Administrator

Administrator

(የፕሮግራም ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር፤ አቶ ጥበቡ ታደሰ)

          ለአምስት ዓመት በጣቢያችሁ ሲተላለፍ የቆየው “ትንንሽ ፀሐዮች” የተሰኘ ተወዳጅ የሬዲዮ ድራማ እንዴት ድንገት ሊቋረጥ ቻለ? እንዳልሽው ድራማው በፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ለአምስት አመታት ያህል ተላልፏል፡፡ የተቋረጠው በሁለት ምክንያቶች ነው፡፡ አንደኛው እንደማንኛውም ድራማ የሆነ ጊዜ ላይ ተጀምሮ ማለቅ ስላለበት ነው፡፡ ሁለተኛውና ዋነኛው ምክንያት ደግሞ ድራማውን ከአድማጭ በሚመጣ አስተያየት እንገመግመዋለንና ከጊዜ ወደ ጊዜ “ይዘት አልባ” ሆነ የሚሉ አስተያየቶች ተበራከቱ። እንደ አጀማመሩ መልእክት የሚያስተላልፍና የሚያስተምር እየሆነ አይደለም የሚሉ አስተያየቶችን አሰባስበን፣ እንዲህ እየተባለ ስለሆነ በተቻለ መጠን አጠንክረው፣ አስተካክለው እያልን በተደጋጋሚ ጠይቀነዋል፤ እንዲያስተካክልም ለአንድ አመት ያህል ጊዜ ሰጥተነው ነበር፣ ያንን ጊዜ ተጠቅሞም አላስተካከለም፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ድራማው ላይ የነበሩት ዋና ዋና ገፀ ባህሪያት በተለያየ ምክንያት ከድራማው ወጡ፡፡

በዚህ በዚህ ምክንያት ድራማው በተወዳጅነቱ መቀጠል ባለመቻሉ ሊቋረጥ ችሏል፡፡ ተዋንያኑ የለቀቁበትን ምክንያት ሊነግሩኝ ይችላሉ-- ለምሳሌ “ቅቤው” የተባለው እና ተወዳጁ ገፀ-ባህሪ አሜሪካ በመሄዱ በድራማው መቀጠል አልቻለም፡፡ “አመዶ” የተሰኘውን አዝናኝ ገፀ-ባህሪ ወክሎ የሚጫወተው በረከት በላይነህም ድራማው ከጊዜ ወደ ጊዜ ይዘቱ እየወረደ በመሄዱ ለክብሬ አይመጥንም ብሎ በራሱ ጊዜ አቁሞታል፡፡ እነዚህ ከምክንያቶች ጥቂቶቹ ናቸው፡፡ ደራሲና አዘጋጁ፣ ከፈቃዴ ውጭ የታሪኩ ሂደት ሳይቋጭ በተፅዕኖ ነው ድራማው የተቋጨው ብሏል፡፡ ድራማውን በምን መልኩ አቋረጣችሁት? ድራማው ሲ ቋረጥ ዝ ም ብ ሎ አ ይደለም የተቋረጠው፡፡ እኛ በመጀመሪያ ድራማው በተገቢው መንገድ እንዲጠናቀቅ በደብዳቤም በቃልም ነግረነው ነበር፡፡ ለዚህ ፈቃደኛ አልሆነም፡፡ ስለዚህ የህዝቡ አስተያየት በድራማው ላይ ጥሩ አይደለም፣ ይዘቱ ወርዷል፣ ዋና ዋና ተዋንያኑ በተለያየ ምክንያት ለቀዋል፡፡ በእነዚህ ምክንያቶች አድማጭ ስላጣ፣ እሱም ለመቋጨት የተሰጠውን ጊዜ ስላልተጠቀመ ጣቢያው ድራማው እንዲቋረጥ አድርጓል፡፡

ደራሲው ዮናስ “ታሪኩ ይዘቱ አልቀነሰም፣ የጣቢያውየተወሰኑ ኃላፊዎች ለእኔ ካላቸው ጥሩ ያልሆነ አመለካከት ሆን ተብሎ ነው እንዲቋረጥ የተደረገው”ብሏል፡፡ እርስዎ በዚህ ላይ ምን ይላሉ? ዝም ብለሽ አንቺ እንኳን ስታስቢው፣ አምስት አመት በስምምነት አብረን ሰርተናል፡፡ ጥላቻና አለመግባባት በመካከላችን ቢኖር፣ ለአምስት አመት ቀርቶ ለአምስት ቀን እንኳን አብሮ መስራት አይቻልም፡፡ በተለይ ለአራት አመታት ድራማው ጥሩ አድማጭና ተቀባይነት ኖሮት ተስማምተን ቆይተናል፡፡ አሁን ድራማው አድማጭ አጣ፣ ይዘቱ ቀነሰ ሲባል “የግል ጥላቻ ነው፣ እኔን አለመፈለግ ነው” የሚለው ሰበብ፣ ለእኔ ውሀ የሚያነሳ አይደለም፡፡ የግል ጥላቻ ቢኖር “ተደማጭነቱ ቀነሰ፣ እንዲስተካከል አድርግ” ብለን ከአንድ አመት በላይ ጊዜ እንሰጠው ነበር? በተደጋጋሚ መጥቶ እንዲያናግረን ሞክረን ፈቃደኛ ሊሆን አልቻለም፡፡ በመጨረሻም ሂደቱን ጠብቆ ድራማው እንዲጠናቀቅ የሶስት ሳምንት ጊዜ ሰጠነው፡፡ ከዚህ በላይ ጣቢያው ምን ማድረግ ነበረበት ትያለሽ? “እማማ ጨቤ”ን “አባባ ጨቤ” በሚል ገፀ ባህሪ በመለወጥ ከጀርባ “መፈንቅለ ድራማ” ተደርጎብኛል ሲል በጣቢያው መተላለፍ የጀመረውን አዲስ ድራማ ይጠቅሳል፡፡ እርስዎስ ምን ይላሉ? እውነት ለመናገር እሱን ለማፈናቀል ድራማ አልተሰራም፡፡

እንዳልኩሽ “ትንንሽ ፀሐዮች” ድራማ ይዘቱ መቀነስና አድማጭንም ማጣት የጀመረውከአንድ አመት በፊት ነው፡፡ ስለዚህ ይህ ድራማ በራሱ ጊዜ እያበቃለት ነው በሚል ነው ድራማ ማዘጋጀት የጀመርነው፡፡ አዲሱ ድራማም አዲስ ይዘት፣ አዲስ ገፀ ባህሪያት፣ አዲስ አቀራረብና አዲስ ርዕስ ያለው እንጂ ከ“ትንንሽ ፀሐዮች” ጋር በምንም መልኩ የሚገናኝ አይደለም፡፡ በድራማው ውስጥ “አባባ ጨቤ” የሚባል ገፀ ባህሪም በፍፁም የለም፡፡ ገና አንድ ሳምንት መተላለፉ ነው፡፡ ርዕሱም “መሀል ቤት” ይሰኛል፡፡ አምስት አመት የዘለቀን ድራማ በሶስት ሳምንት ማጠናቀቅ ይቻላል ብለህ ታስባለህ? ደራሲም ባትሆን ጋዜጠኛ በመሆንህ ስሜቱ ይገባሃል ብዬ ነው፡፡ ደራሲው በሶስት ሳምንት የአምስት አመትን ድራማ ማጠናቀቅ ከባድ ነው ብሏል ---- ቅድም እንዳልኩሽ እኛ ሶስት ሳምንት የሰጠነው፣ የመጨረሻውን መጨረሻ እንዲያጠቃልል እንጂ ድራማው በራሱ ጊዜ አልቋል ብለን ካመንን አንድ አመት አልፎናል፡፡ አመቱን ሙሉ ደብዳቤ እየፃፍን ይዘቱን እንዲያስተካክል ጥረናል፡፡ ቀደም ብዬ እንደገለፅኩት ከአንድ አመት በፊት ነው ድራማው ይዘቱን፣ ዋና ዋና ተዋንያኑን እና አድማጮቹን ያጣው፡፡ በዚህ ምክንያት ድራማው በራሱ ጊዜ ያለቀ ስለሆነ፣ ፎርማሊቲውን ጠብቆ እንዲጠናቀቅ ነው የሦስት ወር ጊዜ የሰጠነው፡፡ ይህን የምንለው ከአድማጭ በሚደርሰን አስተያየትና እኛም እንደጋዜጠኛ በኤዲቶሮያል ቦርድ ገምግመነው ነው፡ ፡

በነገራችን ላይ ተከታታይነት ያለው ታሪክ የያዘ ድራማ አይደለም፡፡ በየሳምንቱ አዳዲስና የተለያዩ ታሪኮች ይዞ የሚመጣ ድራማ ነው፡፡ ስለሆነም እርሱ ቅን ቢሆንና ቢያስብበት፣ በሶስት ሳምንት ለማጠቃለል የሚያስቸግር ነው ብዬ አላስብም፡፡ ዋናው ነገር ድራማው ያለቀለት ከአንድ አመት በፊት ነው፡፡ ድራማው ከተቋረጠ በኋላ ለሁለት ሳምንታት አስተያየት ስትሰበስቡ ነበር፣ የአድማጮች ትክክለኛ አስተያየት ምን ይመስል ነበር? እንዳልሽው ሁለት ሳምንት የአድማጭ፣ አንድ ሳምንት የተዋንያን አስተያት ሰብስበናል። እንደማንኛውም ረ ጅም ጊ ዜ እ ንደቆየ ረ ጅም ድራማ፣ ጊዜ ሰጥተን ጥበቡ አካባቢ ካሉ ምሁራንና ከተዋንያኑ ጋር ቆይታ አድርገን፣ በሶስተኛው ሳምንት ለማጠቃለል ሞክረናል፡፡ የአድማጮችን አስተያየት በተመለከተ እውነት ለመናገር ለረጅም ጊዜ ተወዳጅ ድራማ እንደነበር ነው የገለፁት፡፡ ብዙ አድማጭም አፍርቶልናል፡፡ ይህን አንክድም እናደንቃለን፡፡ በኋላ ላይ ግን ቀደም ስል በነገርኩሽ ምክንያቶች ድራማው ተቀዛቅዟል፡፡ አድማጭም ያለው ይሄንኑ ነው፡፡ ድራማው ቀደም ሲል ያዝናናን ነበር፣ የተለያዩ መረጃዎችን እናገኝበት ነበር፣ በጣም የቅርባችን የሆኑ የምንወዳቸው ገፀ ባህሪያት አሉት፣ ብለዋል፡፡ የጠቃቀስኳቸው ምክንያቶች እንዳሉ ሆነው፣የሚያልቁት ማለቅ ስላለባቸው ነው እንጂ ስለማይወደዱ አይደለም፡፡ ጠቅለል ባለ መልኩ ለማስቀመጥ፣ የአድማጩ አስተያየት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየደከመ መጣ እንጂ ተወዳጅና አዝናኝ ድራማ መሆኑን መግለፃቸውን ልደብቅሽ አልችልም፡፡

ለተወዳጅነቱም ምስክሩ አምስት አመት በጣቢያው ላይ መቆየቱ ነው፣ ይሄ ምንም ጥርጥር የለውም፡፡ እንደ መጀመሪያው መጨረሻው ሊያምር አልቻለም ነው፣ የመቋረጡ ምስጢር፡፡ አጨራረሱም በዚህ መልኩ የሆነው እሱ ተባባሪ ባለመሆኑ ነው፡፡ ጥፋቱ የማንም ይሁን የማን አምስት አመት ተወዳጅ ድራማ ይዛችሁ ዘልቃችሁ፣ ከድራማውም ውጭ ዮናስ የእናንተ ቀደምት ጋዜጠኛ እንደመሆኑ በዚህ መልኩ መለያየታችሁ--- ለሁለታችሁም (ለጣቢያውም ሆነ ለዮናስ) ጥሩ ነው ብለው ያስባሉ? (ሳ….ቅ) በነገራችን ላይ ድራማውን የጀመረው እዚሁ ጋዜጠኛ ሆኖ እየሰራ መሆኑን ታውቂያለሽ? አዎ አውቃለሁ! ያን ጊዜ የመዝናኛ ክፍል ኃላፊ ሆኖ ተመድቦ ይሰራ ነበር፡፡ እኛ የምናውቀው ጋዜጠኛ መሆኑን እንጂ ደራሲ መሆኑን አናውቅም ነበር፡፡ በፋና ህግ መሰረት ጋዜጠኛ ሆነሽ ድርሰት መፃፍ፣ መተወን አትችይም ነበር፡፡ እንደነገርኩሽ በወቅቱ እሱ የመዝናኛ ክፍል ኃላፊ ስለነበረ እንዲከታተለው ተመድቦ፣ እንደ ጋዜጠኛ ብቻ ነው ሲሰራ የነበረው፣ በኋላ ከእኛ ጋ ስራ ከለቀቀ በኋላ ነው የ“ትንንሽ ፀሀዮች” ደራሲ እሱ መሆኑን ያወቅነው፡፡ አልገባኝም! እኛ ዮናስን የመዝናኛ ክፍል ኃላፊ አድርገን መድበነው ድራማውን ይከታተለው ነበር እንጂ የድራማው ደራሲ እሱ መሆኑን አናውቅም ነበር፡፡

