Administrator

Administrator

      ከንጉሱ ዘመን ጀምሮ ለረዥም ዓመታት በመንግስት ብቻ ተይዞ በነበረው የአየር መንገድ ስራ ውስጥ የግል ባለሀብቶች መሳተፍ የጀመሩት በቅርቡ ነው ማለት ይቻላል፡፡ ይህን እድል በመጠቀም ወደዘርፉ ከተሰማሩ ጥቂት የግል አየር መንገዶች መካከልም ናሽናል ኤርዌይስ አንዱ ነው፡፡ የዛሬ ስድስት ዓመት የተመሰረተው አየር መንገዱ፤ በዘርፉ የሚታየውን የባለሙያ እጥረት ለማቃለል፣ በ2003 ዓ.ም ናሽናል አቪየሽን ኮሌጅን የከፈተ ሲሆን የመጀመሪያዎቹን ሰልጣኞችም ባለፈው ነሐሴ ወር አስመርቋል፡፡ ናሽናል ኤርዌይስ እንዴትና በእነማን ተቋቋመ፣ ምን ምን አገልግሎቶችን ይሰጣል፣ የኮሌጁ አመሰራረትና የስልጠና ሂደቱ ምን ይመስላል በሚሉትና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ የአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ ናፍቆት ዮሴፍ፤ ከናሽናል አቪየሽን ኮሌጅ ዲን ከአቶ ገዛኸኝ ብሩ ጋር ተከታዩን ቃለምልልስ አድርጋለች፡፡

ስለ ናሽናል ኤርዌይስ አመሰራረት ሊነግሩኝ ይችላሉ? ናሽናል ኤርዌይስ በ2001 ዓ.ም ነው የተመሰረተው፡፡ የመሰረቱትም ከዚህ ቀደም በኢትዮጵያ አየር መንገድና በሌሎች አገራት አየር መንገዶች በአብራሪነት የረጅም ጊዜ ልምድ ያካበቱ ኢትዮጵያዊያን ካፒቴኖች ናቸው፡፡

አየር መንገዱ የኢትዮጵያ ሲቪል አቪየሽን ያወጣውን መስፈርትና መመዘኛ በማሟላት ኤር ኦፕሬተር ሰርተፍኬት ሊያገኝ ችሏል፡፡ በዚህ ሰርተፍኬት መሰረት የኤር አምቡላንስ፣ የቪአይፒ እንዲሁም የካርጎና የቻርተር በረራዎች አገልግሎቶችን እየሰጠ ይገኛል፡፡ ይህ ቻርተርድ ኩባንያ አገር በቀል ቢሆንም የሚታገዘው በውጭ አገር ባለሙያዎች ጭምር በመሆኑ በጥሩ ሁኔታ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል፡፡ የግል አየር መንገድ ለማቋቋም የኢትዮጵያ ሲቪል አቪየሽን የሚያስቀምጣቸው መስፈርቶች ምንድን ናቸው? በርካታ ነገሮች ያስፈልጋሉ፤ ከፍተኛ ውጣ ውረድም አለው፡፡ ከኢንቨስትመንት ጀምሮ ለአየር መንገዱ የሚያስፈልጉ ክራፍቶችን ማሟላት፣ የውስጥ አሰራርና አደረጃጀትን ማጠናከር እንዲሁም በቂ የሰለጠነ የሰው ኃይል ከሚጠየቁት መስፈርቶች አንዱ ነው፡፡

