Administrator

Administrator

Saturday, 25 November 2023 20:04

በቡና ፍቅር የወደቀው ራስታ

ብሬዳ ኒል ከኪንግ ሻይሎህ ሳውንድ ሲስተም

ብሬዳ ኒል ይባላል፡፡ በትውልዱ እንግሊዛዊ ቢሆንም ቋሚ መኖርያው ግን በሆላንድ አምስተርዳም ነው፡፡  የሳውንድ ሲስተም ኦፕሬተር፤ የሬጌ ሙዚቃ ባለሙያና ዲጄ ሆኖ በመስራት ከ35 ዓመታት በላይ አስቆጥሯል፡፡ ከሬድ ላየንና ማጀስቲክ ቢ ጋር በመሆን የኪንግ ሻይሎህ ሳውንድ ሲስተምን King Shiloh Sound system መስርቷል፡፡ ሳውንድ ሲስተሙ በአውሮፓ፤ በሰሜን አሜሪካ፤ በደቡብ አሜሪካና በሌሎች የዓለም ክፍሎች በሚካሄዱ የሙዚቃ ዝግጅቶችና የሬጌ  ፌስቲቫሎች ቋሚ ተሳታፊነት ይታወቃል፡፡ብሬዳ ኒል ሰሞኑን ወደ ኢትዮጵያ  የመጣው ለሰባተኛ ጊዜ ነው፡፡ ከታዋቂ የሬጌ ሙዚቀኞች መካከል በተደጋጋሚ በመምጣት የልዩ ክብረወሰን ባለቤት ያደርገዋል፡፡ለሙዚቃ ስራና ለጉብኝት ከሰባት ጊዜ በላይ ወደ ኢትዮጵያ በመምጣቱ ነው፡፡    ራስተፈርያኖችና የሬጌ ሙዚቀኞች ወደ አፍሪካ ወደ ኢትዮጵያ ስለመምጣት በብዛት እንደሚዘፍኑ ይታወቃል፡፡ ግን ለብዙዎቹ አይሆንላቸውም፡፡ ታዋቂው የሬጌ  ድምፃዊ ሉችያኖ ወደ ኢትዮጵያ ከ5 ጊዜ በላይ በመምጣት ይታወቅ ነበር፡፡   
ብሬዳ ኒልና የኪንግ ሻይሎህ ሳውንድ ሲስተም ቡድን ዘንድሮ ወደ ኢትዮጵያ ሲመጡ ትልቅ ራእይ ሰንቀው ነው፡፡  ኢትዮጵያን በሳውንድ ሲስተም ዝግጅቶችና የሬጌ  ፌስቲቫሎች የቱሪዝም መስህብና መናሐርያ በምትሆንበት አቅጣጫ ላይ ለመስራት ነው፡፡ ከአገር ውስጥና ከዓለም አቀፍ የሬጌ ድምፃውያን፤ ባለሙያዎችና ባለድርሻ አካላት በመተባበር ተከታታይ የሙዚቃ ዝግጅቶችን በአዲስ አበባ እና በተለያዩ የኢትዮጵያ ከተሞች ተዟዙሮ ለማዘጋጀትም አቅደዋል፡፡
የኪንግ ሻይሎህ ሳውንድ ሲስተም ቡድን ከሆላንድ አምስተርዳም በመነሳት ከሳምንት  በፊት አዲስ አበባ ገብተዋል፡፡ በመጀመርያ 7ኛውን አዲስ ደብ ክለብ የሬጌ ሙዚቃ ዝግጅት ከታዋቂዎቹ የሬጌ ሙዚቀኞች ራስ ጃኒ ፤ ቴዲ ዳን፤ ከአፍሪካ ወንድምና ሌሎች ሙዚቀኞች ጋር በመሆን አካሂደዋል፡፡ በማግስቱ ደግሞ በ23ኛው ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ  ላይ  ሳውንድ ሲስተሙን በመትከል በሙዚቃ ጨዋታቸው አስደናቂ ትኩረት አግኝተዋል፡፡ የሳውንድ ሲስተም ቡድኑ በታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ላይ የተሳተፈው ለ3ኛ ጊዜ ነበር፡፡ ባለፈው ሳምንት 5ኛ ፖሊስ ጣቢያ አካባቢ በሚገኝ አደባባይ ላይ ግዙፉ ሳውንድ ሲስተም ተተክሎ በብሬዳ ኒልና ሌሎች አጋሮቹ የቀረበው ጨዋታ የጎዳና ላይ ሩጫው ተሳታፊዎችን በከፍተኛ ደረጃ አዝናንቷል፡፡ የታላቁ ሩጫ ተሳትፎ የሳውንድ ሲስተሙን የጎላ ሚና  ያረጋገጠ ሲሆን ኪንግ ሻይሎህ ሳውንድ ሲስተምን ከኢትዮጵያ ህዝብ ጋር ማስተዋወቅ የተቻለበት ነው፡፡  በተለይ ብሬዳ ኒል የኢትዮጵያ ቡና የስፖርት ክለብ ማልያ ለብሶ  ሙዚቃዎቹን ማጫወቱ በርካቶችን ያስደሰተ ነበር፡፡ በጎዳና ላይ ሩጫው የተሳተፉ የቡና ደጋፊዎች፤ የእግር ኳስ አድናቂዎች፤ የሬጌ አፍቃሪዎች በሳውንድ ሲስተሙ ዙርያ በነበረው ማራኪ ድባብ እጅግ ተደስተዋል፡፡ከታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ስለነበራቸው  ለስፖርት አድማስ አስተያየት ሲሰጥ ‹‹ በሳውንድ ሲስተም ቡድናችን እኔን ጨምሮ ሁለትና ሶስት አባላት በአትሌቲክስ ውስጥ ያለፉ ናቸው፡፡ በታዳጊነት እድሜዬ  እግር ኳስና ውሃ ዋና ባዘወትርም ፕሮፌሽናል  አትሌት ለመሆን ነበር የሞከርኩት ፡፡ በረጅም ርቀት አትሌቲክስ  ወጣትነቴን ካሳለፍኩ በኋላ ነው ስፖርቱን በመተው ወደ ሙዚቃ የገባሁት፡፡ አትሌት ሆኜ  በማሳለፌ እጅግ ደስተኛ ነኝ፡፡ ፅናትን ተምሬበታለሁ፡፡ ዛሬ በሳውንድ ሲስተም ባለሙያነት ለምሰራቸው ተግባራት ሙሉ የአካል ብቃት ያዳበረኩበት ነው፡፡  አንዳንድ ግዜ በምናዘጋጀው የሳውንድ ሲስተም ሙዚቃ 6፤ 8  እና  10 ሰዓታትን ተወጥረን የምንሰራበት ሁኔታ አለ፡፡ በአጠቃላይ ሳውንድሲስተምን እንደ ማራቶን ውድድር መመልከት ይቻላል፡፡ አትሌቲክስ የአዕምሮና የአካልን ዲስፒሊን የሚጠይቅ ነው፡፡ ሳውንድ ሲስተምም እንደዚያው ነው፡፡ የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ላይ በነበረን ተሳትፎ በአትሌቲክስ እና በሳውንድ ሲስተም መካከል ያለውን መተሳሰርና መመሳሰል ያስተዋልኩበት ነው፡፡›› በማለት ተናግሯል፡፡ በ23ኛው ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ላይ የኪንግ ሻይሎህ ሳውንድ ሲስተም መስራት ከፍተኛ ድምቀት መፍጠሩን በስፍራው ተገኝተን ለመታዘብ ችለናል፡፡ ከሳውንድ ሲስተሙ ጋር የነበሩ ባለሙያዎች የጎዳና ላይ ሩጫውን ተሳታፊዎች በሬጌ ሙዚቃ ከማነቃቃታቸውም በላይ ከሩጫው ባሻገር በዳንስ የሚፈለገውን እንቅስቃሴ እንዲሰሩ በማድረግ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ነበረው፡፡
ከታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ በኋላ ብሬዳ ኒልና የኪንግ ሻይሎህ ሳውንድ ሲስተም አባላት ለመገናኘት የበቁት ከኢትዮጵያ ቡና ስፖርት ክለብ ጋር ነው፡፡ በሳምንቱ አጋማሽ ላይ  በአበበ ቢቂላ ስታድዬም የተካሄደው የአዲስ አበባ ሲ ካፕ የዋንጫ ጨዋታ ምክንያት ሆኗል፡፡ ብሬዳ ኒል በታላቁ  ሩጫ ላይ የቡናን ማልያ ለብሶ ሙዚቃ ማጫወቱ ብዙዎቹ የክለቡ ደጋፊዎች በማህበራዊ ሚዲያው በተለይ በቲክ ቶክ በአድናቆት ተከታትለውታል፡፡ ስለዚህም ከሲቲ ካፑ የፍፃሜ ጨዋታ በፊት ማለዳ ላይ ከቀንደኛ የቡና ደጋፊዎች ጋር የኪንግ ሻይሎህ ሳውንድ ሲስተም ቡድን አባላት ተገናኝተዋል፡፡ ብሬዳ ኒልን ያረፈበት ሆቴል ድረስ መጥተው አድናቆት የገለፁለትና በክለቡ ደጋፊነት እንዲመዘገብ የጠየቁት አንጋፋው የክለቡ ደጋፊ አዳነ ሽጉጤ እና  ከወቅቱ የክለቡ ደጋፊዎች አስተባባሪ ሆነው  አብርሐም ናቸው፡፡
ብሬዳ ኒል  በወጣትነት ዘመኑ በአትሌቲክስ ፕሮፌሽናል ደረጃ ላይ ደርሷል፡፡ በክለብ ደረጃ ለረጅም ጊዜያት የተወዳደረ ሲሆን እንግሊዝን በኦሎምፒክና በዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮን የመወከል ፍላጎት የነበረው ቢሆንም ሩጫውን ብዙም አልገፋበትም፡፡ ከአትሌቲክሱ ባሻገር ለእግር ኳስም ልዩ ፍቅር ነበረው፡፡ በተለይ በታዋቂው የእንግሊዝ ክለብ ሊድ ዩናይትድ ደጋፊነቱ ይታወቅ ነበር፡፡ የሳውንድ ሲስተም ባለሙያ ሆኖ ለመስራት ወደ ሆላንድ አምስተርዳም ገብቶ ከከተመ በኋላ ደግሞ ለአያክስ ክለብ ድጋፉን በመስጠት እግር ኳስን ሲከታተል ቆይቷል፡፡‹‹ ከስፖርት ጋር የተዋወቅኩት ገና በታዳጊነቴ ነው፡፡ ያደግኩት ከእግር ኳስ ጋር ነው፡፡ አባቴ ስፖርት በጣም ይወዳል፡፡ ስለዚህም በሳምንቱ መጨረሻ ላይ ወደ ስታድየም ተያይዘን እንሄዳለን፡፡ የምደግፈው ክለብ ሊድ ዩናይትድን ነው፡፡ በተጨማሪም የበርንሌይና የሌችስተር ሲቲ ክለቦች የሚያደርጓቸውን  ጨዋታዎች በየስታድየማቸው እየተገኘን እንመለከታለን፡፡ እድገቴ በሙሉ ከስታድዬም ጋር የተገናኘ ነው፡፡ የስፖርቱ ባህልና ስሜቱ ዛሬም ውስጤ    አለ፡፡›› ሲል ይናገራል፡፡
ከሰባት ዓመት በፊት ለመጀመርያ ጊዜ ወደ ኢትዮጵያ ሲመጣ፤ በሬጌ ሙዚቃ ውስጥ የተስፋፋውን የሳውንድ ሲስተም ባህል ለማስተዋወቅ ነበር፡፡ ከዚህ ስራው ባሻገር ለስፖርቱ ባለው ፍቅር ስለ አገሪቱ የእግር ኳስ ክለቦች መጠየቅ ነበረበት፡፡ አብረውት ከሚሰሩ ባለሙያዎች መካከል ሽሜ የሚባለው በተለይ ስለ ኢትዮጵያ ቡና ክለብ አብራራለት፡፡ የህዝብ ክለብ መሆኑና ደጋፊዎቹ በዝማሬያቸው፤ በቀለማቸውና በስታድዬም ውስጥ በሚፈጥሩት ድምቀት የሚስተካከላቸው አለመኖሩን  በደንብ ገለፀለት፡፡ ብሬዳ ኒል ስለ ቡና ክለብ የመጀመርያውን ማብራርያ ከሰማ በኋላ ስታድዬም ገብቶ የክለቡን ጨዋታ መመልከት የፈለገው፡፡ ከኢትዮጵያዊው ሽሜ  የቡናን ጨዋታ ስታድዬም ገብተው ለመመልከት በቁ፡፡ ከዚያ በኋላ ብሬዳ ኒል ከኪንግ ሻይሎህ የኢትዮጵያ ቡና ስፖርት ክለብ ደጋፊ ሆኖ ቀረ፡፡ወደ ኢትዮጵያ ቡና የስፖርት ክለብ ስለተሳበበት አጋጣሚ ሲገልፅ  ‹‹እግር ኳስ ያደግኩበት ስፖርት ብቻ አይደለም ፤ በተለያየ የዓለም ክፍል እየተዘዋወርኩ ባህሉን የተማርኩት ነው፡፡  ወደ አዲስ አበባ ስመጣ የአፍሪካን እግር ኳስ  የማወቅና የመረዳተ ፍላጎት ነበረኝ፡፡ ከመላው ዓለም ጋር ለማነፃፀር ነው፡፡ ሽሜ የተባለው ወዳጄ ይህን ፍላጎት ተረድቶ እሽ እንሂድ አለኝ፡፡ የተ ስለው እኔ የምደግፈው ቡድን ቡና ነው በማለት እንባ እየተናነቀው ስለክለቡ ብዙ ነገረኝ፡፡  የቡና ደጋፊዎች መደበኛ የከተማ ነዋሪዎች መሆናቸውን፤ ደሃው የህብረተሰብ ክፍል ለክለቡ ቅርብ መሆኑን፤ ጠንካራ ሰራተኞችና በላባቸው ለፍተው የሚያድሩ ህዝቦች ክለብ መሆኑን በተለያየ መንገድ አስረዳኝ፡፡ በመጨረሻም ስታድየም ገብተን የቡናን ጨዋታ እንድንመለከት ሃሳብ አቀረብኩለት፡፡ ተያይዘን ወደ ስታድዬም ጉዞ ቀጠልን መንገድ ላይ የቡና ደጋፊዎች የክለባቸውን ማልያ ለብሰው በህብረ ዝማሬ ታጅበው ወደ ስታድዬም ሲጓዙ ተመለከትኩ፡፡ ስታድዬም ስገባ የደጋፊዎቹ ማራኪ ዝማሬዎችና እንቅስቃሴዎችን በአይኔ በብረቱ ስመለከት በቡና ክለብ በእጅጉ ተማረኩኝ፡፡ ደጋፊዎቹ ክለባቸውን የሚያበረታቱበት የጠለቀ ስሜት የሚገርም ነው፡፡ እግር ኳስ የህይወት ነፀብራቅ መሆኑን የምትመለከትበት ድንቅ ክለብ ነው፡፡›› በማለት  ለስፖርት አድማስ  አብራርቷል፡፡