ደራሲው ነው ተብሎ ገንዘብ እየመጣ የሚወስደው ሌላ ሰው ነበር፡፡ የድራማውም ደራሲ ስም ያን ጊዜ ያ ብር እየመጣ የሚወስደው ሰው ስም ነበር፡፡ ያንን ሰው የድራማው ደራሲ ነው ብሎ የሚያረጋግጥልን ራሱ ዮናስ ነበር፡፡ ምክንያቱም የመዝናኛው ክፍል ኃላፊ ስለነበር ማለት ነው፡፡ ከዚያስ? ከዚያማ ያኛው ሰው ደራሲ ነኝ ብሎ መጥቶ ገንዘብ ይወስዳል፡፡ በኋላ ስንገነዘበው ገንዘቡ የሚደርሰው ዮናስ ጋ ነበር፡፡ ይህንን ሁሉ ያወቅነው ከጋዜጠኝነት ስራው ከፋና ከለቀቀ በኋላ ነው፡፡ ነገር ግን ድራማው ሲጀመር አንስቶ በህብረተሰቡ ዘንድ ተወዳጅ በመሆኑ፣ ለአድማጭ ክብር ሲባል ድራማው እንዲቀጥል ተነጋግረን፣ በይፋ ደራሲነቱን አውጆ መስረት ጀመረ፡፡ ያን ጊዜ ዮናስ ጋዜጠኛ እንጂ ደራሲ መሆኑን አናውቅም ነበር፡፡ በሌላ አማርኛ ድራማው ከጅምሩ አንስቶ የፋና እንጂ የዮናስ አይደለም፣ምክንያቱም ለሰራበት ስራ ይከፈለዋል፡ ፡ በነገራችን ላይ ከፍተኛ ክፍያ ነበር የሚከፈለው፡ ፡ በየሚዲያው ከሚከፈለው አንፃር በጣም በተሻለ ሁኔታ ለእሱም ለተዋንያኑም እየከፈልን ነው የቀጠልነው፡፡ ይህን እሱንም ብትጠይቂው ይነግርሻል፡፡ ዮናስ ደግሞ ለሙያው ሲል እንጂ ድራማው ከሚያስገባው ገቢ አንፃር የሚከፈለኝ እዚህ ግባ የሚባል አይደለም ባይ ነውይሄ እንግዲህ ሰዎች አንድን ነገር ማጥላላት ከፈለጉ የሚናገሩት ነገር ስለሆነ ምንም ማድረግ አይቻልም፡፡ እኔ ግን ጥሩ ክፍያ እንደሚከፈለውና በዚህም ደስተኛ እንደነበር ነው የማውቀው፡፡

በመጨረሻ የተለያያችሁበትን ሁኔታ በተመለከተ አልመለስልክልኝም---- አዎ ስለ መጨረሻችን ያነሳሽው ነገር አለ---- አዎ አምስት አመት አብረን ቆይተናል፡፡ ቀደምት ጋዜጠኛችንም ነ ው፤ ይ ህንን የ ሚክድም የ ለም፡፡ ስለስንብቱም ቢሆን ጣቢያው የሚያስባቸው ነገሮች አሉ፤ እነዚህ ነገሮች የሚከናወኑት ተቀራርበሽ ስትሰሪ ነው፤ ሌላው ቀርቶ እንደ ደራሲ ማጠቃለያው ላይ አስተያየት እንዲሰጥ ብዙ ጊዜ ወትውተነው ለዚህ ጉዳይ ፈቃደኛ ሊሆን አልቻለም፡፡ የመለያየታችን መጨረሻ አለማማር የጣቢያው ችግር ሳይሆን የእሱ ተባባሪ አለመሆን ነው፡፡ ለመጨረሻ ጊዜ የተፃፈልኝ ደብዳቤ የአንድ ሙያተኛ ክብር የማይመጥን ነው ሲል ዮናስ ወቅሷል፡፡ የደብዳቤው ይዘት ምን ይመስላል? ምናልባት ደብዳቤውን ብታይው ደስ ይለኛል፡፡ ባጋጣሚ ደብዳቤውን የፃፍኩትም እኔ ነኝ፡፡

የድራማው ይዘት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየወረደ መምጣቱን፣ ከአድማጮች የሚመጣውም አስተያየት ይህንኑ የሚያረጋግጥ መሆኑን፣በኤዲቶሪያል ቦርዱ በተደረገው ግምገማም ድራማው በጥሩ ሁኔታ መቀጠል እንዳልቻለ፣ እንደገናም የድራማው ዋና ዋና ገፀ ባህሪያት ከድራማው እየወጡና እያለቁ ስለመሆናቸው፤ በዚህም ምክንያት ድራማው የነበረው ተወዳጅነት እየቀዘቀዘ መምጣቱን፣በዚህም ለጣቢያው እየመጠነ ስላለመሆኑ፣ ይህንንም ከአመት በላይ በደብዳቤም በቃልም ማሳወቃችንንና ይህንንም ለማስተካከል ፈቃደኛ እንዳልሆነ፣በዚህም ምክንያት በሶስት ሳምንት ውስጥ መጠቃለል እንዳለበትና ከሶስት ሳምንት በኋላ በጣቢያው እንደማይተላለፍ መወሰናችንን ገልፀን---- በአክብሮት፣ ፎርማል በሆነ መንገድ ነው የፃፍነው፡፡ ከዚህ ሌላ የሚናገር ደብዳቤ ሰጥተውኛል የሚል ከሆነ ማስረጃ ያቅርብ። ከዚያ ውጭ ሞ ራልና ክ ብር የ ሚነካ ሃ ሳብም ን ግግርም አልተካተተበትም፡፡ ይሄው ነው ምላሼ፡፡

(የ“ትንንሽ ፀሐዮች” ደራሲና አዘጋጅ፤ ዮናስ አብርሃም)

            በፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ላለፉት አምስት አመታት ቅዳሜ ረፋድ ላይ ሲተላለፍ የቆየው “ትንንሽ ፀሐዮች” የሬድዮ ድራማ፣ ከሶስት ሳምንት በፊት ተቋርጧል፡፡ የድራማው ደራሲና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ዮናስ አብርሃም፤ የጀመርኩት ታሪክ ሳይቋጭና ሳያማክሩኝ በጣቢያው ሌላ ድራማ ተጀምሯል፣ እሱ ደግሞ “አባባ ጨቤ” በሚል ከእኔ ድራማ ባልተለየ ድባብ የተቃኘ ነው በማለት ድራማው ያለፈቃዱ መቋረጡንና “መፈንቅለ ድራማ” እንደተፈፀመበት ተናግሯል፡፡ የጣቢያው የፕሮግራም ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ጥበቡ ታደሰ በበኩላቸው፤ ድራማው ከጊዜ ወደ ጊዜ እየደከመና ይዘቱን እያጣ በመሄዱ፣ ለአንድ አመት ማስጠንቀቂያ ከሰጠነው በኋላ ባለማስተካከሉ፣ በሶስት ሳምንት ውስጥ ድራማውን እንዲቋጭ በደብዳቤ ጠይቀነው ምላሽ ሳይሰጥ በመቅረቱ፣ ድራማውን ለማቋረጥ ተገደናል ብሏል፡፡

የአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ ናፍቆት ዮሴፍ፤ ከሁለቱም ጋር ያደረገችውን ቃለምልልስ እንደሚከተለው አጠናቅረነዋል፡፡ “ትንንሽ ፀሀዮች” ድንገት ነው እንዴ ያለቀው ? ለአምስት ዓመት ያህል የዘለቀው “ትንንሽ ፀሀዮች” የሬድዮ ድራማ በእኔ ሀሳብ አላለቀም። እንዲቋረጥ የተደረገው በጣቢያው ፍላጎት ነው። በቂ ጊዜ ሳላገኝ አቋርጥ የሚል ደብዳቤ ደረሰኝ። ደብዳቤው በሶስት ሳምንት ውስጥ ድራማውን እንዳጠናቅቅ የሚያዝ ነበር፡፡ ሆኖም የአምስት ዓመት ታሪክ በሶስት ሳምንት ውስጥ መቋጨት በጣም አስቸጋሪ ስለሆነብኝ ጥዬ ወጥቻለሁ፡፡ በሶስት ሳምንት ውስጥ ታሪክ መቋጨት ያን ያህል አስቸጋሪ ነው እንዴ? በጣም እ ጅግ በ ጣም ያ ስቸግራል! አ ንድን ትልቅ ዘገባ በጋዜጠኝነት ስትሰሪ እንኳን፣ በሁለት ሳምንት እጨርሳለሁ ብለሽ አራት ሳምንት ሊወስድ ይችላል፡፡ ጉዳዩ እየሰፋ ተጨማሪ ግብአቶች እያስፈለጉ ሊራዘም ይችላል፡፡ አምስት አመት የሄደው የኔ ድራማ ደግሞ ትልልቅ ጉዳዮችን ይዟል፣ ከ120 በላይ ተዋንያን እና ጉዳዮቻቸው አሉ፡፡

ይህንን ሰፊ ጊዜና ሰፊ ሀሳብ የያዘ ድራማ፣ በሶስት ሳምንት ማጠቃለል አስቸጋሪ ነው፡፡ ምክንያቱም እንዳንዱ ጅምር ታሪክ፣ ምላሽ ይፈልጋል። ስለዚህ ድራማውን ለማጠቃለል የሚበቃኝን ጊዜ እኔ ነኝ የምወስነው፣ ነገር ግን እኔን ያማከረኝ የለም፡፡ በተደጋጋሚ አብረን እንድንሰራ እና አፅመ-ታሪኩን (ሲኖፕሲስ) እንዳቀርብ ተጠይቄያለሁ፡፡ ሲኖፕሲስ ማቅረብ የምችለው የጀመርኩትን ታሪክ ከሰበሰብኩ በኋላ፣ድራማው እረፍት አድርጎና የሰው አስተያየትተሰብስቦ፣ እንደገና ሁለተኛ ዙር የሚቀጥል ከሆነ፣ ምን መስራት እንዳሰብኩኝ አሳውቃለሁ፡፡ ነገር ግን ረጅም ድራማ ከጫፍ እስከ ጫፍ በሲኖፕሲስ ማስቀመጥ አይቻልም---- የሚል ምላሽ ሰጥቻለሁ፡፡ ቀደም ሲል የጣቢያው ጋዜጠኛ ነበርክ፡፡ የእነማማ ጨቤን ታሪክም እዚያው በጋዜጠኝነት እየሰራህ ነበር የጀመርከው፡፡ በመሀል የጋዜጠኝነት ስራህን ለቀቅህ፡፡ ድራማው ታዲያ እንዴት ቀጠለ? ልክ ነው፡፡ በጣቢያው ጋዜጠኛ ሆኜ እየሰራሁ ነው የጀመርኩት፣ነገር ግን በመሀል በደረሰብኝ በደል ከስራዬ ስለቅ፣ ድራማው ተወዳጅ ስለነበር፣ ለአድማጭ ሲባል በደሌን ወደ ጎን ትቼ በዲኬቲ ኢትዮጵያ ስፖንሰርነት በዚያው መቀጠል ችሏል። በኋላም ዲኬቲ በስፖንሰርነት ለአራት አመት ቀጥሏል፡፡ ዲኬቲ ስፖንሰርነቱን ሲያቆም፣ የድራማውን የወደፊት አፅመ ታሪክ አስቀምጥና፣ አብረን እንስራ አሉኝ፡፡ እኔ ደግሞ በጋዜጠኝነት ታዝዤ ይህን ስራ ተብዬ ልሰራ እችላለሁ፡፡

የድርሰት ስራ ግን ፈጠራ ስለሆነ የሰዎችን ሀሳብ እቀበል ይሆናል እንጂ በዚህ አውጣው፣ በዚህ አውርደው ተብዬ ልሰራ አልችልም፡፡ በዚህ አቅጣጫ ላይ ብታተኩር የሚል ሀሳብ በደፈናው ልቀበል እችላለሁ፡፡ ነገር ግን እንዴት እንደምፅፍ ጭምር እጄ እየተጠመዘዘ የምፅፍ ከሆነ፣ እኔ ደራሲ ሳልሆን ሪፖርት ፀሐፊ ነኝ ማለት ነው፡፡ ይህንን ደግሞ እኔ ራሴ በመርህ ደረጃም የምቀበለው አይደለም፡፡ ድራማውን የማቋረጥ ነገር የተነሳው አሁን ልገልፃቸው በማልፈልጋቸው ግላዊ ጉዳዮች ምክንያት ነው፡፡ ዞሮ ዞሮ ረጅም ድራማ በባህሪው፣ ደራሲውም ቢሆን መንገድ ያመላክታል እንጂ ወደፊት የሚፈጠረውን ነገር ቀድሞ መተንበይ አይችልም፡፡ ወቅታዊ ክስተቶች ይፈጠራሉ፣ እኔ ወደፊት አንድ ነገር እንደሚከሰት የምተነብይበት መለኮታዊ ባህሪ የለኝም፣ ነገር ግን ወቅቱ የሚወልዳቸውን ነገሮች አድማጭን በሚያሳዝንና በሚያስተምር መልኩ በድራማው አካትታለሁ፡፡ ስለዚህ የዛሬ ስድስት ወር ወደፊት ስለሚከሰት ነገር በድራማው ባህሪ መሰረት መተንበይ አልችልም፡፡ ከአንዳንድ አድማጮች በድራማው ዙሪያ አስተያየት ሳሰባስብ፣ “ትንንሽ ፀሐዮች” በወቅታዊ ነገሮች ላይ የሚያተኩር በመሆኑ መቋጫ የለውም---ያሉኝ ነበሩ። አንተ ከጣቢያው ጋር ያለህ ግንኙነት ባይቋረጥ ኖሮ፣ ድራማውን ለመቋጨት ምን ያህል ጊዜ ይበቃህ ነበር? ይህ በጣም የምፈልገው ጥያቄ ነው! ምን መሰለሽ---- ህይወት ይቀጥላል፣ ሰዎች ሊንጠባጠቡ ይችላሉ፡፡

