን ያስተማረ ሲሆን ከዚህ ጐን ለጐን በኢትዮጵያ ሬዲዮና በኩራዝ አሳታሚ ድርጅት ሲሰራ ቆይቷል፡፡
ጋሽ መስፍን በድርሰት ዓለም “የቡና ቤት ሥዕሎች”፣ “አውደ ዓመት”፣ “የሌሊት ድምጾች”፣ እና ሌሎች የወግ መጽሐፍትን አበርክቶልናል፡፡ “አዜብና ሌሎች አጫጭር ልቦለዶችን”፣ እንዲሁም የተረት መጻሕፍትን አሳትሟል፡፡ “በቆንጆ ልጅ ፈተና” ሥነ - ግጥሙም እናውቀዋለን፡፡
ጋሽ መስፍን ወደ 550 የሚጠጉ የተለያዩ መጣጥፎችን በጋዜጦችና በመጽሔቶች ላይ በማውጣት ከዘመን ዘመን እያጫወተና እያስተማረ አሸጋግሮናል፡፡ ጋሽ መስፍን ከድርሰቶቹ በተጨማሪ ሃያሲም ነበር፡፡ ጋሽ መስፍን ሳይቤሪያ በዘመተው የኢትዮጵያ የሰላም አስከባሪ ጦር ጋር በመዝመት በአስተርጓሚነት አገልግሏል፡፡
የአብራኩ ክፋይ የሆኑ የሁለት ወንድ ልጆችና የአራት ሴት ልጆች አባትም ነው፡፡
ጋሽ መስፍን በመጨረሻዎቹ የእስትንፋስ ሰዓታቱ ልጁን ሀ/ማርያም መስፍንንና ቃልኪዳን መስፍንን አሳድጉልኝ፣ ለወግ አብቁልኝ እያለ ሲወተውትና ሲማፀን ነው ሕይወቱ ያለፈችው፡፡
ጋሽ መስፍን The Merchant of Fear የምትሰኝ አጭር ልቦለዱንና ሌሎች ያልታተሙ ሥራዎቹ ለንባብ ይበቁለት ዘንድ ሲማፀን ቆይቶ ለአንዴና ለሁሌም ተለይቶናል፡፡
ይህ ሁላችንም የምንወደው፣ ይህ ትሁት፣ ይህ ቅን፣ ይህ የኑሮ ጫና ሳይበግረው ዘመኑን ሙሉ ያገለገለንን ታላቅ የጥበብ ሰው፣ የመጨረሻ ሰዓት ኑዛዜውን ያገለገለው የሀገራችን ህዝብና የጥበብ ወዳጆች ሁሉ እውን እንደሚያደርጉት የፀና እምነቴ ነው፡፡
በመጨረሻም በዚህ በታላቁ የጥበብ ሰውና የወግ አባት በሆነው በደራሲ መስፍን ሃ/ማርያም የቀብር ስነስርዓት ላይ ተገኝታችሁ ቤተሰቦቹን ያጽናናችሁትን ሁሉ በልጆቹ፣ በዘመዶቹ፣ በኢ.ደ.ማ አባላት፣ በራሴና በጥበብ ወዳጆች ሁሉ ስም ላመሰግን እወዳለሁ፡፡
ታላቁ አምላክ ይህን ፍዳውን ሁሉ በምድር ዓለም የጨረሰን የጥበብ አባት መስፍን ሃ/ማርያምን ነፍሱን በገነት ያሳርፋት ዘንድ እንለምናለን፡፡
አመሰግናለሁ

          በህገወጥ የምግብ፣ የመድሃኒትና የጤና አገልግሎት ላይ ያተኮረ የህዝብ ንቅናቄ መድረክ በደሴ፣ በአላማጣና በሽሬ ከተሞች ባለፈው ግንቦት ወር ተካሂዷል፡፡
የህዝብ ንቅናቄ መድረኩ በተለይ በህገወጥ የምግብና መድሃኒት ንግድ ምንነትና የሚያስከትለው ችግር ላይ ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችና ባለድርሻ አካላት ጋር በሰፊው ምክክር ለማድረግና ህብረተሰቡን የቁጥጥሩ ባለቤት ለማድረግ ታልሞ የተካሄደ መድረክ ነው፡፡
የኢትዮጵያ የምግብ፣ የመድሃኒትና የጤና ክብካቤ አስተዳደርና ቁጥጥር ባለስልጣን፤ ከህገወጥ የምግብና የመድሃኒት ዝውውር ጋር በተያያዘ በጣም ተጋላጭ በሆኑና በተመረጡ ቦታዎች ላይ የህዝብ ንቅናቄ መድረክ ያካሂዳል፣ በቅርቡም በሶስት ከተሞች ላይ የተከናወኑት መድረኮች የዚህ እንቅስቃሴ አካል ናቸው፡፡
በውይይት መድረኮቹ የጤናና ጤና ነክ አገልግሎትና ግብአት ከየት ወዴት፣ ህገወጥ የምግብና የመድሃኒት ንግድና የጤና አገልግሎት ቁጥጥር ነባራዊ ሁኔታ፣ የምግብና የመድሃኒት ህገወጥ ዝውውር አጠቃቀምና ጤና አገልግሎት ክልላዊ ገጽታ፣ ህገወጥ የምግብ፣ የመድሃኒትና ጤና አገልግሎት እንቅስቃሴን በጋራ ለማስወገድ ቀጣይ አቅጣጫ (የጋራ ዕቅድ) የሚሉ ሰነዶች የቀረቡ ሲሆን ለተሳታፊዎች ጥያቄና አስተያየትም በቂ ጊዜ ተሰጥቶ በርካታ ሃሳቦች ተንሸራሽረዋል፡፡