ብሬዳ ኒል ለኢትዮጵያ ቡና ስፖርት ክለብ ያለው ፍቅር እየጨመረ የሄደው የክለቡን ማሊያዎች በቡኒና ቢጫ ቀለማት ከገዛ በኋላ ነበር፡፡ በአውሮፓ፤ በሰሜን አሜሪካ፤ በኤሽያና በአፍሪካ በሚሰራቸው ትልልቅ ኮንሰርቶች ላይ ለብሶት ታይቷል፡፡ የሳውንድ ሲስተም ጨዋታውን ሲያቀርብ ከሚለይባቸው አለባበሶች  xንዱ ሆኖለታል፡፡ ባለፉት አምስት ዓመታት በዓለም ዙርያ ባቀረባቸው ኮንሰርቶች የቡናን ማልያ በመልበስ በከፍተኛ ደረጃ ክለቡን ሊያስተዋውቀው በቅቷል፡፡ በተለይ ከ2019 እኤአ ወዲህ በመላው ዓለም በሰራቸው ኮንሰርቶች ነው፡፡ በቡና ማሊያ ዝግጅቶቹን ማቅረቡን የተመለከቱ የሳውንድ ሲስተም ቡድኑ አባላት ማልያውን በመልበስ ስሜቱን መጋራታቸው ክለቡን በመደገፍ እንዲቀጥል መነቃቃት ስለፈጠሩለት እጅግ አስደስቶታል፡፡ በፈረንሳይ ፓሪስ በሚካሄደውና በቀን ውስጥ ከ45ሺ በላይ ተሳታፊ በሚያገኘው ደብ ካምፕ  የሳውንድ ሲስተም ፌስቲቫል ላይ የቡናን ማልያ ለብሶ ነበር፡፡ በሳምንት ውስጥ ከ250ሺ በላይ ጎብኝዎችና ታዳሚዎችን በሚያሳትፈው የስፔኑ ሮተተቶም ሰንስፕላሽ የሬጌ ፌስቲቫል ላይም የቡና ማሊያውን ለብሶ ለመጫወት በቅቷል፡፡ ዘንድሮ ወደ ኢትዮጵያ ከመምጣቱ በሰሜን አሜሪካ በነበረው ቆይታም ጋር በተያያዘ የቡናን ማሊያ ታጥቆ ነበር፡፡ በሜክሲኮ ከተማ በሚካሄድ የሬጌ ፌስቲቫል ላይ የሰራው የሚወደውን ክለብ ቡኒ ማልያ በመልበስ ሲሆን ከወር በፊት ሎስአንጀለስ ውስጥ በግዙፍ ክለብ ባቀረበው ዝግጅትም የሰራው በተመሳሳይ አለባበስ ነበር፡፡ በሎስ አንጀለስ ዝግጅት ላይ ሁለት ኢትዮጲያውያን ታዳሚ እንደነበሩ ለስፖርት አድማስ ያስታወሰው ብሬዳ ኒል የቡና ክለብ ደጋፊዎች እንደሆኑና የክለባቸውን ማልያ ለብሶ መጫወቱ እንዳኮራቸው ገልፀውልኛል ብሏል፡፡
ብሬዳ ኒል በሳምንቱ አጋማሽ ላይ በአበበ ቢቂላ ስታድዬም የተካሄደውን የቡና እና የሃድያ ሆሳዕና የሲቲ ካፕ ጨዋታ ከመመልከቱ በፊት  ከአንጋፋው የቡና ክለብ ደጋፊ አዳነ ሽጉጤ እና ከደጋፊዎች አስተባባሪው አብርሃም ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ውይይት አድርገዋል፡፡ የቡና ደጋፊዎች አውሮፓዊው ክለባቸውን በዓለም ዙርያ ስላስተዋወቀላቸው አመስግነውታል፡፡ እሱም ለክለቡ ያለው ፍቅር የገለፀላቸው ሲሆን ወደ ኢትዮጵያ በመጣ ቁጥር የሚያስደስተው የቡናን ጨዋታ ስታድዬም ገብቶ መመልከት መሆኑንም ነግሯቸዋል፡፡ ከዚህ ቆይታው በኋላ ብሬዳ ኒል አራት ኪሎ አምባሳደር የሚገኘውን የክለቡን የስፖርት ትጥቆች መሸጫ መደብር ጎብኝቶም ነበር፡፡ በስፖርት ትጥቅ መሸጫው መደብር የክለቡን የተለያዩ የስፖርት ትጥቆችና ምርቶች በመጎብኘት ከመደሰቱም በላይ ከሳውንድ ሲስተም አጋር ባለሙያዎች ጋር በርካታ የማስታወሻ ማልያዎች፤ የስፖርት ትጥቆችና ቁሶችን ለመሸመት በቅተዋል፡፡
 ብሬዳ ኒል፤ ማጀስቲክ ቢ እና  አይታል ዩዝ ከኪንግ ሻይሎህ ሳውንድ ሲስተም ዛሬ ቅዳሜ ላይ የመጀመርያውን አርባምንጭ ሬጌ ፌስቲቫል ያቀርባሉ፡፡ ከአዲስ አበባ ከተማ ወጣ ብሎ  በተዘጋጀ ፌስቲቫል ላይ ዲጄ ሀርቲካል ከኬንያ፤ ራስ ጃኒ፤ ቴዲ ዳንና ራስ ኪውንተሰብ ከኢትዮጵያ ተሳታፊ ይሆናሉ፡፡
የኪንግ ሻይሎህ ሳውንድ ሲስተም አባላት ወደ አውሮፓ ሲመለሱ የኢትዮጵያ ቡና ክለብ ኦፊሴላዊ ደጋፊ የሚሆኑበትን እቅድ ይዘው ነው፡፡ የሳውንድ ሲስተሙን ሌሎች አባላት ወደ ክለቡ ድጋፍ ለማምጣት ቃል ገብተዋል፡፡ በቀጣይ በመላው ዓለም በሚያቀርቧቸው የሙዚቃ ዝግጅቶች የክለባቸውን ማልያዎችን እየለበሱ ማስተዋወቅ እንደሚቀጥሉም ተናግረዋል፡፡ ብሬዳ ኒል ለስፖርት አድማስ እንደገለፀው ወደፊት ከቡና ክለብ አስተዳደር እና ከደጋፊዎች ጋር በመተባበር የሳውንድ ሲስተም ዝግጅቱን ክለቡን በሚጠቅም ፕሮጀክት ለማቅረብ ይፈልጋል፡፡ በተለይ  ኢትዮጵያ ውስጥ በሚገኝ ስታድዬም የሳውንድ ሲስተም  ጨዋታውን ለማቅረብ ከፍተኛ ፍላጎት እንዳለው የገለፀ ሲሆን የቡና ክለብ ስታድዬም ለመገንባት በሚያደርጋቸወ እንቅቃሴዎች የበኩሉን ድጋፍ ለመስጠት፤ ክለቡን ለማጠናከር በሚዘጋጀው የጎዳና ላይ ሩጫ ልዩ ተሳትፎ ማድረግ እንደሚፈልግም ተናግሯል፡፡