የዚህ ድራማ ባህሪ የሚያሳየው ታሪኮች ይጀመራሉ፣ ይቋጫሉ ግን አንድ ሰው ታሪኩ የሚጠናቀቀው በሞት ሲሰናበት ነው፡፡ እዚህ ድራማ ታሪክ ውስጥም ሰዎች ያድጋሉ፣ እነ አመዲ ወደ ዩኒቨርሲቲ ደረጃ ይገባሉ፡፡ እማማ ጨቤ አርጅተው እስከ ኑዛዜ ይደርሳሉ፣ ከዚያም ህይወት አለ፡፡ በዚህ ስሌት መሰረት የሚያልቅ አይደለም፡፡ እኔ ማቆም የምፈልገው ህዝቡ (አድማጩ) በዚህ ድራማ ጣዕም ካጣ ወይም መስማት ካልፈለገ ብቻ ነው፡፡ እኔ መለኪያዬ የህዝብ አስተያየት ነው፣ እያንዳንዱን ሁኔታና አስተያየት እከታተላለሁ፡፡ በህዝቡ በኩል እንደተወደደ ነበር የቀጠለው፡፡ ለዚህ ረጅም ድራማ መነሻህ ምንድነው? መነሻዬ ለ40 ዓመታት በተከታታይ የሄደ አንድ የውጭ ድራማ ነው፡፡ ለአምስት አመት በተከታታይ የተደመጠ በአገራችን የመጀመሪያው ድራማ ነው - “ትንንሽ ፀሀዮች”፡፡ ከዚህ በኋላም የሚመጡት ድራማዎች “ትንንሽ ፀሐዮች” ተቀባይነት ስላገኘ፤ ተፅዕኖው እንደሚያርፍባቸው ጥርጥር የለኝም፡፡ ምን ያህል ጊዜ ለማጠናቀቅ ይበቃሀል ላልሺው---- እድሜ ልኬን ቢቀጥል ደስ ይለኛል፡፡ “መፈንቅለ ድራማ” ደርሶብኛል ስትል ሰምቻለሁ፡፡ ሌላ ድራማ ጣቢያው ተክቷል? እኔን አጣድፈውና ገፍተው አስወጥተውኝ ሲያበቁ፣ “እማማ ጨቤ” ን “አባባ ጨቤ” ብለው ተክተዋል፡፡ ድባቡ ሁሉ ከእማማ ጨቤ የተለየ አይደለም፡፡

ይህን ወደፊት ህዝብ ይፈርደዋል፡፡ በእኔ እድሜ ልክ ድራማው መቀጠል ይችላል ብለሀል፡፡ አሰልቺ አይሆንም? በፍፁም!! ከጣቢያው ጋር ስምምነት ኖሮ መፃፍ እስከቻልኩ ድረስ በእኔ እድሜ ልክ መጓዝ የሚችል ባህሪ ያለው ድራማ ነው፡፡ በመሀከል እረፍት እያደረገ፣ የህዝብ ገንቢ አስተያየት እየተጨመረበት በጥሩ ሁኔታ መቀጠል ይችላል፡፡ ህዝቡ በአስተያየቱ ሰለቸኝ፣ በቃን፣ ካለ ደግ መቆም ይችላል፡፡ ምክንያቱም የድራማው ግብ አድማጭ ነው፡፡ አሁን እኮ የድራማው ተዋንያን ገፀ-ባህሪ ብቻ ሳይሆኑ ህያው ሆነዋል፡፡ ስለዚህ እነሱን መሰረት አድርጎ፣ ትልልቅ አገራዊ ጉዳዮችን በማንሳትና አዳዲስ ሀሳቦችን በማካተት እንደጣፈጠ እንዲዘልቅ የማድረግ ብቃትም አቅምም አለኝ፡፡ በዚህ አጋጣሚ ይህን ለሚያነቡ ሁሉ የምናገረው፣ ድራማው በውስጤ አላለቀም፣ የመፃፍ አቅምም አላጠረኝም፡፡ ድራማው ከተቋረጠ በኋላ የአድማጮችን ምላሽ ለማወቅ ሞክረሃል? በሚገርም ሁኔታ--- ለድራማው አድማጮች የግል ስልኬ ተሰጥቷል፡፡ ሰዎች በማናቸውም ሰዓት ስልክ ይደውላሉ፣የሚጠቅመኝ ግብአት ስለማገኝበት ሳልሰለች አዳምጣለሁ፡፡ የሚደወልልኝ ስልክ ቁጣም ጭምር አለበት፡፡ አንድ መዝናኛችንና ብዙ የምንማርበት ነው፣ ለምን ቆመ የሚል ቁጣ። በዚህ መልኩ መቋረጥ የለበትም፣ ችግር ካለም ፍቱትና ይቀጥል እያለ ነው - አድማጭ፡፡ እኔ የምፅፈው ህይወትን ነው፡፡ እኔ የምፅፈውን ህይወት የሚኖሩ ሰዎች ያማክሩኛል፡፡ እንደውም የሆነ ወቅት ላይ “የአድማጭ ደራሲያን” ማለት ጀምሬ ነበር፡፡ አድማጮች ይሄ ቢሆን፣ ይሄ ነው ብለው ተነጋግረው የወሰኑትን አንድ ሰው ይደውልልኛል፡፡ ከዚህ በኋላስ እነ እማማ ጨቤን በሌላ ጣቢያ የመቀጠል ሀሳብ አለህ? አድማጮች እንደዚህ እያሉ ነው፡፡

በሌላ የሬድዮ ጣቢያው ቢቀጥል ደስ ይለናል ብለዋል፡፡ ነገር ግን ይህን አደርጋለሁ አላደርግም የሚለውን አሁን አልወሰንኩም፡፡ ማስመር የምፈልገው ድራማውን በተፅዕኖ ሳልፈልግ ማቋረጤን አድማጮች እንዲያውቁ ነው፡፡ ድራማውን በሶስት ሳምንት እንድታጠናቅቅ የተፃፈልህ ደብዳቤ አጠቃላይ ይዘት ምን ይላል? ለድራማው በአስቸኳይ መቋጨት ጣቢያው ያቀረበው ምክንያት ምንድን ነው? መነሻ ችግሮቹ ሌላ ሆነው ሳለ፣ እዚያ ያሉ ጥቂት ሰዎች የራሳቸው ፍላጎት ስላለ የሚሰጡኝ አስተያየት ትክክለኛ አልነበረም፡፡ ረዘመ፣ ታሪኩ አይራመድም፣ የበፊቱን ያህል ጣዕም የለውም--- የሚሉ ሀሳቦችን ሰምቻለሁ፡፡ ሰምቼም ዝም አላልኩም፡፡ የድራማው የታሪክ ፍሰት ምንም ችግር እንደሌለበት ባውቅም ሀሳብና አስተያየት ነው፣ ለማሻሻልና የበለጠ ለማጣፈጥ ጥረት ሳደርግ ቆይቻለሁ፡፡ ነገር ግን ለድራማው መምረርና መጣፈጥ መለኪያዎቼ አድማጮቼ ናቸው፡፡ የዚህ ድራማ አድማጭ - ከገጠር እስከ ከተማ፣ ከህፃን እስከ አዛውንት፣ከምሁሩ እስካልተማረው--- ሁሉንም መደብ ያካተተ ነው። እነሱ ናቸው መመዘኛዎቼ፡፡ ከወራት በፊት በጋራጥሩ የሚሆነውን እናዘጋጅ ተብዬ በአቶ ብሩክ ከበደ ተጠይቄያለሁ፡፡ ሀሳብ መስማት እችላለሁ፡፡ ልታዘዝ ግን አይገባም፡፡ በምን ጉዳይ ልሰራ እንደሚገባ ሀሳብ ልቀበልና የማምንበትን ልወስድ እችላለሁ፡ ፡ ከጣቢያው ሰዎች አ ይደለም ከየትኛውም ሰው ሀሳብ እወስዳለሁ፡፡ ይሄ ለመማርና ለመሻሻል ያለኝን ሀሳብ ያመለክታል፣ መታዘዝ ግን አልችልም፡፡ ዝም ብዬ ስራዬን ቀጠልኩ፡፡ በቃልም ተነጋግረናል፡፡ ድራማውን አንድ መሰረት ካስያዝኩት በኋላ በምን አቅጣጫ እንደምሄድ፣ አንኳር አንኳር ሀሳቦችን ላነሳ እችላለሁ ብዬ ተናገርኩኝ፣ ከዚያ በኋላ ሌላ ደብዳቤ መጣ፡፡

ምን አይነት ደብዳቤ? የመጣው ደብዳቤ የአንድን ሙያተኛ ክብር የሚጠብቅ አይደለም፡፡ ከአንድ ትልቅ ጣቢያም የሚወጣ አይነት አይደለም፣ ስድብ አዘል ነው። ድራማው ደከመ፣ ለዛውን አጣ፣ የሚል አይነት ተገቢ ያልሆኑ ቃላት የሰፈረበት ነው፡፡ በነገራችን ላይ ደግሜ የምነግርሽ መመዘኛዎቼ አድማጮቼ ናቸው፡፡ አድማጩ ድራማውን ባይፈልግ ጣቢያው ለእኔ የወር ደሞዝ አይከፍለኝም፡፡ ስለዚህ መለኪያዬ መላው ህብረተሰብ ነው፡፡ ስለ ስነፅሁፍ ባያውቅ ስለ ህይወት ይረዳል፡፡ ስለ አንዲት የቤት ሰራተኛ ስፅፍ፣ ብዙ የቤት ሰራተኞች ነባራዊ እውነታውን ይነግሩኛል፡፡ ስለዚህ አለቆችና ህብረተሰቡ አንድ አይነት አስተያየትና ግምገማ የላቸውም፡፡ የሆነ ሆኖ የጣቢያው ሰዎች ለእኔ ያላቸው ጥሩ ያልሆነ አመለካከትና ከጀርባው ሌላ ፍላጎት ተጨምሮበት ነው እንጂ፣ ህዝቡ ሰጠ የተባለውና በደብዳቤው ላይ የተገለጸው አስተያየት ለእኔ የሚመጥን አይደለም፣ አድማጩም ይህን አላለም፣ በየቀኑ የሚደርሰኝ አስተያየት የጣቢያው ሰዎች ከፃፉት ደብዳቤ ፍፁም የተለየ ነው፡፡ የግል ጥላቻ፣ መጥፎ አመለካከት እያልክ በተደጋጋሚ ነግረኸኛል፡፡ በጣቢያው ከሚሰሩ ሰራተኞች አሊያም ኃላፊዎች ጋር የተጣላህበት ጉዳይ አለ? ብዙ ታሪክ ያለው የረጅም ጊዜ ሂደት ስለሆነ፣በአሁኑ ወቅት እንዲህ ነው እንደዚያ ነው ለማለት እቸገራለሁ፡፡

ድራማውን ስትፅፍና ስታዘጋጅ ከጣቢያው ጋር ያለህ ስምምነት ምን ይመስላል? ድራማውን አምስት አመት ሙሉ ስፅፍና ሳዘጋጅ የቆየሁት በአጠቃላይ ኃላፊነቱን ይዤ የምሰራው እኔ ነኝ፡፡ ኃላፊዎቹ ድራማውን የሚያዳምጡትም አይመስለኝም፣ ተዋንያኑንም አያውቋቸውም፡፡ እነሱ ደሞዝ ብቻ ነው የሚከፍሉት፣ ይህንን ሁሉ ነገር አስተባብሬ በየሳምንቱ እየተሰራ የሚቀርበው በእኔ የግል ጥረት ነው፡፡ እኔ እሰራለሁ፣ እነሱ ደሞዝ ይከፍላሉ በቃ! ይህ በራሱ ትልቅ እውቅና ሊሰጠው ሲገባ፣ በፍቅርና በሰላም መሰነባበት እየተቻለ--- -ለእኔ ይህ አይገባኝም፣ የብዙ ድራማዎች ፍፃሜ እንዲህ አይደለም፣ በደስታና በፌሽታ፣ ተደግሶና በሰላም ተቋጭቶ ነው የሚሰነባበቱት፡፡ ድራማው በአምስት አመት ጉዞው በገቢ ደረጃ እንዴት ነበር? በገቢ ደረጃ ጥሩ ነበር፣ ስፖንሰር አለው ከዲኬቲ ጋር ነው የተጀመረው፡፡ ለስድስት ወር እንምከረው ብለው እስከ አራት አመት ዘልቀዋል። በየቀኑ ማስታወቂያዎች አሉት፡፡ እኔ ከሚገባው ገቢ በደቂቃ ተሰልቶ በወር ነው የሚከፈለኝ፣ ደሞዝተኛ ነኝ፡፡ ለጣቢያው ጥሩ ገንዘብ አስገብቷል። እኔ አሁን ብስጭቴ ከጣቢያው በማቆሜ አይደለም፣ የተቋረጠበት ሂደት ላይ ነው፡፡

በማቋረጤ ሌላ ቦታ ስለምሰራ፣ ብዙ ገንዘብ አገኛለሁ፡፡ እስካሁንም ስራውን ስለማከብር እንጂ ጣቢያው ከሚያስገባው ገቢ አኳያ ለእኔ የሚከፍለኝ በቂ አይደለም፡፡ በገቢ ብቻ ሳይሆን በተደማጭነትም ድራማው የጣቢያው ጌጥ ነበር ብዬ አፌን ሞልቼ እናገራለሁ፡፡ ተወዳጅ ስለመሆኑ እነሱም አይክዱትም፡፡ ነገር ግን ለእኔ እውቅና ላለመስጠት ከፍተኛ ጥረት አድርገዋል፡፡ በስልክ ደውለው እንኳን እግዜር ይስጥልኝ አላሉኝም! ይሄ በጣም ያሳዝናል፡፡ አሁን ድራማው የፋና ነው ወይስ የአንተ? እስካሁን ወጪ አውጥቶ ያስተላለፈው ራሱ ጣቢያው ነው፡፡ እኔም አልፈልገውም፡፡ ከዚህ በኋላ ያለው እና ገፀ ባህሪያቱ ግን የእኔ ናቸው፡፡ እዚህ ሆነህ ስለጀመርከው እኛ በፈለግነው ምገድ እናስቀጥለዋለን የሚል ሀሳብ ነበራቸው፡፡ ይሄ ፈፅሞ እንደማይሆን እኔም በአፅንኦት ተናግሬያለሁ፡፡ ወደፊት ምን ሀሳብ አለህ? ይሄንን አንድ አመት ካለፈው በኋላ ወደ ቴሌቭዥን ልንለውጠውም በሲዲም ለህዝብ እንድናደርስ አስተያየቶች ይጎርፋሉ፡፡ ጥያቄውም የሚቋረጥ አይደለም፡፡ እኔ ይሄንን ድራማ እየፃፍኩ ሌላም ነገር አዘጋጃለሁ፡፡ ጥሩ ልምድ አግኝቻለሁ። ስለሆነም ከዚህ በላቀ ጭብጥና በማራኪ አቀራረብ በሌላ ጣቢያ ልቀጥል እችላለሁ፡፡ ይሄንን የግድ መቀጠል ላያስፈልገኝ ይችላል፡፡ ነገር ግን አንዴ ህያው የሆኑ ገፀ ባህሪያት ሆነዋልና በተለያየ መንገድ ይገለጋሉ፡፡ የህዝቡን አስተያየት አይቼ እንደሁኔታው አደርጋለሁ፡፡ ነገር ግን እኔ በተሻለ ሁኔታ መምጣት የምችልበት አቅምም ብቃትም ዝግጅትም አ ለኝ፡፡ “ ትንንሽ ፀሐዮች”ን መልሶ በሬድዮ የማምጣት ጉዳይ ላይ ገና አስቤ አልጨረስኩም፡፡ ገፀ ባህሪያቱ የማይረሱና የሚፈለጉ ከሆነ አንድ ነገር ለማድረግ እገደዳለሁ፡፡ ይሄ የኔ መብት ነው፡፡

“276 ሴት ተማሪዎች መጠለፋቸውን ብቻ ታወራላችሁ። በሦስት እጥፍ የሚበልጡ ተማሪዎችን ጠልፈናል። ሰሞኑን በአንድ ቦታ 300 ሰዎች ገድለናል። ለምን ይሄ አይወራም?”