በጋራ ምክክር መድረኩ ትኩረት አግኝተው ከተነሱት ርዕሰ ጉዳዮች አንዱ “ህገወጥ የምግብ፣ መድሃኒት ንግድና የጤና አገልግሎት ቁጥጥር ስራዎች ነባራዊ ሁኔታ” በሚል በባለስልጣን መ/ቤቱ የኢንስፔክሽንና ቅኝት ዳይሬክቶሬት የቀረበው ገለፃ ሲሆን አላማውም በሀገራችን በምግብ፣ በመድኃኒትና በጤና አገልግሎት ዙሪያ ያለውን ህገወጥ እንቅስቃሴ በማስቃኘት በቀጣይ ህገወጥ እንቅስቃሴን በመከላከሉ ስራ ሁሉም የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያበረክትና ንቁ ተሳትፎ እንዲኖረው ለማነቃቃት ነው፡፡
አግባባዊ የምግብ ንግድ ስራ
ማንኛውም ምግብ ባለስልጣኑ ወይም የክልል ጤና ጤና ተቆጣጣሪ አካል ሳይፈቅድ መመረት፣ ወደ ሀገር ውስጥ መግባት፣ መላክ፣ መዘጋጀት፣ መከማቸት፣ መከፋፈል፣ መጓጓዝ ወይም ለሽያጭ ወይም ለህብረተሰቡ ሊቀርብ አይችልም፡፡
ማንኛውም ምግብ ጥራቱና ደህንነቱ ተጠብቆ መመረት፣ መታሸግ፣ ገላጭ ጽሑፍ መለጠፍ፣ መከማቸት፣ መጓጓዝና መሸጥ አለበት፡፡
በማንኛውም ምግብ ላይ መጠኑን ወይም ክብደቱን ለመጨመር፣ መልኩን ለማሳመር ወይም ለሌላ ተመሳሳይ ዓላማ ሲባል የሰውን ጤና ሊጐዳ ወይም የምግቡን ጥራትና ደህንነት ሊያጓድል የሚችል ባእድ ነገር መጨመር ወይም መቀላቀል የተከለከለ ነው፡፡
ማንኛውም ለህብረተሰቡ ሽያጭ አገልግሎት የሚውል የታሸገ ምግብ በአማርኛ ወይም እንግሊዝኛ ቋንቋ የተፃፈ ገላጭ ጽሑፍ ሊኖረው ይገባል፡፡
የምግቡ ስም
በምግቡ ውስጥ ያለው ይዘት
የምግቡ አምራች ድርጅት ስምና ሙሉ አድራሻ
የምግቡ መለያ ቁጥር (Batch no)
ምግቡ የተመረተበትና የመጠቀሚያ ጊዜው የሚያበቃበት ቀን
አግባባዊ የመድሃኒት ንግድ ስራ
ማንኛውም መድኃኒት ደህንነቱ፣ ፈዋሽነቱና ጥራቱ ተገምግሞ በአስፈጻሚ አካሉ ሳይመዘገብ በጥቅም ላይ ሊውል አይችልም፣
ማንኛውም መድሃኒት ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባት፣ ለማምረትና ለህብረተሰቡ ሽያጭ ለማዋል መጀመሪያ በባለስልጣኑ በብሔራዊ የመድሃኒት መዘርዝር ውስጥ በመካተት ተመዝግቦ የገበያ ፈቃድ ማግኘት አለበት፡፡
የማንኛውም መድሃኒት ገላጭ ጽሑፍ፡-
የመድሃኒቱ ሳይንሳዊ ስም
በመድሃኒቱ ውስጥ ያለው ይዘት
የመድሃኒቱ አምራች ድርጅት ስምና ሙሉ አድራሻ
መድሃኒቱ የተመረተበትና አገልግሎት የሚያበቃበት ጊዜ
በቀን መወሰድ ያለበት መጠንና የአወሳሰድ ሁኔታ…ሊያካትት ይገባል፡፡
አግባባዊ የጤና አገልግሎት አሰጣጥ
ማንኛውም የጤና ተቋም በሀገሪቱ የተቀመጠውን የጤና አገልግሎት ደረጃ ያሟላ መሆን አለበት
ከሚመለከተው የጤና ተቆጣጣሪ አካል ህጋዊ እውቅና የተሰጠው መሆን ይኖርበታል
ለሚሰጠው አገልግሎት የሚያስፈልጉ በቂ የህክምና መሳሪያዎች እንዲሁም ብቃታቸውና ሙያዊ ስነ ምግባራቸው የተረጋገጠ የጤና ባለሙያዎች ሊኖሩት ይገባል፡፡