በቅርቡ አፍሮ ባሮሜትር በተባለው ታዋቂ  የምርምር ተቋም ይፋ የተደረገውን የሕገ- መንግስቱ ማሻሻያ አስፈላጊነት፤ “ጊዜውን ያልጠበቀና ግልፅነት የጎደለው ነው” ሲሉ የፌደሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባዔ አገኘሁ ተሻገር አጣጣሉት።
ተቋሙ የጥናቱ ውጤቱን ባለፈው ህዳር 6 ቀን 2016 ዓ.ም በኢንተር ሌግዥሪ ሆቴል ይፋ ማድረጉ ይታወሳል።
ሕገ መንግስቱ የፖለቲካና የሕግ ሰነድ መሆኑን መረዳት ያስፈልጋል ያሉት አፈ ጉባዔ አገኘሁ ተሻገር፤ ከነባራዊው ሁኔታ አንፃር ጥናቱ በችኮላ መሰራት የነበረበት አይደለም ብለዋል።
አፍሮ ባሮሜትር  የተሰኘው ይኸው የምርምር ተቋም፤ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የስልጣን ጊዜ ገደብ ይጣልበት በሚለው ዙሪያና  የሕገመንግስት ማሻሻያ ያስፈልጋል የሚል መደምደሚያ ያለው የጥናት ውጤት ይፋ ማድረጉ አይዘነጋም።“ጥናቱ የሁሉንም ብሔሮችና የህብረተሰብ ክፍሎች ያላካተተ በመሆኑ በርከት ያሉ ጉድለቶች የተመለከትንበት የጥናት ሰነድ ነው” ሲሉ አፈ  ጉባኤ  አገኘሁ ተሻገር አጣጥለውታል። አፈጉባኤ አገኘሁ እንደሚሉት ከሆነ፤ የጥናቱ ናሙናዎች ናቸው ተብለው የተወሰዱ መረጃዎች ግልፅነትና  የውክልና ተአማኒነት የሚጎድላቸው ናቸው በማለት የጥናት ግኝቱን ተችተውታል።
ህገ-መንግስቱ በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ብሔር ብሔረሰቦች ቃልኪዳን ሰነድ እንደመሆኑ መጠን፣ ህዝቦች በህገ-መንግስቱ ዙርያ ካላቸው ልዩ ፍላጎት አንፃር የጥናት ውጤቱ “በመሬት ላይ ካለው ሀቅ ጋር የሚጋጭ ነው” ብለዋል አፈጉባዔው።በአፍሮ ባሮሜትር ጥናት መሠረት፣ የአገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር የሥልጣን ዘመን መገደብ አለበት የሚሉ ኢትዮጵያውያን 66 በመቶ ሲሆኑ፣ አዲስ አበባ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አባል እንድትሆን የሚፈልጉ ኢትዮጵያውያን ደግሞ 53 በመቶ መሆናቸው ተጠቁሟል፡፡
ጥናቱ፤ በሁሉም ክልሎችና በሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች፣ ዕድሜያቸው 18 እና ከዚያ በላይ የሆኑ 2400 ኢትዮጵያውያንን ቃለመጠይቅ በማድረግ የተከናወነ መሆኑ ተገልጿል፡፡
አፍሮ ባሮ ሜትር የተሰኘው ተቋም ያቀረበው የጥናት ውጤት እንደሚያመለክተው፤ በጥናቱ ውስጥ ከተካተቱት አብዛኞቹ ኢትዮጵያውያን አሁን በስራ ላይ ያለው የኢትዮጵያ ህገ- መንግስት “መሻሻል አለበት”  ብለዋል።
“ጥናቱ አካታችነት የጎደለው ነው። አፈጉባኤ አገኘሁ በበኩላቸው ጥቂት ልሒቃን አነጋግሮ እንዲህ አይነት ሰነድ ማቅረብ የህገ-መንግስቱን መሠረት በውል ካለመረዳት የሚመነጭ ነው” ሲሉ ተችተዋል።

25ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን እያከበረ ነው
ለ10 የበጎ አድራጎት ድርጅቶች 15 ሚሊዮን ብር ለግሷል


ህብረት ባንክ ጠቅላላ የሀብት መጠኑ 84 ቢሊዩን ብር መድረሱን አስታወቀ፡፡ ባንኩ ይህን የገለፀው የተመሰረተበትን 25ኛ ዓመት የብር ኢዩቤልዩ በዓል እያከበረ ባለበት ወቅት ነው፡፡
ባንኩ ከትላንት በስቲያ ምሽት በሸራተን አዲስ ሆቴል 25ኛ ዓመት ክብረ በዓሉን፣ የባንኩ ከፍተኛ አመራሮች፣ ሰራተኞች፣ የሌሎች ባንኮች ተወካዮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በይፋ ማክበር የጀመረ ሲሆን፤ ለ10 የበጎ አድራጎት ድርጅቶች 15 ሚ.ብር መለገሱም ታውቋል። ባንኩን በትጋት ላገለገሉ ሰራተኞችም እውቅናና ሽልማት ሰጥቷል፡፡
የባንኩ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ መላኩ ከበደ፤ የባንኩን የ25 ዓመት ጉዞና እድገት አስመልክተው በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳብራሩት ባንኩ በፆታ በእድሜ በመልክ “አምድርና በማንኛውም ሁኔታ ሳይገደብ ሁሉን አሳታፊና አቃፊ እንዲሆን ተደርጎ በ1991 ዓ.ም መመስረቱን ያስታውሳሉ። “በህብረት ሰርተን በህብረት እንደግ” በሚል መሪ ቃሉ ብዙዎችን አቅፎ እየሰራና በየዓመቱ ትልልቅ ለውጦችን እያስመዘገበ የግል ከአገሪቱ ግንባር ቀደም ባንኮች አንዱ መሆን እንደቻለም ዋና ስራ አስፈፃሚው ተናግረዋል፡፡ “ባንካችን በተቀማጭ በብድርና በትርፍ ደረጃ ከ25-30 በመቶ እያደገ የመጣ ሲሆን በቴክኖሎጂም ቢሆን ከ15 እና ከ16 ዓመታት በፊት ኢንተርኔትና ሞባይል ባንኪንግ በማይታወቅበት ዘመን ቀድሞ የጀመረ ስመጥር ባንክ ነው” ሲሉም አብራርተዋል-ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ መላኩ ከበደ፡፡
የኮር ባንኪንግ ሲስተም የሚሰራው በውጪ አገር ዜጎች ነው ያሉት ሃላፊው፤ ይሁን እንጂ ህብረት ባንክ ግን የውስጥ አቅሙን በማዳበር፣ በውጪ ዜጎች ላይ ያለውን አመለካከት ሰብሮ በራሱ ሰራተኞች ማሰራቱንና በዚህም 1ሚ ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማዳኑን ተናግረዋል፡፡
አዲስ የሞባይል መተግበሪያም እንደዚሁ በባንኩ የውስጥ አቅም መሰራቱ የተጠቆመ ሲሆን ከአፍሪካም ከኢትዮጵያም ባንኮች የህብረት ባንክን ተሞክሮ እየወሰዱ መሆኑንና ሶስት የኢትዮጵያ ባንኮችም የህብረት ባንክን ፕላትፎርም ለመጠቀም ስምምነት መፈራረማቸውን አቶ መላኩ ተናግረዋል፡፡ባንኩ በ25 ዓመት ጉዞው ካሳካቸው አንዱና ዋነኛው ዋና መስሪያ ቤቱን ለገሀር አይን በሆነ ቦታ ላይ መገንባቱ መሆኑን የገለፁት ዋና ስራ አስፈፃሚው እ.ኤ.አ በ2015 ዓ.ም የመሰረት ድንጋይ ተጥሎ በ2021 ዓ.ም መመረቁንና ግንባታውም 6 ዓመታት መፍጀቱን ተናግረዋል። የባንኩ ህንፃ ባለ 32 ወለል ሲሆን አራት ቤዝመንቶች ያሉት እጅግ ዘመናዊ ህንፃ ነውም ተብሏል። ባንኩ ለ20 ዓመት ያገለገለውን ሎጎ በመቀየር ትርጉም ያለውና ለባንኩ ስያሜ የሚመጥን አዲስ ሎጎ ማሰራቱን አስታወሰው አዲሱ ሎጎ የሁለት እጅ ትስስር የገበሬውን የገመድ ጉንጉንና የሐበሻ ልብስ ጥለትን ያጣመረ ዘርፈ ብዙ ትርጉም ያለውም ነው ተብሏል፡፡
ባንኩ የ25ኛ ዓመት የምስረታ በዓን ለቀጣዩ አንድ ዓመት በፎቶ ኤግዚቢሽን፣ በበጎ አድራጎት ትጉህ ሰራተኞች በመሸለምና በተለያዩ ተግባራት እስከ ሰኔ ድረስ ማክበሩን እንደሚቀጥል አስታውቋል።
ባንኩ በአሁኑ ወቅት አጠቃላይ ሀብቱ 84 ቢሊዩን የደረሰ ሲሆን የቅርንጫፎቹ ብዛትም ከ475 በላይ መድረሳቸውንና ከ8ሺህ በላይ ሰራተኞ ማፍራቱን የባንኩ ከፍተኛ አመራሮች ገልፀዋል፡፡