   “አገር በቀል እውቀት” በሚል ሰበብ ስልጣኔን እያንቋሸሸ፤ አልያም የአሜሪካና የአውሮፓ የሳይንስ ትምህርትን እያብጠለጠለ፣ ኋላቀርነትን የሚሰብክ ፕሮፌሰርና ዶክተር ሞልቷል። ቦኮ ሐራም ከዚህ የተለየ አላማ የለውም። ስሙ ራሱ፤ “የምዕራባዊያን ትምህርት ሐራም ነው” እንደማለት ነው። ቦኮ ሐራም፤ ከወገኛ ምሁራን የሚለይበት ዋነኛ ባህርይው፤ ኋላቀርነትን በመስበክ ብቻ የሚመለስ አለመሆኑ ነው። ስብከቱን በተግባር ያሳያል። አዳሪ ትምህርት ቤት ውስጥ ገብቶ ከ50 በላይ ተማሪዎችን መግደል፤ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ማዕከልን አቃጥሎ ደርዘኖችን መጨፍጨፍ፣ ሴት ተማሪዎችን መውሰድ... የሳይንስ ትምህርትን ከማንቋሸሽ አልፎ፤ ሳይንስ የሚያስተምሩና የሚማሩ ሰዎችን ያሳድዳል።

ቦኮ ሐራም በሚፈነጭበት ሰሜናዊ የናይጄሪያ አካባቢ፣ “276 ሴት ተማሪዎች መጠለፋቸውን ብቻ ታወራላችሁ። በሦስት እጥፍ የሚበልጡ ተማሪዎችን ጠልፈናል። ሰሞኑን በአንድ ቦታ 300 ሰዎች ገድለናል። ለምን ይሄ አይወራም?” የቦኮ ሐራምና የአቡበከር ቁጣ፡ “የገደልነውና የጠለፍነውን ያህል አልተወራልንም” የሽብር ፍርሃት ስለነገሰ ብዙዎቹ ትምህርት ቤቶች ተዘግተዋል። የአመቱ ፈተና እንዳያመልጣቸው በአንድ ትምህርት ቤት ለመሰባሰብ የደፈሩት ሴት ተማሪዎችም፤ ከቦኮ ሐራም አላመለጡም። ትምህርት ቤቱን በመውረር ነው 276 ሴት ተማሪዎችን የጠለፋቸው። ከወላጆችና ከቤተሰቦች እሮሮ ጋር የባኮ ሐራም ዝና በመላው አለም የገነነው፤ ከዚሁ ጠለፋ ጋር ተያይዞ ነው። ተቃውሞና ውግዘት ከየአቅጣጫው ከሁሉም የአለም ማዕዘናት ጐረፈ። የባኮ ሐራም አለቃ ነውጠኛው አቡባከር ባለፈው ሰኞ በቁጣ እየደነፋ ለአለማቀፉ እሪታ ምላሽ ሰጥቷል።

ውግዘት ስላበዛ አይደለም አቡበከር የተናደደው። “ጥፋት አልሰራሁም፤ ጥፋቴ ተጋነነ” የሚል አይደለም የአቡበከር ምላሽ። በተቃራኒው፤ “የሰራሁትን ነገር አሳነሳችሁብኝ” በማለት ቁጣውን የገለፀው አቡባከር፤ ከተወራለት የሚበልጥ ጠለፋና ግድያ እንደፈፀመ ድርጊቶቹን በመዘርዘር ተናግሯል። አለም ሁሉ የሚያወራው ስለተጠለፉት ሴቶች ብቻ መሆኑ አናድዶታል። በአመት ውስጥ በሶስት እጥፍ የሚበልጡ ታዳጊዎችን እንደጠለፍን ለምን ይዘነጋል? አለም ሁሉ ይህንን የ ማ ያ ወ ራ ው ለ ም ን ድ ነ ው ? በማለት ብስጭቱን ገልጿል አቡበከር። የተናደደው በዚህ ብቻ አይደለም። ቦካ ሐራም ሴት ተማሪዎችን ከመጥለፉ በፊትም ሆነ በኋላ የፈፀምኳቸው ብዙ “ጀብዱዎች” ቸል ተብለውብኛል ባይ ነው - አቡበከር። ከወር በፊት በናይጄሪያ ዋና ከተማ በአቡጃ የአውቶብስ መነሃሪያ ላይ ባደረሰው የፍንዳታ ጥቃት 71 ሰዎች ተገድሏል።

ይሄስ ለምን ተረሳ? ለምን አይወራም? አቡበከር በዚህ ሁሉ ይንገበገባል። በቅርቡ ከሳምንት በፊትም ቦኮ ሐራም በአንዲት ከተማ መስጊድ ውስጥ የተጠለሉ 300 ሰዎችን ጨፍጭፏል። ይሄም መነጋገሪያ መሆን እንዳለበት አቡበከር አሳስቧል። እውነትም፤ ቦኮ ሐራም፤ በአማካይ በየእለቱ 10 ናይጀሪያዊያን እየገደለ በሁለት ዓመታት ውስጥ ከሰባትሺ በላይ “ግዳይ” ጥሏል። በኋላቀር ባህልኮ ክብር እና ማዕረግ የሚገኘው “ስንት ሰው ገደለ?” በሚል ነው። አቡበከርም “ገዳዬ፣ ገዳዬ” እየተባለ እንዲዘፈንለት ቢጠብቅ አይገርምም። አለም ሌላ ሌላውን ሁሉ ትቶ፣ ስለ ተጠለፉት ሴቶች ብቻ ማውራቱን የሚቀጥል ከሆነስ? አቡበከር፤ ለዚህም ምላሽ አለው። ብዙዎቹ ሴት ተማሪዎች... ገና የ9 አመት፣ ቢበዛ የ12 አመት ታዳጊዎች ናቸው።

“ፈጣሪ ምስክሬ ነው፤ ገበያ አውጥቼ እሸጣቸዋለሁ። የ12 አመት... 9 አመት ልጃገረዶቹን ሁሉ ባል እንዲያገቡ አደርጋለሁ” ሲል ዝቷል - በቪዲዮ ባሰራጨው መልእክት። እስካሁን የተወሰኑት ልጃገረዶች በ12 ዶላር እየተሸጡ ሚስት ለመሆን እንደተገደዱም ተዘግቧል። አቡበከር፤ ለናይጄሪያውያን ያስተላለፈው መልእክት የእልቂት አርአያነቱን እንዲከተሉ የሚጋብዝ ነው። “ሳታመነቱ ገጀራችሁን ጨብጣችሁ ተነሱ። በየቤቱ ሰብራችሁ እየገባችሁ ግደሉ። ያገኛችሁትን ሰው ሁሉ እዚያው በተኛበት ግደሉ” ብሏል - አቡበከር።

ሴንትራል አፍሪካ ለሁለት ከመሰንጠቅ የሚያድናት አልተገኘም

             በአገር ስ ም እ ና ዘ ረኝነት ወ ይም ደ ግሞ በሃይማኖት ሰበብና በአክራሪነት ሳቢያ የሚቃወሱ አገራት እየተበራከቱ፤ በተቃራኒው የመፍትሔ ሃሳቦች እየተመናመኑ መምጣታቸውን ከደቡብ ሱዳንና ከሴንትራል አፍሪካ ትርምስ ማየት ይቻላል። የዘመናችን ነገር! የግጭቱ መነሻ የኢኮኖሚ ችግርና ሙስና፣ የስልጣን ሽኩቻና የምርጫ ውዝግብ ሊሆን ቢችልም፤ ዞሮ ዞሮ ወደ አስፀያፊ ዘረኝነት ወይም ወደ አስቀያሚ አክራሪነት መዝቀጡ የተለመደ ሆኗል። ዩክሬንን አይቶ ደቡብ ሱዳንን፤ ሶሪያን አይቶ ሴንትራል አፍሪካን ማየት ነው። ለሁለቱ አገራት ቀውስ እልባት ለማፈላለግ ደፋ ቀና የሚሉ አልታጡም። ከጐረቤት አገራትና ከአፍሪካ ህብረት ጀምሮ እስከ አሜሪካና አውሮፓ ህብረት፣ እስከ ቻይናና የተባበሩት መንግስታት... ሰላም ለማምጣት ጉድጉድ ያላለ የለም። ነገር ግን እስካሁን ሁነኛ መፍትሔ አልተገኘም።

እናም በ10ሺ የሚቆጠሩ ሰዎች ተገድለዋል፤ ሚሊዮኖች ተሰደዋል። በእርግጥ፤ ሰላም ለመፍጠር የሚካሄዱ ሙከራዎች ዋጋ ቢስ ናቸው ማለት አይደለም። ቢያንስ ቢያንስ፤ በአፍሪካ እንደ ድሮው ያለ ከልካይ “አገር በቀል እውቀት” በሚል ሰበብ ስልጣኔን እያንቋሸሸ፤ አልያም የአሜሪካና የአውሮፓ የሳይንስ ትምህርትን እያብጠለጠለ፣ ኋላቀርነትን የሚሰብክ ፕሮፌሰርና ዶክተር ሞልቷል። ቦኮ ሐራም ከዚህ የተለየ አላማ የለውም። ስሙ ራሱ፤ “የምዕራባዊያን ትምህርት ሐራም ነው” እንደማለት ነው። ቦኮ ሐራም፤ ከወገኛ ምሁራን የሚለይበት ዋነኛ ባህርይው፤ ኋላቀርነትን በመስበክ ብቻ የሚመለስ አለመሆኑ ነው። ስብከቱን በተግባር ያሳያል። አዳሪ ትምህርት ቤት ውስጥ ገብቶ ከ50 በላይ ተማሪዎችን መግደል፤ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ማዕከልን አቃጥሎ ደርዘኖችን መጨፍጨፍ፣ ሴት ተማሪዎችን መውሰድ... የሳይንስ ትምህርትን ከማንቋሸሽ አልፎ፤ ሳይንስ የሚያስተምሩና የሚማሩ ሰዎችን ያሳድዳል።

ቦኮ ሐራም በሚፈነጭበት ሰሜናዊ የናይጄሪያ አካባቢ፣ “276 ሴት ተማሪዎች መጠለፋቸውን ብቻ ታወራላችሁ። በሦስት እጥፍ የሚበልጡ ተማሪዎችን ጠልፈናል። ሰሞኑን በአንድ ቦታ 300 ሰዎች ገድለናል። ለምን ይሄ አይወራም?” የቦኮ ሐራምና የአቡበከር ቁጣ፡ “የገደልነውና የጠለፍነውን ያህል አልተወራልንም” የሽብር ፍርሃት ስለነገሰ ብዙዎቹ ትምህርት ቤቶች ተዘግተዋል። የአመቱ ፈተና እንዳያመልጣቸው በአንድ ትምህርት ቤት ለመሰባሰብ የደፈሩት ሴት ተማሪዎችም፤ ከቦኮ ሐራም አላመለጡም። ትምህርት ቤቱን በመውረር ነው 276 ሴት ተማሪዎችን የጠለፋቸው። ከወላጆችና ከቤተሰቦች እሮሮ ጋር የባኮ ሐራም ዝና በመላው አለም የገነነው፤ ከዚሁ ጠለፋ ጋር ተያይዞ ነው። ተቃውሞና ውግዘት ከየአቅጣጫው ከሁሉም የአለም ማዕዘናት ጐረፈ። የባኮ ሐራም አለቃ ነውጠኛው አቡባከር ባለፈው ሰኞ በቁጣ እየደነፋ ለአለማቀፉ እሪታ ምላሽ ሰጥቷል።

ውግዘት ስላበዛ አይደለም አቡበከር የተናደደው። “ጥፋት አልሰራሁም፤ ጥፋቴ ተጋነነ” የሚል አይደለም የአቡበከር ምላሽ። በተቃራኒው፤ “የሰራሁትን ነገር አሳነሳችሁብኝ” በማለት ቁጣውን የገለፀው አቡባከር፤ ከተወራለት የሚበልጥ ጠለፋና ግድያ እንደፈፀመ ድርጊቶቹን በመዘርዘር ተናግሯል። አለም ሁሉ የሚያወራው ስለተጠለፉት ሴቶች ብቻ መሆኑ አናድዶታል። በአመት ውስጥ በሶስት እጥፍ የሚበልጡ ታዳጊዎችን እንደጠለፍን ለምን ይዘነጋል? አለም ሁሉ ይህንን የ ማ ያ ወ ራ ው ለ ም ን ድ ነ ው ? በማለት ብስጭቱን ገልጿል አቡበከር። የተናደደው በዚህ ብቻ አይደለም። ቦካ ሐራም ሴት ተማሪዎችን ከመጥለፉ በፊትም ሆነ በኋላ የፈፀምኳቸው ብዙ “ጀብዱዎች” ቸል ተብለውብኛል ባይ ነው - አቡበከር። ከወር በፊት በናይጄሪያ ዋና ከተማ በአቡጃ የአውቶብስ መነሃሪያ ላይ ባደረሰው የፍንዳታ ጥቃት 71 ሰዎች ተገድሏል። ይሄስ ለምን ተረሳ? ለምን አይወራም? አቡበከር በዚህ ሁሉ ይንገበገባል። በቅርቡ ከሳምንት በፊትም ቦኮ ሐራም በአንዲት ከተማ መስጊድ ውስጥ የተጠለሉ 300 ሰዎችን ጨፍጭፏል። ይሄም መነጋገሪያ መሆን እንዳለበት አቡበከር አሳስቧል።