ባለስልጣን መ/ቤቱ ከላይ ከተገለፀው አግባባዊ አካሄድ በተቃራኒ የሚካሄዱ ህገወጥ የምግብ፣ የመድሃኒትና የጤና አገልግሎቶችን ይቆጣጠራል፣ በአዋጅ (661/2002) በተሰጠው ስልጣንና ተግባር መሰረት፣ አስተዳደራዊና ህጋዊ እርምጃም ይወስዳል፡፡ ለአብነት ያህል ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከደንብና አግባብ ውጪ ሲሰሩ በነበሩ ላይ የተጣሉ ቅጣቶችን ማየት ይቻላል፡፡
ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገቡ የተከለከሉ ምርቶች (ባለፉት 9 ወራት)
የምርት ዓይነት         ብዛት በቶን
ምግብ             45 ቶን
መድሃኒት            27 ቶን
ኮስሞቲክስ         14 ቶን
በቁጥጥር ወቅት የተገኙና ተገቢውን መስፈርት ሳያሟሉ ቀርተው የተወገዱ ምርቶች
የምርት ዓይነት         የድርጅቶች ብዛት
ምግብ             127 ድርጅቶች
መድሀኒት             130 ድርጅቶች
አስተዳደራዊ እርምጃ የተወሰደባቸው ድርጅቶች
705 የምግብ አስመጭዎችና ጅምላ አከፋፋይ ድርጅቶች ላይ ቁጥጥር ተካሂዶ 90 ድርጅቶች የብቃት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀታቸውን እንዲመልሱ ተደርጓል፡፡ 8 ድርጅቶች ላይ የእገዳ አስተዳደራዊ እርምጃ ተወስዷል፡፡
በ321 መድሃኒት አስመጪና አከፋፋይ ድርጅቶች ላይ ቁጥጥር ተካሂዶ በ24 ድርጅቶች ላይ ከማስጠንቀቂያ ጀምሮ እስከ የብቃት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ስረዛ ድረስ አስተዳደራዊ እርምጃ ተወስዷል፡፡
በህዝብ ንቅናቄ መድረኮቹ ላይ የዞንና የወረዳ ከፍተኛ አመራሮች፣ የክልል ጤና ቢሮ ሃላፊዎች፣ የክልል ተቆጣጣሪ አካላት፣ የፍትህ አካላት (የፍርድ ቤትና ፖሊስ ተወካዮች) የወጣትና ሴት አደረጃጀቶች፣ ከተለያዩ ሴክተር መ/ቤቶች የተውጣጡ ባለሙያዎች (ከገቢዎችና ጉምሩክ፣ ከንግድ ቢሮ፣ ከንግድ አሰራርና ሸማቾች ጥበቃ ባስልጣን….) ተሳታፊዎች ነበሩ፡፡ መሰል የምክክር መድረኮች ችግሮችን በጋራ ነቅሶ ጠቃሚ የመፍትሔ ሃሳቦችን ለመስጠት የሚኖራቸው ፋይዳ ከፍተኛ ነው፡፡ በተለይም በአሁኑ ጊዜ የመላው ማህበረሰብ ችግር የሆነውንና ውስብስብ እየሆነ የመጣውን ህገወጥ የምግብና መድሃኒት ዝውውር ለመግታት፣ የህዝብ ንቅናቄ መድረኮችን ማዘጋጀት የግድ ይላል፡፡ የጤና ጠንቅ የሆነውንና በሁላችንም ህይወት መንገድ ላይ የቆመውን ህገወጥ የምግብና የመድሃኒት ንግድና ዝውውር መግታት የሚቻለው ህብረተሰቡ የቁጥጥሩ ባለቤት መሆን ሲችል ብቻ ነው፡፡ በዚህ ረገድ ባለስልጣን መ/ቤቱ እያደረገ ያለው እንቅስቃሴ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላትን ብሎም የመላው ማህበረሰብን የተጠናከረ ድጋፍ ይሻል፡፡
ህብረተሰቡ ጥራቱና ደህንነቱ የተጠበቀ ምግብና ጥራቱ፣ ደህንነቱና ፈዋሽነቱ የተረጋገጠ መድሃኒት በመጠቀም ጤናውን ሊጠብቅ ይገባል፡፡ እንዲሁም በምግብ፣ በመድሃኒትና በጤና አገልግሎቶች ላይ ማናቸውም ዓይነት ህገወጥ እንቅስቃሴ ሲገጥመው ለሚመለከተው ተቆጣጣሪ አካልና ለፖሊስ በመጠቆም መተባበር አለበት፡፡
ህገወጥ የምግብና መድሃኒት ንግድና የጤና አገልግሎትን በጋራ እንቆጣጠር!!!