ኢትዮጵያ በማዕድን ሃብት የታደለች ድንቅ ሀገር ናት። ይህንን ሃብት አልምተን ለመጪው ትውልድ የተሻለች ሀገር ማስረከብ አለብን። ዛሬ የተከፈተው የማዕድንና ቴክኖሎጂ ኤክስፖም የኢትዮጵያን የማዕድን አቅም በማሳየት በዘርፉ ያለውን ኢንቨስትመንት ያነቃቃል።

•  ስፖርቱ መስፋፋቱ በሥነ ምግባር የታነፁ ዜጎችን ለማፍራት
ጉልህ አስተዋፅኦ ያበረክታል ተብሏል


የኢትዮጵያ ሌጀንድ ኢንተርናሽና ፕሮ ቴኳንዶ ፌደሬሽን፣ የቴኳንዶና የማርሻል አርት ስፖርትን በት/ቤቶችና በመዝናኛ ቦታዎች ለማስፋፋትና ለማጠናከር የሚያስችለውን የስምምነት ሰነድ ከአሴቅ ዲኮርና ኢቨንት ኦርጋናይዜሽን ጋር ትላንት ተፈራረመ፡፡

የስምምነቱ ዋና ዓላማ፤ የቴኳንዶና የማርሻል አርት ስፖርትን በት/ቤቶች፣ በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት፣ በመዝናኛ ቦታዎችና በሌሎችም መንግስታዊና መንግስታዊ ባልሆነ ተቋማት ማስፋፋትና ማጠናከር ነው ተብሏል፡፡

የቴኳንዶና የማርሻል አርት ስፖርቱን የማስፋፋት ፕሮጀክቱ፤ በተለይም ት/ቤቶችና ታዳጊዎች ላይ የሚያተኩር ሲሆን፤  ጤናቸው የተጠበቀ፣ በአካልና በአዕምሮ የዳበሩ እንዲሁም  በመልካም ሥነምግባር የታነፁ ብቁና አሸናፊ ዜጎችን በማፍራት ረገድ ጉልህ አስተዋፅኦ ይኖረዋል ተብሏል፡፡

በተጨማሪም፤ የሌጀንድ ኢንተርናሽና ፕሮ ቴኳንዶ ስፖርት ውድድርን በየደረጃው በስፋት፣ በጥራትና በስርዓት በማዘጋጀት በከተማ አቀፍ፣ አገር አቀፍና ዓለማቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሚሆኑ ምርጥ ስፖርተኞችን በማፍራት የአገርን ክብርና ዝና ከፍ ለማድረግ ታልሟል፡፡

በስምምነት ሰነዱ ላይ እንደተመለከተው፤ በከተማ ውስጥ የሚታየውን የማርሻል አርት ስፖርት ማሰልጠኛ ሥፍራ እጥረት ለመቅረፍ ከት/ቤቶች ጋር በትብብር የሚሰራ ሲሆን፤ የተለያዩ የሌጀንድ የማርሻል አርት ስፖርት ሌሎች ውድድሮችንና መዝናኛ ፕሮግራሞችን በተቀናጀ መልኩ በማዘጋጀት  ስፖርቱን ተደራሽ ለማድረግና ለህብረተሰቡ በስፋት ለማስተዋወቅ ታቅዷል፡፡