እውነትም፤ ቦኮ ሐራም፤ በአማካይ በየእለቱ 10 ናይጀሪያዊያን እየገደለ በሁለት ዓመታት ውስጥ ከሰባት ለደቡብ ሱዳን 5 ፕሬዚዳንቶች ያስፈልጓታል ተባለ ሴንትራል አፍሪካ ለሁለት ከመሰንጠቅ የሚያድናት አልተገኘም እንደልብ እየተዋጉና እየተጨፈጨፉ አመታትን የመቁጠር ልምድ ቀንሷል። በአንድ በኩል የግጭቱ መሪዎች አለማቀፉ የወንጀል ፍ/ቤት ጥርስ ውስጥ እንዳይገቡ ትንሽ ትንሽ ይፈራሉ። በሌላ በኩል፤ ጥላ ከለላ የሚሆንላቸውና “አይዞህ ጨፍጭፍ” እያለ የሚያበረታታ ሃያል አገር በቀላሉ አያገኙም። “ተደራደሩ” እያለ የሚገፋፋና ጫና የሚያሳድር ሲበዛባቸው፤ የሰላም ስምምነት መፈራረማቸው አይቀርም። ግን ምን ዋጋ አለው? ሳምንት ሳይቆይ ግጭቱ ያገረሻል። በሃይማኖትና በዘር የተቧደኑ ነውጠኞችየገነኑበት አስቀያሚ ግጭት ለገላጋይ አስቸጋሪ ሆኗል። አዲስ አበባ መጥተው የሰላም ስምምነት የተፈራረሙ ተቀናቃኞች፤ በማግስቱ ወደ ደቡብ ሱዳን ሲመለሱ ነው የግጭት ዘመቻ የሚጀምሩት። በመሃል፤ ሕይወት ይረግፋል፤ ኑሮ በስደት ይመሳቀላል። አንዲት የደቡብ ሱዳን ከተማ በአንድ ወር ውስጥ ብቻ፣ ተቀናቃኝ ጦሮች በየተራ አንዱ በሌላው ላይ እየዘመቱ፣ አምስት ጊዜ ተፈራርቀውባታል። ታዲያ ዘመቻው በተቀናቃኝ ጦር ላይ ብቻ ያነጣጠረ አይደለም። በውጊያው አሸንፎ ከተማዋን የሚቆጣጠር ጦር፣ የከተማዋ ነዋሪዎች ላይም ይዘምታል - በዘር እየለየ። ደግሞም በድብቅ የሚካሄድ ዘመቻ አይደለም።

የጦር መሪዎች የጭፍጨፋ ዘመቻ የሚያውጁት በሬድዮ ነው። የዘመናችን ግጭቶች መነሻቸውም ምንም ይሁን ምን፤ በአጭር ጊዜ ውስጥ መልካቸው ይቀየርና፣ የጭፍጨፋ ዘመቻ የሚያውጁ ጨካኝ አረመኔዎችገንነው ይወጣሉ። የአንዱን ጐሳ ተወላጆች በጠላትነት እየፈረጁ “ከተማዋን ለቀው ካልወጡ ከየቤታቸው እየለቀማችሁ ግደሏቸው። ሴቶቹን በሙሉ ድፈሯቸው” እያሉ ይቀሰቅሳሉ። እና የሰላም ስምምነት በተፈራረሙ ማግስት የእልቂት ዘመቻ የሚያውጁ ከሆነ ምን ይሻላል? የአገሪቱ የቀድሞ ባለስልጣናት፤ ታዋቂ የህግ ባለሙያዎችና የፖለቲካ ምሁራን ተሰባስበው ያመጡትን የመፍትሔ ሃሳብ ተመልከቱ። “አሉ የተባሉ” የደቡብ ሱዳን ታላላቅ ሰዎች የመፍትሔ ሃሳባቸውን ሲያቀርቡ፤ በመጀመሪያ አገሪቱ አንድ ጠቅላይ ሚኒስትር፣ ሁለት ምክትሎች እንዲሁም 18 ሚኒስትሮች ያስፈልጓታል በማለት ይጀምራሉ። ለአገሪቱ ቀውስ መነሻ የሆነው የፕሬዚዳንት ቦታስ? “አገሪቱ አምስት ፕሬዚዳንቶች ይኖሯታል። በግማሽ አመት እየተፈራረቁ ስልጣን ይይዛሉ” ብለዋል የደቡብ ሱዳን ታላላቅ ሰዎች። የጨነቀው ብዙ ያወራል! የፕሬዚዳንቶችን ቁጥር በማብዛት፤ የስልጣን ሽኩቻንና ኋላቀር የዘረኝነት ፖለቲካን ማስወገድ ይቻላል እንዴ? የሴንትራል አፍሪካ ቀውስም እንዲሁ መላ የሌለው ሆኗል።

በስልጣን ሹክቻ የተጀመረው ቀውስ፤ ያፈጠጠ ያገጠጠ የሃይማኖት አክራሪነት ነግሶበት ወደ እልቂት ለማምራት ጊዜ አልፈጀበትም። “ሰላም አስከባሪ ሃይል” ቢሰማራም፤ የአፍሪካና የአውሮፓ መንግስታት አገር ለማረጋጋት ተፍተፍ ቢሉም፤ መፍትሔ አላመጡም። እንዲያውም “መፍትሔ ሊገኝ ይችላል” የሚል ተስፋም ርቋቸዋል። በሃይማኖት የተቧደኑ አክራሪዎች የገነኑበት ግጭት ምን መላ አለው? ሙስሊም፣ ክርስቲያን እያሉ የጭፍጨፋ ዘመቻ ያካሂዳሉ። እና ምን ይሻላል? ሙስሊሞችን ወደ ሰሜን፣ ክርስቲያኖችን ደግሞ ወደ ደቡብ አቅጣጫ ማሸሽ ብቻ! ከዚህ ውጭ ለጊዜው መፍትሔ አልተገኘም። ለዘለቄታውም አገሪቱ ለሁለት ከመሰንጠቅ የሚያድናት አልተገኘም - እስካሁን።

         የ80 ትልልቅ ድርጅቶች ባለቤት የሆነውና በግዙፍነቱ ከአለም አምስተኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው BERKSHIRE HATHAWAY ለዚህ ማዕረግ የበቃው በዋረን ቡፌት ነው። የዛሬ ሃምሳ አመት፤ አንድ ሰው የኩባንያውን አንድ አክስዮን በ10 ዶላር ቢገዛ፤ በየአመቱ አንድ ዶላር ትርፍ ይደርሰው ይሆናል። ነገር ግን፤ ኩባንያው በከፍተኛ ፍጥነት ስላደገ፣ የአክስዮኑ ዋጋ ዛሬ 170ሺ ዶላር ገደማ ይደርስለታል። አስሯን ዶላር በሃምሳ አመት ውስጥ ወደ 170 ሺ ዶላር መለወጥ ነው የዋረን ቡፌት ስራ።

ከሚዳስ አስደናቂ አፈታሪክ ጋር ይቀራረባል። ሚዳስ፤ እጁ የነካውን ነገር ሁሉ ወደ ወርቅ የመቀየር ችሎታ ነበረው። ደረጃው ይለያይ እንጂ፣ “ምርታማነት” ማለት ይሄው ነው - የዘመናችን “ሚዳስ” - ዋረን ቡፌት እፍኝ ከማይሞላ የእህል ዘር ኩንታል የሚሞላ አዝመራ ማምረት።

በተለያዩ ምክንያቶች የተዳከሙና የከሰሩ በርካታ ኩባንያዎች ዳግም ሕይወት የዘሩት በዋረን ቡፌት አስደናቂ ችሎታ ነው። በቅርቡ 83 አመታቸውን ያከበሩት ታታሪ የቢዝነስ ሰው፤ ዛሬ የ65 ቢሊዮን ዶላር ጌታ ናቸው። ትልቅ ሃብት ነው። በጥረታቸው ከፈጠሩት የሃብት መጠን ጋር ሲነፃፀር ግን ኢምንት ነው። በበርካታ የሃብት ፈጠራ አመታት ውስጥ ብዙዎችን ለሚሊዮነርነት አብቅተዋል። ባለፈው አመት ብቻ፣ የኩባንያው ባለአክሲዮኖች 20 ቢሊዮን ዶላር ገደማ ትርፍ አግኝተዋል። ለሚሊዮኖች የስራና የገቢ እድል ፈጥረዋል።

 ግንባታው የተጓተተው በገንዘብ እጥረትና በክፍያ መዘግየት ነው የቤቶች ልማት፤ የባጀት እጥረትም የጥራት ጉድለትም የለም ብሏል

           በአዲስ አበባ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ግንባታ፣ የባጀት እጥረትና የግንባታ ጥራት ችግር እንዳለባቸው ኮንትራክተሮች የገለፁ ሲሆን ሠራተኞችም ደሞዝ እስከ አራት ወር ይዘገይብናል ሲሉ ያማርራሉ፡፡ አሰሪው የቤቶች ልማት በበኩሉ፤ የግንባታ ጥራት እና የባጀት እጥረት እንደሌለበት ጠቁሞ፣ በአንዳንድ ተቋራጮች አቅም ማነስ የተነሳ የግንባታ መዘግየት መከሰቱን ገልጿል አቃቂ አካባቢ የሚገኘው የቂሊንጦ ሣይት የጋራ መኖሪያ ቤቶች ግንባታ፣ የባጀት እጥረትና የግንባታ ጥራት ችግር እንዳለባቸው ኮንትራክተሮች የገለፁ ሲሆን ሠራተኞችም ደሞዝ እስከ አራት ወር ይዘገይብናል ሲሉ ያማርራሉ፡፡ አሰሪው የቤቶች ልማት በበኩሉ፤ የግንባታ ጥራት እና የባጀት እጥረት እንደሌለበት ጠቁሞ ፤በአንዳንድ ተቋራጮች አቅም ማነስ የተነሳ የግንባታ መዘግየት መከሰቱን ገልጿል፡፡

ከተጀመረ አንድ አመት ከአምስት ወር ገደማ ባስቆጠረው የቂሊንጦ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ግንባታ ሳይት፤ ለ7ሺህ ቤት ፈላጊዎች የሚሆኑ 290 ብሎኮች እየተገነቡበት ሲ ሆን ባ ለፈው ጥ ቅምት ወር የግንባታ ሂደቱን የጎበኙት ከንቲባ ድሪባ ኩማ፤አብዛኞቹ ቤቶች ዘንድሮ በጥር፣ ግንባታቸው ዘግየት ብሎ የተጀመሩት ደግሞ በሚያዚያ እንደሚጠናቀቁ ተናግረው ነበር። ሰሞኑን ሳይቱን የተመለከቱ ሪፖርተሮቻችን እንደገለፁት፤ አብዛኞቹ ቤቶች በብሎኬት እና ባልከን የግንባታ ሂደት ላይ ናቸው፡፡ በሳይቱ ላይ የሚሰሩ የህንፃ ተቋራጮች በሰጡት አስተያየት፤ “ከቤቶች ልማት ለስራ ማስኬጃ በየጊዜው የሚለቀቅልን በጀት ከእጅ ወደ አፍ ነው፤ በዚህም የተነሳ በ ገባነው ው ል መሰረት፤ ስራችንን አጠናቀን ማስረከብ አልቻልንም” ብለዋል፡፡ ሁሉም ተቋራጭ መኖርያ ቤትና ንብረቱን አስይዞ ወደ ስራው መግባቱን የጠቆሙት አንድ ኮንትራክተር፤ አሰሪው አካል የግንባታውን ሂደት እያጤነ ተገቢውን በጀት በወቅቱ ባለመልቀቁ፣ ለከፍተኛ ችግር እንደተጋለጡ ገልፀዋል፡፡

አንዳንድ የሙያ ባልደረቦቻቸው፤ በዚሁ ምክንያት ለኪሳራ ተዳርገው ሥራውን እንዳቋረጡም ኮንትራክተሩ ይናገራሉ፡፡ የቤቶቹ መሰረት እስኪወጣ ድረስ በጀት ቶሎ ቶሎ ይለቀቅላቸው እንደነበር የሚያስታውሱት ተቋራጩ፤ ወደ ማጠናቀቂያው ላይ ግን የበጀት አለቃቀቁ በቁጥ ቁጥ ከመሆኑም ባሻገር፣ ያለ ማስጠንቀቂያ ግንባታውን ነጥቆ ለሌላ አካል መስጠትን የመሳሰሉ ከውል ውጪ የሆኑ አሰራሮች መጀመራቸውን ይናገራሉ፡፡ ከቤቶች ልማት የሚለቀቀው ገንዘብ እኛ ከምንጠይቀው ከ6 በመቶ ብቻ ነው የሚሉት ተቋራጩ፤ ይሄም ለገንዘብ ችግር እንደዳረጋቸውና አብዛኛው ተቋራጭ ከራሱ ኪስ እያወጣ ብዙ ጉዳዮችን እንደሚሸፍን ይገልፃሉ፡፡ “ወር በደረሰ ቁጥር ተቋራጩ የሚከፍለው ደሞዝ እያጣ ከሰራተኛው ጋር የአይጥ እና ድመት ድብብቆሽ ይጫወታሉ፤ ይሄም አለመግባባት እየፈጠረ፣ አንዳንዶችን ለፀብ ሁሉ ይጋብዛል፤ ስራውን ለቀው የሚሄዱም ስላሉ ተቋራጩ በሰራተኛ እጦት ይቸገራል” ሲሉ ችግሮቻቸውን ያስረዳሉ -ተቆራጩ።