(የኢትዮጵያ የምግብ፣ የመድሃኒትና የጤና ክብካቤ አስተዳደርና ቁጥጥር ባለስልጣን የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ)

Saturday, 19 July 2014 12:01

የጸሐፍት ጥግ

ፀሃፊዎች መድኃኒት አያዙም፤ ራስ ምታት እንጂ።
ቺኑዋ አቼቤ
(ናይጄሪያዊ ደራሲ፣ ገጣሚና ወግ ፀሃፊ)
ትንሽ ልጅ ሳለሁ ውሸታም ነበር የሚሉኝ፡፡ አሁን ስድግ ግን ፀሃፊ ይሉኛል፡፡
አይሳክ ባሼቪስ ሲንገር
(ትውልደ-ፖላንድ አሜሪካዊ ፀሃፊ)
ተሰጥኦ ብቻውን ፀሃፊ አያደርግም፡፡ ከመፅሃፉ ጀርባ ሰው መኖር አለበት፡፡
ራልፍ ዋልዶ ኤመርሰን
(አሜሪካዊ ገጣሚና ወግ ፀሃፊ)
ፀሃፊ በመሞት መሆኑን ማሰቡ ጥሩ ይመስለኛል፡፡ ጠንክሮ እንዲሰራ ያተጋዋል፡፡
ቴኒሲ ዊሊያምስ
(አሜሪካዊ ፀሃፌ ተውኔት)
ቶኒ ሞሪሰን ቴሌቪዥን እንደማትመለከት በቅርቡ አነበብኩ፡፡ እርሷ ከአሜሪካ ባህል ሙሉ በሙሉ ተፋታ ለምንድነው የእሷን መፅሃፍ የማነበው
ካሚሌ ፓግሊያ
(አሜሪካዊ ምሁርና ደራሲ)
እነዚህን መተየቢያ ማሽኖች ያስቀመጥኳቸው በዋናነት በአንድ ወቅት ፀሃፊ እንደነበርኩ ራሴን ለማስታወስ ነው፡፡
ዳሺል ሃሜት
(አሜሪካዊ የወንጀል ታሪኮች ፀሃፊ)
ሌንሱ ክፍት የሆነ ካሜራ ነኝ፡፡ ዝም ብሎ የሚቀርፅ፣ የማያስብ፡፡
ክሪስቶፈር አይሸርውድ
(ትውልደ-እግሊዛዊ አሜሪካዊ ፀሃፊ)
ግን ማነው አለቃ መሆን ያለበት? ፀሃፊው ወይስ አንባቢው?
ዴኒስ ዲዴሮት
(የፈረንሳይ ኢንሳይክሎፒዲያ አዘጋጅና ፈላስፋ)
የአሜሪካ ጸሃፊዎች ጥሩ ሳይሆን ታላቅ መሆን ይፈልጋሉ፡፡ ሁለቱንም ግን አይደሉም፡፡
ጎሬ ቪዳል
(አሜሪካዊ ደራሲና ወግ ፀሃፊ)
ህፃናትን የምትወድ ከሆነ ከደራስያን ጋር መግባባት ከባድ አይደለም፡፡
ማይክል ጆሴፍ
(እንግሊዛዊ አሳታሚ)

Saturday, 19 July 2014 11:45

የፖለቲካ ጥግ

የሥራ ማቆም አድማን አልታገስም፡፡ እኔ የሥራ ማቆም አድማ ባደርግና ደሞዝ አልፈርምም ብል ሰራተኞቼ ምን ይሉኛል?
አላን ቦንድ
(አውስትራሊያዊ የቢዝነስ ሥራ አስፈፃሚ)
ህገ-መንግስታዊው መንግስት ጥቃት እየተሰነዘረበት ነው - አጠቃላይ አድማው ለፓርላማው ፈተና ነው፡፡ የሥርዓት አልበኝነትና የጥፋትም ጎዳና ነው፡፡
ስታንሌይ ባልድዊን
(የእንግሊዝ ጠ/ሚኒስትር)
ሁላችንም ካልተባበርነው በቀር ማንም ሰው አገርን ሙሉ ሊያሸብር አይችልም፡፡
ኢዲ ሙሮው
(አሜሪካዊ ጋዜጠኛ)
በሌላው ላይ የማዘዝ ሥልጣን ያለው ሰው ሁሉ ጨቋኝ ነው፡፡
ፍራንሲስኮ ፒዋይ ማርጋል
(ስፔናዊ ፖለቲከኛና ደራሲ)
ሰዎች ቄሳሮችንና ናፖሊዮኖችን ማምለክ እስካላቆሙ ድረስ ቄሳሮችና ናፖሊዮኖች መከራ ሊያበሏቸው መነሳታቸው አይቀርም፡፡
አልዶስ ሁክስሌይ
(እንግሊዛዊ ደራሲና ወግ ፀሐፊ)
ራሱን እንዲወደድ ማድረግ ያቃተው፣ ራሱን እንዲፈራ ማድረግ ይሻል፡፡
ዣን ባንቲስት ራሲን
(ፈረንሳዊ ፀሐፌ ተውኔት)
ጭቆና ሁልጊዜ ከነፃነት የተሻለ የተደራጀ ነው፡፡
ቻርልስ ፒሬ ፔለጉይ
(ፈረንሳዊ ፀሐፊና ገጣሚ)
በጨቋኝ ሥርዓት ውስጥ ከማሰብ ይልቅ መተግበር ይቀላል፡፡
ሃና አሬንድት
(ትውልደ - ጀርመን አሜሪካዊ ፈላስፋና የታሪክ ምሁር)