ሌጀንድ ኢንተርናሽና ፕሮ ቴኳንዶ ፌደሬሽን፣ ከ24 ዓመተ በፊት በዓለማቀፍ ደረጃ ተቋቁሞ ሥራ መጀመሩን  በፊርማ ስነስርዓቱ ላይ የጠቆሙት ማስተር ሄኖክ፤ በኢትዮጵያ ደግሞ ላለፉት 4 ዓመታት ፈቃድ ተሰጥቶት ተደራሽነቱን ለማስፋትና ትርጉም ያለው አስተዋጽኦ ለማበርከት  እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡

በሌጀንድ ፎር ኦል እና በአሴቅ ዲኮርና ኤቨንት ኦርጋናይዜሽን የተደረሰው ስምምነት፣ በዋናነት ተግባራዊ የሚደረገው በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥር በሚገኙ ት/ቤቶች ውስጥ ነው ተብሏል፡፡

Sunday, 19 November 2023 00:00

ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ

•  ማህበሩ 70 ቢሊዮን ብር ለብድር ማቅረቡ ተነግሯል

የኢትዮጵያ አነስተኛ ብድርና ቁጠባ ተቋማት ማህበር የተመሰረተበትን የ25ኛ ዓመት የኢዮቤልዩ ክብረ በዓል በመጪው ሳምንት በተለያዩ ዝግጅቶች እንደሚያከብር ተገለፀ፡፡

በዝግጅቱ ላይ በአገሪቱ በልማቱ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረከተውና የ25 ዓመታት እድሜ ያስቆጠረው የማይክሮፋይናንስ ዘርፍ ኅዳር 18ን “የኢትዮጵያ የብድርና ቁጠባ ቀን” በማለት እንደሚሰይም ተነግሯል፡፡  

በማህበሩ የ25ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ላይ በዘርፉ የተሰማሩ የአገር ውስጥና የውጭ ተቋማት እንዲሁም መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችና የልማት አጋሮች እንደሚሳተፉ የጠቆመው የማህበሩ መግለጫ፤ ክብረ በዓሉ በፓናል ውይይትና ኤግዚቢሽን እንዲሁም ጥናቶች በሚቀርቡበት ኮንፍረንስና ሌሎች ኹነቶች እንደሚከበር አመልክቷል፡፡

ክብረ በዓሉ በመጪው ሳምንት ከህዳር 18-21 ቀን 2016 ዓ.ም፣ ለአራት ተከታታይ ቀናት፣ በሃይሌ ግራንድ ሆቴል ይከበራል፡፡

የ25ኛ ዓመት በዓል አከባበሩን  በተመለከተ በዛሬው ዕለት ረፋዱ ላይ ዳሙ ሆቴል አጠገብ ወደ ፒኮክ መናፈሻ መግቢያ ላይ በሚገኘው የማህበሩ አዳራሽ ፣ የማህበሩ የቦርድና የማኔጅመንት ከፍተኛ አመራሮች ለሚዲያ ባለሙያዎች  መግለጫ ሰጥተዋል፡፡

በዓሉ “ማይክሮፋይናንስ በዲጂታል ዘመን፣ የፋይናንስ አካታችነት ለስራ ፈጠራና ለሴቶች ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት” በሚል መሪ ቃል የሚከበር መሆኑን ያመለከተው  ማህበሩ፤ ባለፉት ዓመታት በዋናነት የዲጂታል ስርዓት በማስፋፋትና በፋይናንስ አካታችነት ረገድ ጉልህ ስኬት መቀዳጀቱን ጠቁሟል፡፡

የማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት የዲጂታል ሥርዓት ተጠቃሚ መሆናቸው በተጨባጭ ውጤታማ እንዳደረጋቸው የተገለጸ ሲሆን፤ በቴክኖሎጂው አማካኝነት  የተደራሽነት ሽፋናቸውን ቀድሞ ከነበረው 35 በመቶ ገደማ ወደ 50 በመቶና ከዚያም በላይ ማሳደጋቸው ተጠቁሟል፡፡  

ከ50 የማህበሩ አባላት መካከል በ30 የማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት የኮር ባንኪንግ ዲጂታል ሥርዓት መተግበሩን የገለጹት አመራሮቹ፤ በፋይናንስ አካታችነት ረገድም ከባንኮች ይልቅ ተቋማቱ የበለጠ ስኬት መቀዳጀታቸውን ጠቁመዋል፡፡

እስካሁን ድረስ ስድስት የሚሆኑ የማህበሩ አባላት ብሔራዊ ባንክ ያስቀመጠውን መስፈርት በማሟላት ወደ ባንክ ማደጋቸውንና በሂደት ላይ የሚገኙም እንዳሉ የጠቆሙት አመራሮቹ፤ ተቋማቱ ወደ ባንክ ሽግግር ቢያደርጉም የቀድሞ አገልግሎታቸውን የመስጠት ግዴታ እንዳለባቸው አመልክተዋል፡፡


ማህበሩ የሴቶች ተጠቃሚነትን በማረጋገጥ ረገድም ትርጉም ያለው ሥራ ማከናወኑን የተናገሩት አመራሮቹ፤ በመጀመሪያዎቹ ዓመታት ለሴቶች ሲቀርብ የነበረው ብድር አነስተኛ ቢሆንም፣ በሂደት እየተሻሻለ መጥቶ በአሁኑ ወቅት የብድሩ መጠን 50-50 (እኩል ለእኩል) ለመሆን መብቃቱን ጠቅሰዋል፡፡  ለሴቶች ተስማሚ የሆነ የብድር አገልግሎት ለመተግበር ጥረት መደረጉንና የሴቶች ተሳትፎም ከዓመት ወደ ዓመት እያደገ  መምጣቱን አክለው ገልፀዋል፡፡

በማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት የሚቆጥቡ ደንበኞች ከ20 ሚ. በላይ እንደሚደርሱ የተነገረ ሲሆን፤ ማህበሩ  ከ70 ቢሊዮን ብር በላይ ለብድር  ማቅረቡን  ለማወቅ ተችሏል፡፡