ችግሩ ግን የገንዘብ እጥረት ብቻ አይደለም - ተቋራጩ እንደሚሉት፡፡ ብሎኬት፣ ፕሪካስትና ሌሎች የግንባታ ግብአቶችን ራሱ የቤቶች ልማት እንደሚያቀርብ ጠቅሰው፣ አቅርቦቱ በቂ ካለመሆኑም በላይ የጥራቱ ጉዳይ እጅግ አሳሳቢ እንደሆነ ይናገራሉ፡፡ በተለይ ብሎኬቱ ገና ሲነኩት እንደሚፈረካከስ የሚገልፁት ተቋራጩ፤ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችን ለመጥቀም ተብሎ የጥራት ቁጥጥር ያልተደረገለት ብሎኬት እየቀረበ ነው ሲሉ ያማርራሉ። ወደ ሥራ ለመግባት ኮንትራት ስንፈርም፣ ለግንባታ የሚያገለግሉ በቂ የውሃ፣ የመንገድ እና የኤሌክትሪክ አቅርቦት እንዳለ ተነግሮን ነው የሚሉት ሌላው የሳይቱ ህንፃ ተቋራጭ በበኩላቸው፤ እነዚህ ሁሉ አስፈላጊ ግብአቶች ግን እንደተባለው ተሟልተው ባለመገኘታቸው በስራው ላይ ከፍተኛ እንቅፋት እንደፈጠረባቸው ጠቁመዋል፡፡ የተስተካከለ መንገድ ባለመኖሩ ትንሽ ዝናብ ሲዘንብ አካባቢው ስለሚጨቀይ መንቀሳቀስ ¾cV’ < ›Ë”Ç የአዲስ አበባ የጋራ መኖሪያ ቤት ግንባታ እየተጓተተ ነው አይቻልም የሚሉት እኒሁ ቅሬታ አቅራቢ ባለሙያ፤ አንዳንድ ተቋራጮች በራሳቸው ኪሳራ መንገዱን ለማስተካከል እንደሚሞክሩ ገልጸዋል፡ ፡

“የውሃ አቅርቦቱም ከሌላ አካባቢ በተሽከርካሪ የሚመጣ በመሆኑ፣ ለሁሉም ህንፃዎች በበቂ መጠን አይዳረስም፣ የጠብታ ያህል ነው” ብለዋል፡፡ የውሃ እጥረት በመኖሩም የህንፃዎቹ ግድግዳዎች ውሃ የሚጠጡት በጆክ እየተረጨ ነው ያሉት ተቋራጩ፤ ሰዎች ከገቡበት በኋላ ተሰነጣጥቀው ጉዳት እንዳይደርስ እሰጋለሁ ብለዋል። የግንባታ ግብአቶችን መርምሮ ማቅረብን ጨምሮ ሁሉም የስራ ኃላፊነቶች ለህንፃ ተቋራጮች ቢሰጥ ኖሮ፣ አሁን የሚነሱት የጥራት ጥያቄዎች ችግር አይሆኑም ነበር የሚሉት ቅሬታ አቅራቢዎቹ፤ ህንፃ ተቋራጩ ባላመነበት የግንባታ ቁሳቁስና የስራ ሂደት መመራቱ ተገቢ አይደለም ሲሉ ይተቻሉ፡፡ አንድ የህንፃ ተቋራጭ ለሰራተኛና ለግዢ ከሚያወጣው ማትረፍ ይጠበቅበታል ያሉት ተቋራጩ፤ አሰሪው አካል ባጀቱን አፍኖ በመያዙና ተገቢ የአከፋፈል ስርዓትን ባለመከተሉ ህንፃ ተቋራጩ የበይ ተመልካችና ተበዝባዥ ሆኗል ሲሉ ያማርራሉ። እኚህ ቅሬታ አቅራቢ ኮንትራት ከፈረሙ ጀምሮ የመጋዘን ጠባቂ ደሞዝ እና የጫኝ አውራጅ ተብሎ ከሚለቀቅላቸው በጀት ውጪ የቀረውን በራሳቸው እየሸፈኑ መቆየታቸውንም አክለው ገልፀዋል፡፡

ይህም መጀመሪያ ከአሰሪው አካል ጋር ከተዋዋሉት አጠቃላይ የገንዘብ መጠን አንፃር ቢሰላ ኪሳራ እንደሚያሳይ ጠቁመዋል፡፡ ቁጥራቸው ቀላል የማይባል ተቋራጮች፤ ቤት ንብረታቸውን አስይዘው ለስራ ማስኬጃ የተበደሩትን ገንዘብ እንኳ ሳይመልሱ “የስራ አፈፃፀማችሁ ደካማ ነው” ተብለው ግንባታው ወደ መጠናቀቁ ሲደርስ ሥራውን ይነጠቃሉ የሚሉት ሌላው የህንፃ ተቋራጭ፤ እሳቸውም ግንባታውን ካጠናቀቁ በኋላ፣ የማጠቃለያ ስራውን ጨምሮ በርና መስኮት መግጠሙን በጥቃቅንና አነስተኛ ለተደራጁ ወገኖች እንደተሠጠባቸው ይናገራሉ፡ ፡ ህንፃ ተቋራጩ ውሉን ከተፈራረመ በኋላ፣ በብዙ የስራ ሂደቶች ላይ የበይ ተመልካች ነው የሚሉት ቅሬታ አቅራቢው፤ ከግንባታ ስራው በከፍተኛ ደረጃ የሚጠቀሙት በጫኝና አውራጅነት የተደራጁ ወጣቶች እና የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ናቸው ይላሉ፡፡

የቤቶች ልማት፣ ለህንፃው ግንባታ ከ3 ሚሊዮን ብር በላይ ሊከፈለኝ ተስማምቷል፤ ነገር ግን እስካሁን ዘጠኝ መቶ ሺህ አምስት ብር ብቻ ነው የከፈለኝ ያሉት ሌላው ህንፃ ተቋራጭ፤ የገንዘብና የባጀት ጥያቄዎችን ስናነሣ ከፖለቲካ አንፃር እየተመነዘረ ‘ልማታዊ አይደላችሁም’ በሚል እንፈረጃለን በማለት የገቡበትን አጣብቂኝ ይገልፃሉ፡፡ በቤቶች ግንባታ ዘርፍ ሠፊ የስራ እድል መኖሩን ከጓደኞቹ ሰምቶ ከትውልድ ቀየው ደብረ ብርሃን ወደ አዲስ አበባ መምጣቱን የሚናገረው የ27 አመቱ ተስፋሁን፤ ምንም እንኳ የተነገረው የስራ እድል ቢኖርም የደሞዝ ክፍያ ከ2 እና ከ3 ወር በላይ እየዘገየ፣ ከቤት አከራዩ ጋር ንትርክ ውስጥ እየገባ በመቸገሩ በቅርቡ ወደ ትውልድ ቀዬው ለመመለስ መወሰኑን ጠቅሶ ቀደም ሲልም በተመሳሳይ ችግር ሥራቸውን ጥለው ወደ ትውልድ ቀዬአቸው የተመለሱ ጓደኞች እንዳሉት ጠቁሟል፡፡ በደሞዝ መዘግየት የተነሳ ብዙ ጊዜ ከአሠሪዎቹ ጋር መጋጨቱን የሚያስታውሰው ወጣቱ፤ አሠሪዎቹ ደሞዝ ሲጠየቁ በጀት እንዳልተለቀቀላቸው ለማስረዳት ይሞክራሉ ብሏል፡፡ ፕሮጀክቱን በኃላፊነት የሚመራው የአዲስ ከተማ ቤቶች ግንባታ ፕሮጀክት ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ቤቶች ግንባታ ኃላፊ አቶ ሰለሞን ለማ፤ የቤቶቹ አጠቃላይ የግንባታ ሂደት 72 በመቶ መድረሱን ጠቁመው፣ የቤቶቹ ግንባታ ይጠናቀቃል ከተባለበት ጊዜ የዘገየው በተለያዩ ምክንያቶች ቢሆንም በዋናነት ግን በተቋራጮች ድክመት እና ከግብአት አቅርቦት ጋር በተያያዙ ችግሮች እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ የቤቶቹ ግንባታም ሆነ የግንባታ ግብአቶች ከፍተኛ ቁጥጥር እየተደረገባቸው ነው የሚሉት ኃላፊው፤ አሰሪው አካል ብሎኬት፣ ብረትና ፕሪካስትን ጨምሮ 509 ዓይነት ግብአቶችን ለህንፃ ተቋራጩ እንደሚያቀርብ ጠቁመው፣ ተቋራጩ ደግሞ አሸዋ፣ ነጭ ድንጋይ እና ለሙሌት ስራ የሚውል ምርጥ አፈር ያቀርባል ብለዋል፡፡ ብሎኬት እና የተለያዩ የሲሚንቶ ውጤቶችን ጨምሮ ማንኛውም የግንባታ ግብአት በስርአቱ የጥራት ፍተሻ ተደርጎለት የማረጋገጫ ውጤት ሳይሰጠው ለግንባታ እንዲውል አይደረግም ያሉት ስራ አስኪያጁ፤ የጥራት ፍተሻ ማዕከል ውስጥ የጥራት ፍተሻ ተደርጎ ሰርተፍኬት ከተሰጠ በኋላ ነው ለተቋራጩ የሚቀርቡት ይላሉ። የብሎኬት ምርትን በተመለከተም 4ሺህ ያህል ብሎኬት ከተመረተ በኋላ እንደገና የጥራት ቁጥጥር ይደረጋል የሚሉት አቶ ሰለሞን፤ ከዚህ ባለፈም የአማካሪ ድርጅቶቹ የጥራት ተቆጣጣሪዎች በየእለቱ በየሳይቱ ተመድበው የምርት ጥራት ቁጥጥር ያደርጋሉ ብለዋል፡፡

ለግንባታ የሚውሉ የሲሚንቶ፣ የአሸዋ እና መሰል ግብአቶችን ውህደት መጠንና ጥራት ላይም ባለሙያዎች ከፍተኛ ቁጥጥር እንደሚያደርጉ፤ግዢ ሲፈፀም ህግና መመሪያው በሚያዘው መሰረት ጥራታቸው ተፈትሾ እንደሚገዙ ጠቁመው ጥቅም ላይ ከመዋላቸው በፊትም በአማካሪ ድርጅቱ ባለሙያዎች ፍተሻ ይደረግላቸዋል ብለዋል፡፡ በኔ እምነት በቤቶች ልማት የጥራት ደረጃ የሚገነባ ቤት አለ ለማለት እቸገራለሁ የሚሉት ስራ አስኪያጁ፤ እኛ ከምናቀርበው ግብአት ይልቅ ከፍተኛ የጥራት ችግር የሚያጋጥመው ለተቋራጮች በተተውት እንደ አሸዋና አፈር በመሳሰሉት ላይ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ ከውሃ አቅርቦት ጋር የተነሳውን ቅሬታ በተመለከተም አቶ ሰለሞን ሲመልሱ፤ ውሃ ከ4 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በተሸከርካሪ እያመላለሰ የሚያቀርበው ቤቶች ልማት መሆኑን ጠቁመው፤ የውሃ አቅርቦት በሳይቱ ችግር ሆኖ አያውቅም፤ ውሃ ለጥራት ጉዳይ ተጠያቂ በማይሆንበት ደረጃ አድርሰናል ፣ነገር ግን አንዳንድ ተቋራጮች የውሃ መርጪያ ማሽኖች መጠቀም ሲገባቸው በጆግ ይጠቀማሉ፤ ይሄም ቢሆን በተገቢው መንገድ ስለመጠጣቱ በባለሙያዎች ቁጥጥር ይደረግበታል ብለዋል፡፡

ከበጀት እና ገንዘብ አቅርቦት ጋር ተያይዞ ለቀረበው ቅሬታ ሲመልሱም “ባለፈው 2006 የበጀት አመት ለሁለት ሳምንት ያህል ብቻ የበጀት መዘግየት አጋጥሞን ነበር፣ ከዚያ ውጭ የገንዘብ ችግር አጋጥሞን አያውቅም” ያሉት ሥራ አስኪያጁ፤ በኮንትራት ውሉና በፋይናንስ ስርአቱ መሰረት ተገቢውን ክፍያዎች ያለ እንከን እየፈፀምን ነው፤ ለዚህም ማስረጃ የሚሆኑ ሰነዶች አሉን ብለዋል። ሰራተኞች ደሞዝ አልተከፈለንም ብለው እኛ ጋ መጥተው ሮሮ ያሰማሉ፤ ችግሩም እንዳለ በሚገባ እናውቃለን የሚሉት ኃላፊው፤ ችግሩ የተፈጠረው ተቋራጮች የተከፈላቸውን ክፍያ ለሰራተኛ ደሞዝ ሳይከፍሉ ይዘው ስለሚሰወሩ ነው ሲሉ ወቅሰዋል፡፡ ተቋራጩ ስራውን ስለሚነጠቅባቸው ሁኔታዎች ምላሽ የሰጡት ስራ አስኪያጁ፤ ለሁለት ጊዜያት ድክመቶች በማስጠንቀቂያ እንደሚታለፍና ከፍተኛ የአፈፃፀም ድክመት ያለባቸው ተጣርተው ለስራው ቅልጥፍና ሲባል እንደሚነጠቁ ገልፀዋል። በማንኛውም የቤት ግንባታ ላይ 40 በመቶ የስራ ድርሻ ለጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የተሰጠ መሆኑን አክለው የገለፁት ኃላፊው፤ በርና መስኮት እንዲሁም የጣራ ስራ ለነዚሁ አካላት የተተው መሆኑን ተቋራጮችም በሚገባ ያውቃሉ ብለዋል፡፡ ለተቋራጩ የግብአት አቅርቦት የተገደበበት ምክንያት ስራ አስኪያጅ ሲያስረዱ፤ ከፍተኛ ፕሮጀክት ስለሆነና ከ500 በላይ የግንባታ ግብአቶችን መጠቀም ስለሚያስፈልግ መሆኑን ጠቁመው፣