ሰውየውን እየጨቆንክ ለታሪኩ፣ ለሰዋዊነቱና ለስብዕናው ዕውቅና መስጠት አትችልም፡፡ ስለዚህ እነዚህን ነገሮች በዘዴ ከእሱ ላይ መውሰድ አለብህ፡፡ እናም ይሄ ሰው በታሪክ ውስጥ ያለውን ሚና በተመለከተ በመዋሸት ትጀምራለህ፡፡
ጆን ሄንሪክ ክላርክ
(አሜሪካዊ የታሪክ ባለሙያና የትምህርት ሊቅ)
ሁሉም ዘመናዊ አብዮቶች የተጠናቀቁት የመንግስትን ሥልጣን በማጠናከር ነው፡፡
አልበርት ካሙ
(ትውልደ - አልጀርያ ፈረንሳዊ ደራሲና ድራማ ጸሃፊ)

የ”ዋቢ የግል ፕሬስ አሳታሚዎች የዘርፍ ማኅበር በኢትዮጵያ” መግለጫ


መሰባሰብ ከጀመረ ሁለት ዓመት የሆነውና ሕጋዊ ዕውቅና በሚያዝያ 30 ቀን 2006 ዓ.ም. ያገኘው “ዋቢ የግል ፕሬስ አሳታሚዎች የዘርፍ ማኅበር በኢትዮጵያ” በተደጋጋሚ ስብሰባዎቹ ከሕዝቡና ከደንበኞቹ ለአባል ጋዜጦችና መጽሔቶች የሚቀርቡትን ሐሳቦች አስተያየቶችና ቅሬታዎች ሲመረምርና ሲወያይበት ሰንብቷል፡፡ በዚህ ሳምንት ስብሰባውም ለአንባቢዎች መልስ ለመስጠት ይህን መግለጫ አውጥቷል፡፡
ከሚጻፈው ሐሳብ ጋር ይስማማ አይስማማ ሌላ ነገር ሆኖ በጋራ አንባቢው ኅብረተሰብ የሚያቀርበው ቅሬታ አለ፡፡ ቅሬታውም “ምነው በወቅቱ አትወጡም?”፣ ምነው ጊዜ ያለፈበት ወሬ ትሰጡናላችሁ፣ ምነው ጠቆረ፣ ምነው ባለ ቀለም የነበረው ጠፋ፣ ምነው ተዳከማችሁ፣ ምነው ጊዜ ያለፈበት የሥራና የጨረታ ማስታወቂያ ታስነብቡናላችሁ ወዘተ. ይላል፡፡
ከጋዜጣና ከመጽሔቶች ጋር በማስታወቂያና በስፖንሰርሺፕ የሚገናኝ አካልም ማስታወቂያችን በወቅቱ አልወጣም፣ ጊዜ አልፎበታል፣ ጭራሽ ባለቀለም የነበረው ጥቁርና ነጭ ሆኗል፣ ጭራሽ ቀለሙ ጠቁሮና ደብዝዞ አይታይም አይነበብም ለመክፈል እንቸገራለን ይላል፡፡
“ዋቢ የግል ፕሬስ አሳታሚዎች የዘርፍ ማኅበር በኢትዮጵያ” በማኅበሩ ተደጋጋሚ ስብሰባ እነዚህን በዝርዝርና በጥልቀት ተወያይቶ የሕዝብ ቅሬታና የደንቦች አቤቱታ እውነት እንደሆነ ተቀብሏል፤ አምኗል፡፡ ችግሩ ምን ላይ እንደሆነም ለሕዝብ ግልጽ ለማድረግ ይፈልጋል፡፡
በተከታታይና በተለያዩ መንገዶች በፕሬስ ሕትመቶች ላይ እየታየ ያለው ችግር በዋነኛነት ከማተሚያ ቤት ጋር የተየያዘ ነው፡፡ አብዛኛዎቻችን በብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤት እናሳትማለን። አንዳንዶቻችን በሌሎች ማተሚያ ቤቶች እናሳትማለን።
በተደጋጋሚ የሚታየው የማተሚያ ቤት ችግር አንዱ የሕትመት ማሽን ተበላሸ እየተባለ ጋዜጦችና መጽሔቶች በወቅቱ እንዳይወጡ መደረጉ ነው፡፡ የፈተና ወረቀት እየታተመ ስለሆነ ጋዜጣና መጽሔት በወቅቱ አይታተምም የሚልም ሌላው ምክንያት ነው፡፡ በእነዚህ ምክንያቶች የፕሬስ ውጤቶች ቅዳሜና እሑድ መውጣት ያለባቸው ረቡዕና ሐሙስ ሲወጡ ይታያል፡፡ ይህ ሁኔታ የፕሬስ ቢዝነሱን በእጅጉ እየጐዳ ነው፡፡
ሌላው ችግር ገፅ ቀንሱ ወረቀት የለም ቀለም የለም የሚል ነው፡፡ ይህም ጋዜጦችና መጽሔቶች አንባቢዎች ከሚፈልጉትና ደንበኞች ከተዋዋሉት ጋር የሚሄድ ቁጥር እንዳያገኝ እያደረገና ሰውን እየጐዳ ነው፡፡
ቀለም የለም፣ ፕሌት የለም እየተባለ መልካችሁንና ይዘታችሁን ቀይሩ የሚል ጫናም ከማተሚያ ቤቶች እየመጣ ነው፡፡ ይህም በእጅጉ ቢዝነሱን እየጐዳ ነው፡፡