ዘርፉ ትንሽ ከበድ ያለ እንደመሆኑ ከአገር ደህንነት፣ ከበረራ ደህንነትና ከአጠቃላይ ሴኩሪቲ አንጻር የሚደረጉ ከፍተኛ ጥንቃቄዎች ያሉ ሲሆን ለዚህም በርካታ ነገሮችን ማሟላት የግድ ነው፡፡ በተለይ የገንዘብ አቅም ወሳኝ ነው፡፡ መስፈርቶቹን ለማሟላት የግድ ገንዘብ ያስፈልጋል፡፡ ናሽናል ኤርዌይስ እንግዲህ እነዚህን አሟልቶ ነው የተመሰረተው፡፡ የበረራ አገልግሎታችሁ በአገር ውስጥ የተገደበ ነው ወይስ ወደ ውጭም ትበራላችሁ? ቀደም ብዬ እንደገለፅኩት፤ የቪአይፒ እና የአንቡላንስ አገልግሎቶችን በአብዛኛው በቱሪስት መዳረሻ አካባቢዎች ነው የምንሰጠው፡፡ ከዚያ ውጭ ቻርተርድ በረራዎች ይኖራሉ፡፡ ይህ ማለት መንገደኞችን ይዞ መጓዝ ነው፡፡ በብዛት የአገር ውስጥ በረራ እንሰራለን፡፡ ወደ ጎረቤት አገሮች ለምሳሌ ሶማሌላንድ፣ ጁባ፣ ናይሮቢና መካከለኛው አፍሪካ ድረስ የመብረር አቅም አለን፡፡ አየር መንገዱ በተለያዩ ኢትዮጵያዊያን አብራሪዎች መቋቋሙን ነግረውኛል፡፡ በዋናነት የሃሳቡ ጠንሳሽ ማን ነው? ሀሳቡን በመጠንሰስ እውን እስኪሆን ድረስ ተነሳሽነቱን የወሰዱት ካፒቴን አበራ ለሚ ይባላሉ፡፡ እኚህ ኢትዮጵያዊ ለረጅም ጊዜ ኢትዮጵያ አየር መንገድን ሲያገለግሉ የቆዩ ናቸው፡፡ አየር መንገዱን ከሌሎች ሰዎች ጋር ካቋቋሙ በኋላ በዘርፉ ያለውን የሰለጠነ የሰው ሃይል እጥረት በማጤን ኮሌጁ እንዲመሰረት ሃሳብ ያፈለቁትም ካፒቴን አበራ ናቸው፡፡

እኚህ ሰው ድርጅቱን በመምራትና በማስተባበርም ከፍተኛ ድርሻ አላቸው፡፡ የመነሻ ካፒታላችሁ ምን ያህል ነው? በአሁኑ ሰዓት አየር መንገዱ ምን ያህል አውሮፕላኖች አሉት? ኢንቨስትመንቱ በጣም ከባድ ነው፤ አሁን እንዲህ ነው እንዲህ ነው ለማለት አስቸጋሪ ነው፡፡ እንኳንስ አንድ የግል አየር መንገድ ለመክፈት ቀርቶ አንድ አነስተኛ ምግብ ቤት ለመክፈት እንኳ ምን ያህል ፈተና እንዳለው ግልፅ ነው፡፡ ስለዚህ አሁን በቁጥር ማስቀመጡ አስፈላጊ መስሎ ባይታየኝም እጅግ ከፍተኛ ኢንቨስትመንት እንደሆነ ልደብቅሽ አልችልም፡፡ ምን ያህል አውሮፕላኖች አላችሁ ለሚለው፣ አንድን አየር መንገድ ለማቋቋም የተቀመጠውን መስፈርት ያሟላንባቸውን ያህል አሉን፡፡ አንዳንዴ ስራ ሲበዛና የእኛ ጥገና ላይ ሲሆኑ የሌሎችን የምንጠቀምበት ሁኔታ አለ፡፡ የካፒታል መጠኑንና የአውሮፕላኖቹን ቁጥር ለመግለፅ ያልፈለጋችሁበት ምክንያት አልገባኝም… ወደፊት ይፋ እናደርጋለን፡፡ አሁን በራሳችን ምክንያት ግልፅ ማድረጉ አስፈላጊ መስሎ ስላልታየን ነው፡፡ እሺ-- ናሽናል አቪየሽን ኮሌጅ እንዴት ነው የተመሰረተው? ኮሌጁን የመሰረተው ናሽናል ኤርዌይስ ነው፡፡ የተመሰረተበት ምክንያት የናሽናል ኤርዌይስ ሰዎች አየር መንገዱን ከመሰረቱ በኋላ፣ በአገር ደረጃ በዘርፉ የሰለጠነ የሰው ሃይል እጥረት እንደነበረ በመረዳታቸው፣ ለምን ኮሌጅ ከፍተን ችግሩን አናቃልልም በማለት ነው የመሰረቱት፡፡ እንደሚታወቀው የአቪየሽን ዘርፍ በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ እጅግ እያደገ ያለ ዘርፍ ነው፤ ሆኖም በአገራችን ብዙ ባለሙያዎች የሉም፡፡