“በዚህ ወር ሌላ የአንበጣ ወረርሽኝ ሊከሰት ይችላል” - ፋኦ የአንበጣ መንጋው ጉዳት እንዳያደርስ እየተከላከልን ነው - ግብርና ሚ/ር

     በግብርና ሚኒስቴር የእፅዋት ጥበቃ ዳይሬክተር ወ/ሮ ህይወት ለማ፤ የአንበጣው መንጋ በሱማሌ ላንድ ተራብቶ በንፋስ እየተገፋ ወደ ኢትዮጵያ መግባቱን ገልጸው፣ በሶማሌና በኦሮሚያ አካባቢ በመስኖ በሚለማ ሰባት ሄክታር ሽንኩርትና ድንች ላይ ጉዳት ማድረሱን ጠቅሰዋል፡፡ ከዚህ ውጭ የከፋ ጉዳት ሳያደርስ በቁጥጥር ስር ውሏል ያሉት ወ/ሮ ህይወት፣ ከመጋቢት አጋማሽ ጀምሮ ከሱማሌ ላንድ የገባው የአንበጣ መንጋ አሁን ያለበት እድሜው ብዙ እንዲመገብ የሚያደርገው እንዳልሆነ ጠቅሰው፣ ሚኒስቴር መ/ቤቱ የመከላከል ስራዎችን በማከናወኑ ጉዳት አላደረሰም ብለዋል፡፡ ከ30 የአንበጣ መንጋዎች ለብቻ ተለይቶ የመጣ አንድ መንጋ ሰሞኑን በአዲስ አበባ በኩል እንዳለፈና የንፋስ አቅጣጫን እየተከተለ እንደሚሄድ ወ/ሮ ህይወት ተናግረው፤ አሁን ያለው መንጋ አድጎና እንቁላል ጥሎ እንዳይራባ የመከላከል እርምጃዎች ተወስደዋል ብለዋል፡፡

ሶማሌ፣ ድሬዳዋና ኦሮሚያ ክልል ላይ የአንበጣ መንጋ እንዳለ ጠቅሰው፣ ለብቻ ተነጥሎ ወደ አዲስ አበባ የመጣው መንጋ ከምስራቅ ወደ ምዕራብ የንፋስን አቅጣጫ ተከትሎ በምዕራብ አዲስ ከአዲስአለም አለፍ ብሎ ወልመራ እንደደረሰና የአካባቢው ግብርና ጽ/ቤቶች አስፈላጊውን የመከላከል ስራ እየሰሩ መሆናቸውን ዳይሬክተሯ ተናግረዋል፡፡ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአለም የምግብ ፕሮግራም፣ በምስራቅ ኢትዮጵያ አካባቢ የተከሰተው የአንበጣ መንጋ ወረርሽኝ፣ በወቅቱ ተገቢው መፍትሄ ካልተሰጠው፣ በአርብቶ አደር ማህበረሰቡ ህልውና ላይ አደጋ ሊያስከትል እንደሚችል ገለጸ፡፡ በዚህ አመት 6 ነጥብ 5 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያንን እመግባለሁ ብሏል፡፡

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የምግብና የእርሻ ድርጅት በበኩሉ፣ የበረሃ አንበጣ መንጋ ወረርሽኙ በኢትዮጵያ፣ በሳኡዲ አረቢያና በኦማን ሊባባስ እንደሚችል ባለፈው ሳምንት ባወጣው መረጃ ጠቁሟል፡፡ የአለም የምግብ ፕሮግራም ቃል አቀባይ ኤልዛቤት ባይርስን ጠቅሶ ሮይተርስ ከጄኔቫ እንደዘገበው፣ በአገሪቱ የተከሰተው የአንበጣ ወረርሽኝ አፋጣኝ መፍትሄ ካልተበጀለት በሰብሎች ላይ ጥፋት ሊያስከትል የሚችል ነው፡፡ “በምስራቃዊ ኢትዮጵያ አካባቢዎች እየታየ ያለው የአንበጣ መንጋ ወረርሽኝ፣ የአለም የምግብ ፕሮግራምን እያሳሰበው ነው፡፡ ወረርሽኙን ለመግታት በወቅቱ ተገቢ እርምጃዎች ካልተወሰዱ፣ የአካባቢው ማህበረሰብ ህልውና አደጋ ላይ ሊወድቅ ይችላል” ብለዋል ቃል አቀባዩዋ፡፡ ባለፉት አራት ተከታታይ አመታት በአገሪቱ ሰሜናዊ ክፍል የጣለው ዝናብ፣ ከሚጠበቀው አማካይ የዝናብ መጠን በታች እንደነበር ያስታወሱት ኤልዛቤት ባይርስ፣ ይህም ከአንበጣ ወረርሽኙ በተጨማሪ ለምርት መቀነስ የሚዳርግ ምክንያት ሊሆን እንደሚችል ተናግረዋል፡፡

የእርስ በእርስ ጦርነትን በመሸሽ ከደቡብ ሱዳን ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ ስደተኞች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መምጣቱን ጠቁመው፣ የአለም የምግብ ፕሮግራም ስደተኞቹን ለመመገብ የያዘውን በጀት እያሟጠጠበት እንደሚገኝና ገንዘቡ እስከ መጪው ወር ሊያልቅ እንደሚችል ተናግረዋል፡፡ ባለፉት ስድስት አመታት፣ ከ120 ሺህ በላይ ደቡብ ሱዳናውያን ስደተኞች ድንበር ተሻግረው ወደ ኢትዮጵያ የገቡ ሲሆን አብዛኞቹም በርሃብ የተደቆሱና የምግብ እጥረት ያጠቃቸው እንደሆኑ የጠቆመው የአለም የምግብ ፕሮግራም፣ ይህም በአገሪቱ የሚገኙ ስደተኞችን አጠቃላይ ቁጥር ወደ ግማሽ ሚሊዮን ከፍ እንዳደረገው ገልጿል፡፡ የአለም የምግብ ፕሮግራም ከስደተኞች በተጨማሪ የምግብ እርዳታ የሚያስፈልጋቸውን ከ1 ሚሊዮን በላይ ችግረኛ ኢትዮጵያውያን እየመገበ እንደሚገኝ ጠቁሞ፣ በዚህ አመትም 6 ነጥብ 5 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያንን የምግብ ድጋፍ ተጠቃሚ እንደሚደርግ አስታውቋል፡፡ የአለም የምግብ ፕሮግራም የኢትዮጵያን መንግስት መረጃ በመጥቀስ፣ የምግብ እጥረት ከአምስት ኢትዮጵያውያን ህጻናት የሶስቱን ዕድገት እያቀጨጨ እንደሚገኝ መናገሩን ዘገባው ጨምሮ ጠቁሟል፡፡

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የምግብና የእርሻ ድርጅት በበኩሉ፣ ባለፈው ሳምንት ባወጣው መረጃ የበረሃ አንበጣ መንጋ ወረርሽኙ በኢትዮጵያ፣ በሳኡዲ አረቢያና በኦማን ሊባባስ እንደሚችል ገልጾ፣ በርካታ የአንበጣ መንጋዎች ከሰሜን ምዕራብ ሶማሊያ በመነሳት፣ ወደ ምስራቃዊ ኢትዮጵያ መግባታቸውን ተናግሯል፡፡ ምንም እንኳን በምስራቃዊ ኢትዮጵያ የተከሰተውን የበረሃ አንበጣ መንጋ ወረርሽኝ በቁጥጥር ስር ለማዋል የአየር ላይና የምድር እንቅስቃሴዎች ቢደረጉም፣ አንበጦቹ ሊራቡና በዚህ ወር አዳዲስ መንጋዎችን ፈጥረው የበለጠ ሊሰራጩ እንደሚችሉ ድርጅቱ ገልጿል፡፡

በአንድ ወር ከ700 በላይ ስደተኞች ድንበር ሲያቋርጡ ተይዘዋል አብዛኞቹ ተባርረው የመጡ ናቸው

      በሶማሌ ላንድ በኩል ቀይ ባህርን በጀልባ ተሻግረው ወደ ሳዑዲ አረቢያና ወደ የመን ለመሄድ ጉዞ የጀመሩ ከ700 በላይ ወጣቶች ሀረር አካባቢ እንደተያዙ የክልሉ ፖሊስ ገለፀ፡፡ ከ700 በላይ የሚሆኑት የተያዙት በአንድ ወር ውስጥ መሆኑን የጠቀሱት የሐረሪ ክልል ፖሊስ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ኮማንደር ጣሰው ቻለው ለአዲስ አድማስ እንደገለጹት አብዛኞቹ ከ4ወር በፊት የሳዑዲ አረቢያ ከሳዑዲ የተባረሩ ስደኞች ተመልሰው እየሄዱ ነው በአንድ ወር ከ700 በላይ ስደተኞች ድንበር ሲያቋርጡ ተይዘዋል አብዛኞቹ ተባርረው የመጡ ናቸው መንግስት ህገወጥ ናችሁ በሚል ወደ ኢትዮጵያ የመለሳቸው ናቸው፡፡

ወጣቶች ከባሌ፣ ከጅማ፣ ከአርሲ፣ ከትግራይ ክልል ከተሞችና፣ ከደሴ በመነሳት ለህገወጥ አስኮብላዮች እስከ 5ሺ ብር በመክፈል በቅብብሎሽ ከከተማ ከተማ የተሸጋገሩ ሃረር የደረሱ መሆናቸው ታውቋል፡፡ ፖሊስ፣ የህገወጥ ስደት ሰንሰለቱ ቦሳሶ ድንበርን በመሻገር በጀልባ ከ40 ሠዓት በላይ በመጓዝ ሳዑዲ አረቢያና የመን ድረስ እንደሚዘልቅ ፖሊስ አስረድቷል፡፡ ህገወጥ ስደትን መከላከል የፖሊስ የእለት ተእለት ስራ እየሆነ መምጣቱን የጠቆሙት ሃላፊው፤ ከሐረር ከተማ ወጣቶችን በድብቅ በአይሱዙ በመጫን ወደ ሶማሌ ላንድ የሚያጓጉዙ ህገወጥ ሰዎች በፖሊስ ቁጥጥር ስር እያዋሉ ነው፤ በሚያዚያ ወር ግን ህገወጥ የስዎች ዝውውር በከፍተኛ ሁኔታ ጨምሯል ብለዋል፡፡ በሶማሌ ላንድ በኩል ባህሩን ለማቋረጥ በጀልባ ቀንና ሌሊቱን የሚደረገው ጉዞ እንደሆነ የጠቆመው ፖሊስ፣ ሰሞኑንም 80 ሰዎችን ጭኖ ይጓዝ የነበረ ጀልባ ተገልብጦ በርካታ ስደተኞች ህይወት ማለፉን አስታውሷል፡፡ በየዕለቱ ከአራት በላይ ጀልባዎች ህገወጥ ስደተኞችን በመጫን ወደ የመን ድንበር እንደሚደርሱና አንድ ጀልባ ከ80 እስከ 90 የሚደርሱ ስደተኞች እንደሚጫንም ገልጸዋል፡፡

  • • ‹‹የፓትርያርኩን ሥልጣን ይገድባል›› በሚል ተተችቷል
  • ‹‹አመራራቸውን በብቃት እንዲያከናውኑ የሚያግዝ ነው›› /የሕግ ረቂቁ/
  • ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ የሚያስተላልፉት በብሔራዊ ቋንቋ ብቻ ይኾናል

       የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ፣ ፓትርያርኩን የሚያግዝ እንደራሴ እንደሚመደብ በሚገልጽና የፓትርያርኩን ሓላፊነትና ተጠያቂነት በጉልሕ የሚያሳዩ አንቀጾችን ባካተተ የሕግ ረቂቅ ላይ እየተወያየ እንደኾነ ተገለጸ፡፡ ቤተ ክርስቲያኒቱ በ1991 ዓ.ም. ያወጣችውን ሕግ ከሌሎች ሕጎች፣ ደንቦችና መመሪያዎች ጋር በማጣጣም፣ ከቤተ ክርስቲያኒቱ ዕድገትና ነባራዊ ኹኔታዎች ጋራ በማገናዘብ ያሻሽላል የተባለው የሕግ ረቂቁ ለውይይት የቀረበው፣ ባለፈው ረቡዕ ጀምሮ በመካሔድ ላይ በሚገኘው የቅዱስ ሲኖዶሱ ኹለተኛ ዓመታዊ መደበኛ የምልዓተ ጉባኤ ስብሰባ ላይ ነው፡፡ የቤተ ክርስቲያኒቱ ሕጎች ኹሉ የበላይ ነው የተባለው የሕገ ቤተ ክርስቲያን ማሻሻያ ረቂቁ÷ ርእሰ አበውና ለካህናቷና ለምእመናንዋ ኹሉ መንፈሳዊ አባት ለኾኑት ለፓትርያርኩ እንደራሴ እንደሚሾም በአንቀጽ 24 ላይ ማስፈሩ ተመልክቷል፡፡ እንደራሴው ‹‹ቅዱስ ፓትርያርኩ ከቤተ ክርስቲያን የተጣለበትን ሓላፊነትና መንፈሳዊ አመራር በሚጠበቀው ብቃትና ደረጃ ለማከናወን እንዲችል የሚያግዝ›› መኾኑ በሕግ ማሻሻያ ረቂቁ ተገልጧል፡ ፡