በተለይ በተለይ ደግሞ ደንበኞችን አክብሮና ተወያይቶ አወያይቶ የገበያ ዋጋን ከመወሰን ይልቅ በድንገት ዋጋ ተጨምሯል እያሉ ከፍተኛ የገንዘብ ኪሣራና ጫና መፍጠር በእጅጉ አስጊና አሳሳቢ ሁኔታ ሆኗል፡፡ የጥራት ጉድለትና ጋዜጦችና፣ መጽሔት ፎቶዎቻቸውና ጽሑፎቻቸው መነበብ በማይችሉበት ሁኔታ ተጨማልቆ መውጣትም ሌላው አስፈሪና አሳፋሪ፣ ቢዝነስን በእጅጉ እየጐዳ ያለ ተግባር ሆኗል፡፡
የተከበረው አንባቢ ኅብረተሰብና የቢዝነስ አጋራችን የሆነው አካል ችግራችን ከላይ እንደተጠቀሰው ከአቅማችን በላይ መሆኑን እንዲገነዘብልን በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡ የምንጠቀምበት ማተሚያ ቤት የራሱ የፕሬሱ አይደለምና ‹‹ዋቢ የግል ፕሬስ አሳታሚዎች የዘርፍ ማኅበር በኢትዮጵያ›› የማተሚያ ቤትን ችግር የራሱ ማተሚያ ቤት በማቋቋም ለመፍታት እየተንቀሳቀሰ ነው፡፡ ሆኖም ግን ይህም በአጭር ጊዜ እውን ለማድረግ ቀላል ስለማይሆን ይህ መፍትሔ እስኪገኝ ድረስ ከመንግሥት ጋር ሆኖ ብርሃንና ሰላምና ሌሎች ማተሚያ ቤቶች የሚፈጥሩትን ችግር ለመፍታት ከፍተኛ እንቅስቃሴ እያደረገ ነው፡፡
በቅርብም ችግሩን በጋራ ዓይተንና ተወያይተን በጋራ መፍትሔ ለማስቀመጥ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለ ማርያም ደሳለኝን ለማነጋገር በሚመለከተው አካል በኩል የቀጠሮ ቀን ጥያቄ አቅርበናል፡፡
እኛም የማኅበሩ አባላት የፕሬሶችን ችግር ለመፍታት ራሳችን ማድረግ የሚገባንን ሁሉ ለማድረግና ድክመቶቻችንንም፣ ችግሮቻችንንም አስወግደን በመጠናከር የሚገባንን ሁሉ ለማድረግ ተነስተናል፡፡ ከመንግሥት ጋር ሆነን ችግሩን ለመፍታትም መንግሥትን ጠይቀናል፡፡
ይህ እንዲህ ሆኖ ሕዝብም ዋነኛውና ወሳኙ አካል ስለሆነና የቆምንለት ዓላማ ተገቢ መረጃ ለሕዝብ በወቅቱና በጥራት መስጠትና ሕዝብን ማገልገል ስለሆነ ሕዝብም ችግራችንን ተረድቶ ይበልጥ የምናገለግልበትን አቅም እንድንገነባ በትዕግስት ከጐናችን እንዲቆም እንጠይቃለን፡፡
ዋቢ የግል ፕሬስ አሳታሚዎች የዘርፍ ማኅበር በኢትዮጵያ
            ሐምሌ 11 ቀን 2006 ዓ.ም.          

(ኣፀቢቕና ኣይንበኣስ፣ እንተ ተዓረቕና ከይንጠዓስ)

አንድ የአሜሪካ ጋዜጣ ላይ የሚከተለው ሰፍሯል፡፡ የሚከተለው ኩባንያ (መሥሪያ ቤት) አባል መሆን ይፈልጋሉ?” በሚል ርዕስ፡፡ ነገሩ ዕውነት ነው፡፡ ግን ላታምኑ ትችላላችሁ፡፡
ይህ ኩባንያ ከ500 ጥቂት ከፍ ያሉ ሠራተኞች አሉት፡፡
ኩባንያው የሚከተለው ስታቲስቲክስ አለው፡-
ካሉት አባላት 29ኙ በሚስቶቻቸው ላይ ግፍ በመፈፀም ተከሰዋል፡፡
7ቱ በማጭበርበር ወንጀል ተከሰው ታስረው ነበር፡፡
19ኙ የተሳሳተ ቼክ በፈረም ተከሰዋል፡፡
117ቱ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ሁለት የንግድ ተቋማትን ኪሣራ ላይ ጥለዋል፡፡
3ቱ አስገድደው ደፍረዋል፡፡
71ዱ ከዚህ ቀደም ባደረሱት ጥፋት ክሬዲት ካርድ ማግኘት አይፈቀድላቸውም፡፡
14ቱ ከአንደዛዥ ዕፅ ጋር በተያያዘ ክስ ቀርቦባቸዋል፡፡
8ቱ ከሱቅ ዕቃ ሲመነትፉ ተይዘው ታስረዋል፡፡
21ዱ በአሁኑ ጊዜ ክሳቸውን ለመከላከል ፍ/ቤት ይመላለሳሉ፡፡
ባለፈው ዓመት ብቻ 84ቱ ጠጥተውና ሰክረው በመንዳት ታስረዋል፡፡
እነዚህን ሁሉ ያቀፈው ይህ ድርጅት፤ የትኛው ይመስላችኋል?