የኢትዮጵያ አነስተኛ ብድርና ቁጠባ ተቋማት ማህበር ባለፉት 25 ዓመታት ስኬት ብቻ አይደለም የተቀዳጀው፤ ቀላል የማይባሉ ተግዳሮቶች እንዳገጠመውም የማህበሩ አመራሮች በመግለጫቸው ላይ ተናግረዋል፡፡

ከተግዳሮቶቹም መካከል የፋይናንስ እጥረት በቀዳሚነት ተጠቅሷል፡፡ የተጀመረውን ኮር ባንኪንግ ተግባራዊ ለማድረግ ማህበሩ ከፍተኛ የፋይናንስ ችግር ገጥሞት ነበር ያሉት አመራሮቹ፤ የውጭ ምንዛሬ በፈለግነው ጊዜና መጠን ባለማግኘታችንም ተቸግረን ነበር ብለዋል፡፡  ሆኖም ማህበሩ ችግሩን ከተቋማቱ  ጋር በጥምረት በመስራት ለመፍታት እንደተቻለ ተጠቁሟል፡፡

የመሰረተ ልማት ችግር ሌላው የገጠማቸው ተግዳሮት እንደነበር የጠቆሙት የማህበሩ አመራሮች፤ የኢንተርኔትና የኤሌክትሪክ ሃይል መቆራረጥ ሥራቸውን እያስተጓጎለባቸው ይቸገሩ እንደነበር ጠቁመው፣ ከፍተኛ አቅም ያለው ጄነሬተር በመጠቀም አገልግሎታቸውን ያለማቋረጥ ማቅረብ መቻላቸውን አስረድተዋል፡፡

ከሁሉም በላይ የማይክሮ ፋይናንስ ተቋማቱ ትልቅ ተግዳሮት የሚያበድሩት ካፒታል ማነስ  መሆኑን በይፋ የገለፁት የማህበሩ አመራሮች፤ በዚህ ረገድ መገናኛ ብዙኃን ስለማይክሮ ፋይናንስ ተቋማትና አገልግሎታቸው ለህብረተሰቡ በቂ መረጃ በመስጠትና ግንዛቤ በማስጨበጥ ትልቅ አስተዋጽኦ ሊያበረክቱ እንደሚችሉ ጠቁመው፣ እግረ መንገዳቸውን በመግለጫው ላይ ለተገኙት የመገናኛ ብዙሃን ጥሪ አቅርበዋል፡፡

Wednesday, 22 November 2023 21:26

addisadmassnews.com Issue1244

Wednesday, 22 November 2023 20:21

እነሆ ድልድዩን !

እነሆ ድልድዩን !
ይህንን መጽሐፍ አንብቤ እንዳጠናቀቅኩ በሃሳቤ " የሰው ልጅ ስልጣን ላይ ሆኖ ባበበበት ወቅት (በተወደደበት ጊዜ ) ያቺ ጊዜ ሳታልፍ ለተተኪው ትውልድ ስልጣኑን ቢያስረክብ በታሪክ ውስጥ ዘላለማዊ ይሆናል ። ታላቅነቱንም ምንጊዜም ትውልድ ይመሰክርለታል። እርሱም ካደለው ይህንን በህይወት ቆሞ ያያል ።" በማለት አብሰለሰልኩ ።
የመጽሐፉ ርእስ " ዘውድ ያልደፋው ንጉሥ " ደራሲው ደረጀ ተክሌ ወልደ ማሪያም ሲሆን በ452 ገጽ ተጠርዞ  በ500 ብር ገበያ ላይ ውሏል።
ባለታሪኩ ጸሐፌ ትእዛዝ ወልደ ጊዮርጊስ ወልደ ዮሐንስ ናቸው ። ከ1893 - 1968 ዓም እዚህ ምድር ላይ ያኖረዋል ።በአፄ ኃይለ ሥላሴ ዘመን ከፍተኛ ባለስልጣን ነበሩ ። እኝህ ድንቅ ሰው ምን እንደከወኑ ደረጄ ማለፊያ በሆነ ትረካ ያወጋናል እና መጽሐፉን ገዝቶም ሆነ ፈልጎ ማንበቡን ለእናንተ ልተው ። እኔ ስለጀግናው ቀደም ብሎ መረጃ ቢኖረኝም ደረጀ መረጃዬን ጥብስቅ ስላደሰገልኝ ላመሰግነው እወዳለሁ ። ጸሐፌ ትእዛዝ ወልደ ጊዮርጊስ ለጃንሆይ ምን ብለዋቸው ነው ከላይ በጥቅስ ያስቀመጥኩትን አባባል ያልኩት ? ጸሐፌ ትእዛዝ የጥንቱን ትውልድ ከአዲስ ትውልድ ያገናኙ ድልድይ ነኝ ይላሉ ። ... የእንግሊዝን መንግስት የኢትዮጵያ ሞግዚትነት አምክነው አገራችንን ነፃነቷን እንድትጎናጸፍ ካደረጉ አርቆ አሳቢዎች መካከል አውራውም ናቸው ። ...
መልሱን ከመጽሐፉ ታገኙታላችሁ ።
ሰላም በምድራችን ላይ ይስፈን !

ከትምህርት ባሻገር ሁለንተናዊ የሰብዕና መገንቢያና የተሻለ የትምህርትና የሥራ አካባቢ ለመፍጠር ባህል ማዕከሉን ማጠናከር እንደሚያስፈልግ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡

ማዕከሉ በየሳምንቱ ማክሰኞ የኪነ-ጥበብ ምሽት ዳግም ማዘጋጀት እንደሚጀምር የባህል ማዕከሉ ኃላፊ ተስፋዬ እሸቱ ገልጸዋል፡፡

ቅዳሜ፣ ማክሰኞና ሐሙስ ደግሞ ፊልም የሚያሳይ ሲሆን፤ በቀረቡት ፊልሞች ላይ በወር አንድ ጊዜ ውይይት ይደረጋል ብለዋል።

ባህል ማዕከሉ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ሰርከስ ማኅ