እንደራሴው የሚመደበው የቅዱስ ሲኖዶሱ አባላት ብቻ በሚሳተፉበት ምርጫ ሲኾን፣ ለምርጫው ሦስት ዕጩዎች በፓትርያርኩና በቅዱስ ሲኖዶሱ አባላት ጥቆማ እንደሚለዩ ተጠቅሷል፡፡ የቤተ ክርስቲያኒቱን ሃይማኖት፣ ቀኖናና ትውፊት የማስጠበቅ እንዲሁም ያለአድልዎ የማስተዳደር ሓላፊነት ላለበት ለፓትርያርኩ በእንደራሴነት የሚመረጠው ሊቀ ጳጳስ ማሟላት የሚገባው መመዘኛ በሕጉ መመልከቱ የተጠቆመ ሲኾን መመዘኛው ለእንደራሴው ከ50 - 60 ዓመት የዕድሜ ገደብ ሲያስቀመጥ፣ የአስተዳደር ችሎታና የመንፈሳዊ አመራር ልምድን፣ መንፈሳዊና ዘመናዊ ዕውቀት አጣምሮ መያዝን እንደሚጠይቅም ታውቋል፡፡ ‹‹ግለሰባዊ የሥልጣን ፈላጊነት ስሜት የሚገንበት፣ የፓትርያርኩን ሥልጣን የሚጋፋና መካሠስን የሚያበረታታ ነው›› በሚል አንቀጹን የተቃወሙ የቤተ ክህነት ሓላፊዎች፣ ምደባው አስፈላጊ ኾኖ ከተገኘም እንደራሴው በፓትርያርኩ ጥቆማ ብቻ መመረጥ እንዳለበት የቃሉ ትርጉም እንደሚያስገደድ በመጥቀስ ይከራከራሉ፡፡

የአህጉረ ስብከት የሥራ ሓላፊዎች በአንጻሩ፣ የእንደራሴው ምደባ፣ መልካም አስተዳደር እንዲሰፍንና ብልሹ አሠራር እንዲታረም የአደረጃጀትና የአሠራርለውጥ ጥናት በማድረግ ላይ ለምትገኘው ቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊ አመራር መጠናከር የራሱ አስተዋፅኦ አለው በሚል እንደሚደግፉት ተናግረዋል፡፡ እንደራሴው ፓትርያርኩን ከማገዝ ውጭ ‹‹ለቅዱስ ፓትርያርኩ ከተሰጡት ተግባራት ውስጥ የሚጋራው የተለየ ሓላፊነት አይኖረውም፤›› በሚል በረቂቁ የሰፈረውን አንቀጽ በመጥቀስ ምደባው ፓትርያርኩን የመጋፋት ሚና እንደሌለውም ገልጸዋል፡፡ ተጠያቂነትን በተመለከተም ፓትርያርኩን ብቻ ሳይኾን ኹሉንም ሊቃነ ጳጳሳትና ኤጲስ ቆጶሳት ለቅዱስ ሲኖዶስ ተጠሪ ከማድረግ፣ በአስተዳደር በደልና በአመራር ጉድለት የካህናቱንና የምእመናኑን አመኔታና ተቀባይነት ማጣትን ጨምሮ ከሀብትና ንብረት ባለቤትነት ጋራ የተያያዙ ዝርዝር የተጠያቂነት አንቀጾች በረቂቁ በመካተታቸው በፓትርያርኩ አልያም በወቅታዊ እይታ ላይ ብቻ የታጠረ ረቂቅ እንዳልኾነ ያስረዳሉ፡፡

ጉዳዩ በዋናነት የቤተ ክርስቲያኒቱን መንፈሳዊ አመራር ከማጠናከር አንጻር ሊታይ ይገባል የሚሉ አስተያየት ሰጭዎች፣ ምልዓተ ጉባኤው የሕግ ማሻሻያ ረቂቁን በጥልቀት በማዳበር የቅዱስ ሲኖዶሱ ሉዓላዊ ሥልጣን በማንም የማይገሠስበት መሣርያ አድርጎ እንደሚያጸድቀው እንጠብቃለን ብለዋል፡፡ በሌላ በኩል፣ ፓትርያርኩ በቤተ ክርስቲያኒቱ ታላላቅ በዓላት ላይ እንዳስፈላጊነቱ እየተገኘ ለሕዝበ ክርስቲያኑ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ የሚሰጠው እንዲሁም በብዙኃን መገናኛ መንፈሳዊ መልእክት የሚያስተላልፈው በአገሪቱ ብሔራዊ ቋንቋ ብቻ እንደሚኾን በሕግ ማሻሻያ ረቂቁ ላይ መስፈሩ ተጠቅሷል፡፡

     በዓለም ላይ በተደጋጋሚ ዝናን አትርፈው ተጠቃሽ ከሆኑት ተረቶች መካከል የሚከተለው ይገኝበታል። ደራሲ ገብረክርስቶስ ኃይለሥላሴ በፃፉት “የሉሲ ከዋክብትና ሌሎችም” በተሰኘው የውርስ ትርጉም የልጆች መልካም ሥነ - ምግባር መጽሐፍ፤ ያገኘነውን ለዛሬ ባጭሩ አቅርበነዋል። በድሮ ጊዜ በአራዊትና በወፎች መካከል ጦርነት ተደርጐ ነበር። የሌት ወፎች ከወፎች ጋር ተሰልፈው ተዋግተዋል። ነገር ግን በመጀመሪያው ጦርነት ወፎች ክፉኛ ተሸነፉ። የሌት ወፎች በሁኔታው ስለሰጉ በየዛፉ አንጓ ላይ ተደብቀው፣ የጦርነቱን የመጨረሻ ውጤት ተጠባበቁ። ድል አድራጊዎቹ አራዊት ወደቤታቸው ሲሄዱ፣ የሌት ወፎች ተደባልቀው አብረው ሄዱ። ትንሽ ከተጓዙ በኋላ፣ አራዊቱ ነቁባቸው (አወቁባቸው)። “ይቅርታ! እናንተ ከወፎች ወገን ተሰልፋችሁ የወጋችሁን አይደላችሁም እንዴ?” በማለት የሌት ወፎችን ጠየቋቸው። የሌት ወፎችም እንዲህ ሲሉ መለሱ።

“ኦ! በፍፁም! እኛ እኮ እንደ እናንተ ነን። ጥፍራችንንና ጥርሳችንን ብትመለከቱ ከእናንተ ጋር ተመሳሳይ ነው። ወንድማማቾች እኮ ነን። ወፎች እንዲህ እንደ እኛ አካል አላቸውን? በፍፁም! እኛ የአራዊት ወገን ነን! (አይጦች ነን!)” አራዊቱ ሁ ኔታውን ከ ሰሙ በ ኋላ ዝ ም አ ሉ። የ ሌት ወ ፎቹንም አ ብረዋቸው እ ንዲሆኑ ፈቀዱላቸው። ከአይጥ ተቆጠሩ ማለት ነው። በሌላ ጦርነት ወፎች ሲያሸንፉ፤ አይጦች ከወፎች ጋር አብረው ለመሄድ ወሰኑ። ዛሬ ደሞ ወፍ ሆኑ ማለት ነው። ሲጠየቁም፤ “እኛኮ እንደእናንተ ነን ክንፍ አለን” አሏቸው። ውሎ አድሮ ወፎችና አራዊት ሰላም ፈጠሩ። አራዊቱም የሌት ወፎቹን “ከእኛ ጋር አይደላችሁም” አሏቸው። ወፎቹም፤ “ከአራዊት ጋር ተሰልፋችሁ ወግታችሁናል። ሂዱልን እናንተ አይጦች! እነሱ ያዛልቋችሁ!” ብለው አገለሏቸው። የሌሊት ወፎች ከአራዊትም ሆነ ከወፎች ጋር መኖር ስላልተፈቀደላቸው፣ ከወፎችና ከአራዊት የተውጣጣው የጋራ ኮሚቴ “ከዚህ በኋላ፣ የሌት ወፎች ሆይ! ሌሊት በአየር ትከንፋላችሁ (ትበርራላችሁ)።

ምንም ጓደኛ አይኖራችሁም። ከእንግዲህ ከሚራመድም ሆነ ከሚከንፍ ተለይታችሁ ትኖራላችሁ” በማለት ወሰነባቸው። ስለዚህ ይኸው እስከዛሬም ድረስ የሌሊት ወፎች በጨለማ ይክነፈነፋሉ፣ በጨለማ ዋሻዎችም ውስጥ ይኖራሉ። የሌት ወፎች እንደ ወፎች ክንፍ ቢኖራቸውም በዛፎች አናትና ቅርንጫፎች ላይ አርፈው አያውቁም። ማንም ቢሆን ስለሌሊት ወፎች አፈጣጠርና ምንነት ደንታ የለውም።

                                                              * * *

በህይወታችን፤ በተለይም በፖለቲካ ህይወታችን ውስጥ ሁለት ቦታ መርገጥ፣ ሁለት አቋም መያዝ፣ በተለይም በፈጠነ ግልብጥብጦሽ ውስጥ እንደእስስት መቀያየር፤ ማንነትን የማጣትን ያህል አደጋ አለው። በኢትዮጵያውያን ዘንድ፤ አርበኛ ነን እያሉ የባንዳ ሥራ መሥራት በታሪክም በኑሮም የእርግማን ዒላማ መሆን ነው። “ጠላትማ ምን ጊዜም ጠላት ነው አስቀድሞ መግደል አሾክሿኪውን ነው” የሚለው የፉከራና የሽለላ ግጥም ያለዋዛ አልተገጠመም። ይሄ ግጥም፤ አይጥ ነው ብለው አቅርበውት የሌሊት ወፍ ሆኖ ለሚገኘውና፤ የሌሊት ወፍ ነው ብለው ሲያቀርቡት አይጥ ሆኖ ለሚገኝ ግለ-ሰብ፤ አልፎ ተርፎም ለሚያንሿክክና ለሚያሾከሹክ ሥራዬ ተብሎ የተፃፈ ሳይሆን አይቀርም። “የአድር - ባይነት ዥውዥው መቼም ማቆሚያ የለውም” ይላል ሌኒን። ዕውነት ነው። መወዛወዙ በራሱ ቢቀር ባልከፋ። ግን ወዲህ ሲመጣ ካንዱ ሲላተም፣ ወዲያ ሲሄድ ከሌላው ሲላተም ጦሱ ለሰው መትረፉ ነው ጣጣው።

ገጣሚና ፀሐፌ - ተውኔት መንግሥቱ ለማ፤ ስለ አንድ ሚስቱ ስለምትደበድበው ባል ሲያወሱ፤ “ሰውዬውን ሚስቱ በትግል ጥላው፤ እላዩ ላይ ተቀምጣ በቡጢ ስታነግለው፤ ጐረቤት ይደርሳል። “ምነው ምን ተፈጠረ?” ይላል ጐረቤት። ይሄኔ ባል፤ የሚስቱን የበላይነትና ነውሩን አለመቀበሉን ለጐረቤቶቹ ለማስረዳት፤ “እስካሁን ከላይ ነበርኩኝ አዲስ ግልብጥ ነኝ! አዲስ ግልብጥ ነኝ!!” እያለ ጮኸ። አቶ መንግሥቱ ይሄን ጨዋታ ያመጡት፣ ባገራችን አዲስ መንግሥት መጥቶ ሁሉም “አሸወይናዬ” ማለት ሲጀምር ነው። ያኔ እንግዲህ “ስለ አዲሱ መንግሥት ለምን አትፅፉም?” ተብለው ሲጠየቁ፤ “እኔ አዲስ ግልብጥ አይደለሁማ!” ባሉበት ወቅት ነው። አዲስ ግልብጥ መሆንና በየጊዜው መገለባበጥ የአንድ ሣንቲም ሁለት ገፅታዎች ናቸው። ከለየለት አድርባይነት ተለይተው አይታዩም። ከአንድ ፓርቲ ወጥቶ ለሌላ ፓርቲ መገበር አድር ባይነት ነው። ከአንድ መንግሥት ወጥቶ ለተቃራኒው መንግሥት እጅ ሰጥቶ ማገልገልም የአድርባይነትን ትርጉም ያሟላል። ከሁሉም በላይ ግን በልብ ማመንዘር ይከፋል። ከዚህ ይሰውረን። ከሀገራችን ችግሮች አንዱ፤ “ወደቀ ሲባል ተሰበረ” ማለታችን ነው። እንዲህ ካልሆነ ሞተን እንገኛለን ብለን ስናበቃ ያ ጉዳይ ከተከወነ፤ አዲስ ቦቃ ልናወጣለት ደሞ ሌላ ፀጉር ስንጠቃ እንጀምራለን።

ደግን ደግ ክፉን ክፉ ማለት መቻል ትልቅ ፀጋ ነው። እርግጥ፤ ዝም ማለትም ሌላው ፀጋ ነው። ቃል በማይከበርበት፣ ፕላን በወግ በማይተገበርበት አገር፣ “ካልታዘልኩ አላምንም” ማለታችን ትክክል መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ፤ ለውጥን ግን በውል ማስተዋል ተገቢ ይሆናል። “ውሃ ከዚህ ቀን እስከዚህ ቀን ድረስ ይጠፋል” ብሎ ቀድሞ ማሳወቅ፣ ውሃ አጠራቅሙ ማለት በትክክለኛ መረጃ አሰጣጥ ማመን ነው። በ ስልክም፣ በ መብራትም፣ በ ምርጫም፣ በ ሹም - ሽ ርም ወ ዘተ አ ስቀድሞ መረጃ እንድናገኝ ቢደረግ መተማመን ይበረክታል። ማንኛውም ወገናችን፤ የመከላከያ ባለስልጣን ይሁን የክልል፣ የጠቅላይ ሚኒስትር ቀራቢ ይሁን ተራ ማሪ፤ ሙስና ከፈፀመ ሙሰኛ ነው! መረጃውን ማግኘትም መብታችን ነው፡፡ በተግባር ምን ማለት እንደሆነ በየቤቱ የሆነውን መቃኘት ነው። መረጃ መስጠት የመሻሻል ምልክት መሆኑን ግን በተቀዳሚ ማድነቅ መልካምነት ነው። ተግባሩ ካረካን መልካም። ውሸት ከሆነ ግን “አርሬ አይተኸኝ ነው እንጂ እኔም ሸክላ ነበርኩ” ያለውን ጀበና በማስታወስ ቸግሮን ነው እንጂ አንታለልም ማለት ግድ ይሆናል።