ምናልባት የአሜሪካ ብሔራዊ ባንክ ነው ትሉ ይሆናል፡፡ ተሳስታችኋል (ሊሆን አይችልም ማለት ግን አይደለም)
አላወቃችሁም? ተስፋ ቆረጣችሁ?
መልሱ ምን መሰላችሁ?
535 አባላት ያሉት የዩናይትድ ስቴትስ ኮንግሬስ ነው፡፡
በየአመቱ በመቶዎች የሚቆጠሩ ህጐችን የሚያወጡትና ሁላችንንም ቀጥ - ለጥ ብላችሁ ተገዙ የሚሉን እነዚሁ የግብዝ ጥርቅሞች ናቸው፡፡
*   *   *
አመራሮች “የራስህን ዐይን ጉድፍ ሳታይ የሌላውን ጉድፍ ለማውጣት አትሞክር” የሚለውን፣ ራስን የማፅዳት መርህ የማወቅ ኃላፊነት አለባቸው፡፡ በሴቶች ላይ ያለን የበላይነት አባዜ ሳይወገድ፣ እጃችን ከማጭበርበር ወንጀል ሳይፀዳ፣ በየንግድ ተቋማቱ ውስጥ የተነካካንበትን ሁኔታ ሳናጠራ፤ ከተለያዩ ሱሶች የተገላገልን ሳንሆንና ከአልባሌ ወንጀሎች ክስ የራቀ የኋላ ታሪክ ሳይኖረን፤ ሌሎችን መምራት አዳጋች መሆኑ መቼም፤ ፀሐይ የሞቀው ሀቅ ነው፡፡ በትምህርት ራስን ማብቃት ዋና ነገር ቢሆንም፤ በሥነ-ምግባራዊና ሥነ-ሰብዓዊ ክሂል ካልተደገፈ ጉዟችን ጎዶሎ ይሆንብናል፡፡
ዛሬ ሀገራችን የምትፈልጋቸው አያሌ ባለሙያዎች፣ በተለይ በአመራር ደረጃ ያሉቱ፤ ከትምህርታቸው በተጓዳኝ ልዩ ልዩ ንጥረ-ባህሪ ያላቸው ሊሆኑ ይገባል፡፡ ይህ ክሂል ከነዚህ ውስጥ የሚከተሉትን ያገናዘበ ቢሆን ይበጃል፡፡
ልዩነትን መወያየት የሚፈልግ ሰው ያስፈልጋል፡፡ (a bone to pick እንዲሉ)
መቼም ቢሆን ድብቅ ፍላጐት ያለው ሰው ጣጣ ነው፡፡ (an axe to grind እንዲሉ) ከዚያ ይሰውረን፣ የሚል ግልጽ ሰው ያሻናል፡፡
አንድ የተበላሸ ፍሬ ሙሉውን በርሜል ያበላሸዋል፡፡ አንድ ሞሳኝ ሰውም እንደዚያው ሁሉንም ሰው ያበላሻል፡፡
የተሳሳተው ዛፍ ላይ መጮህ (Barking up the wrong tree እንዲሉ) የተሳሳተ ጉዳይ ላይ ከተሳሳተ ሰው ጋር ማውራት ጅልነት መሆኑን የተገነዘበ የፖለቲካ መሪ፤ ያሻናል፡፡
ፈረንጆቹ ወይ ህፃን ወይ አዋቂ አለመሆን አለመታደል ነው ይሉናል (Between hay and grass እንዲሉ) ይህንን ልብ ያለ የፖለቲካ ሰው ይስጠን፡፡
ታገስ (Hold your horses ነው ነገሩ) ትልቅ የህይወት መርህ ነው፡፡ ዕለት ሠርክ ትዕግስት የሚጠይቁ አያሌ ውጣ ውረዶች አሉ፡፡ እነዚያን ለመወጣት የሚችል ሰው ይባርክልን፡፡
ሁሉን ነገር (kit and caboodle እንዲሉ) አጠቃሎ የማየት አስተውሎት ያለው የበሰለ ተቃዋሚ ይሰጠን ዘንድ እንፀልይ፡፡
“ከፈረሱ አፍ ስማ” የሚለው መርህ የገባቸው ሰዎች ያስፈልጉናል፡፡ በወሬ፣ በሃሜት፣ በጥቆማ፣ በስማ - በለው ከሚወቅሱና ከሚከሱ ይገላግሉናልና፡፡
Iron in the fire ይላሉ ፈረንጆች፡፡ ሁሉ ቦታ ጥልቅ ማለት አይገባም፡፡ ሁኔታዎችን ከማባባስና የከፉ ከማድረግ በቀር ምንም የረባ ዕድገት አናመጣም - በየነደደበት በመዶል፡፡
You aint the only duck in the pond ይህ ማለት በቁም ትርጉሙ ስናየው ኩሬው ውስጥ ያለኸው ዳክዬ አንተ ብቻ አይደህም የሚል ሲሆን፤ አገሩ ሁሉ ስላንተ የሚያወራ እንዳይመስልህ ማለትም ነው፡፡
ከላይ የጠቀስናቸውን ያህል ጠባያት በአግባቡና በቅጡ ከተቀዳጀን፤ ለመጪው ምርጫ፣ ፋይዳ መኖር ለዕለት - ተዕለት ዲሞክራሲያዊ አሂዶአችን፣ መሳካት ለፍትሕ - ርትዕ ርሃባችን መወገድ፣ ለመልካም አስተዳደር ዕውነተኛ ገጽታችን መበልፀግ፣ ለእጅ አመላችንና ለዕምነት ክልስነታችን መወገድ መጠነኛ አስተዋጽኦ ያደርግልናል፡፡
 “በሀገራችን ምርጫ በመጣ ሰዓት መንግስት ደግ ይሆናል” የሚል ሐሜታ ሁሌ ይነገራል። መንግስትም ይሰማል፡፡ ህዝብም ያውቃል፡፡ ይህን ሁኔታ ለመለወጥ ጥረት ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ በእርግጥም ዲሞክራሪያዊት ሂደት መሆኑን ማመን አለብን፡፡ ተለዋጭ ሁኔታን መቋቋም ያስፈልጋል፡፡
እነሆ ይሆኑናል፣ ይበጁናል፣ የምንላቸውን ሰዎች ስንመርጥ ሙያ - ከምግባር፣ ልብ -ከልቦና ያላቸው ቢሆን መልካም ነው፡፡ “አስወርተህ ሹመኝ፣ ዘርፌ አበላሃለሁ” የሚሊ መሆን የለባቸውም፡፡ ገዢ ፓርቲና ተገዢ ፓርቲ የጋራ የጨዋታ ሜዳ፣ የጋራ የጨዋታ ሕግ፣ ባላቸው አገር ደግሞ ሁነኛ ምርጫ ይኖራል ብሎ ማሰብ፣ ጤናማ ላገር ማሰብ ነው፡፡ አዎንታዊነት ነው! የሻከረው ሊላግ፣ የከረረው ሊላላ፣ የጎደጎደው ሊሞላ ይችል ዘንድ የሁሉም ቅን ልቦና ያስፈልጋል፡፡ እስከመቼ ተሸካክረን? እስከመቼ ተቆሳስለን? እስከመቼ ተወነጃጅለን? እርስ በርስም ሆነ፣ ጎራ ለይተንስ እስከመቼ ተጠላልፈን? እስከመቼስ ብቻዬን እሰራዋለሁ ብለን እንዘልቀዋለን፡፡ ዕውነት ለሀገር ብለን ከሆነ ደፋ ቀና የምንለው፣ ዕውነት ለህዝብ ብለን ከሆነ በፖለቲካ የምንሞራረደው፤ በጠላትነት መፈራረጅና ለመጠፋፋት የምንሽቀዳደምበት ሜዳ ምንጠራ ውስጥ መግባት የለብንም፡፡ የሄድነውን መንገድ ዘወር ብለን ስናይ በራሳችን ላይ መሳቃችን አይቀሬ ነው፡፡ ታሪካችን የጠብ ነው፡፡ የመጣላት ነው፡፡ ቢያንስ ምርጫዎች ሲደጋገሙ ከጠቡ ቀነስ እያደረጉልን፣ እያሰለጠኑን መሄድ አለባቸው፡፡ “በጣም አንጣላ፤ ከታረቅን እንዳይቆጨን” የሚለው የትግሪኛ ተረት ይህን ይነግረናል፡፡

“የታሰሩት የሙስሊም መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት ይፈቱ” የሚል ተቃውሞ ትናንት ከቀትር በኋላ በተካሄደበት የታላቁ አንዋር መስጊድ አካባቢ በርካታ ፖሊሶች ተሰማርተው የዋሉ  ሲሆን፤ ለሰዓታት በዘለቀው ግርግርና ረብሻ የተኩስ ድምጽ የተሰማ ቢሆንም የደረሰው ጉዳት እስካሁን በዝርዝር አልታወቀም፡፡ ቁጥራቸው ያልታወቁ ሰዎች በፖሊስ ተይዘው ሲወሰዱ ታይቷል፡፡
ተቃውሞና ግርግር የተፈጠረው የጁምዓ ስግደት ከመጠናቀቁ በፊት እንደሆነ የተናገሩ የአይን እማኞች፤ ቆመጥ የያዙ ፖሊሶች ተሰማርተው እንደነበርና በርካቶች ድብደባ እንደደረሰባቸው ገልፀዋል፡፡
በተክለሃይማኖት አደባባይ እና ከፒያሳ ወደ መርካቶ የሚወስዱ መንገዶች ለእግረኞችና ለተሽከርካሪ ተዘግተው የነበረ ሲሆን፤ ከተወሰነ ጊዜ በኋላ ለእግረኞች መከፈቱን የተናገሩ የአካባቢው ሰዎች፤ ግርግሩ ግን ወዲያው አልቆመም ብለዋል፡፡
“የታሰሩት የሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት ይፈቱ” ከሚለው እንቅስቃሴ ጋር በተያያዘ “ድምፃችን ይሰማ” በተሰኘው ድረገፅ የተቃውሞ ጥሪ ሲተላለፍ እንደሰነበተ ምንጮች ገልፀዋል። አምናም በተመሳሳይ የረመዳን የጾም ወቅት፣ በሦስት የአዲስ አበባ መስጊዶች ሦስት ሰፋፊ ተቃውሞዎች መካሄዳቸው ይታወሳል፡፡