ኢትዮጵያ አየር መንገድ ለራሱ የሚያሰለጥናቸው የአቪየሽን ባለሙያዎች አሉት፡፡ በግል ደረጃ ግን ከዚህ በፊት የለም፡፡ በመሆኑም ካፒቴን አበራ ለሚ ሃሳቡን ካዳበሩ በኋላ፣ ይህን የባለሙያ ችግር ለመቅረፍ ኮሌጁ ተቋቋመ፡፡ የመጀመሪዎቹ 140 ያህል ሰልጣኞችም ነሐሴ 3 ቀን ለምርቃት በቅተዋል፡፡ ኮሌጃችሁ በአቪየሽን ዘርፍ የሚሰጣቸው ስልጠናዎች ምን ምን ናቸው? በትምህርት ሚኒስቴር በኩል ስልጠና ለመስጠት ፈቃድ ስንጠይቅ፣ዘርፉ በቴክኒክና ሙያ ስልጠና ነው የተመደበው፡፡ ስልጠናው በዓለም አቀፍ ደረጃ ጥራቱን የጠበቀ እንዲሆንና ሰልጣኞቹ የትኛውም ዓለም ቢሄዱ ተቀባይነት እንዲኖራቸው ለማድረግ፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከሚታወቀውና ካናዳ ከሚገኘው ኢንተርናሽናል ኤር ትራንስፖርት አሶሴሽን (IATA) ጋር ለመስራት ከፍተኛ ጥረት ስናደርግ የቆየን ሲሆን አሁን ተሳክቶልናል፡፡ አያታ የራሱ መስፈርትና መመዘኛ አለው፤ ያንን አሟልተን በእነሱ የተፈቀደልን የስልጠና ማዕከል ለመሆን ችለናል፡፡ በዋናነት በበረራ አስተናጋጅነት፣ ትኬቲንግ እና ሪዘርቬሽን፣ በካርጎ፣ በኤርፖርት ኦፕሬሽን ኤርላይን ከስተመር ሰርቪስና ሌሎች ዘርፎች ስልጠና እንሰጣለን፡፡ ሰልጣኞቻችን በአገር ደረጃ መስፈርቱን አሟልተው ከሰለጠኑ በኋላ፣ አያታ በአመት አራት ጊዜ ፈተናዎችን ይሰጣቸዋል፤ ያንን አሟልተው ሲገኙ አለም አቀፍ የምስክር ወረቀትና ዲፕሎማ ያገኛሉ፡፡

የመጀመሪያ ዙር ተመራቂዎቹ በዚህ መልኩ ነው የተመረቁት? አዎ! በዚህ መልኩ ነው የተመረቁት፡፡ እነዚህ ልጆች ሰርተፍኬታቸውንና ዲፕሎማቸውን ይዘው የትኛውም ዓለም ላይ በሰለጠኑበት ዘርፍ መስራት ይችላሉ፡፡ ኮሌጃችሁን ለማሳደግና ወደ ከፍተኛ ትምህርት ለመሸጋገር ከውጭ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር የመግባቢያ ሰነድ መፈራረማችሁን ሰምቼ ነበር፡፡ እስቲ ስለሱ ይንገሩኝ… እስካሁን በዘርፉ በአጭር፣ በመካከለኛና በረጅም ስልጠና ከፍተኛ ፍላጎት መኖሩን ስናጠና ቆይተናል፡፡ በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ሰነድ የተፈራረምነው ከሶስት የቻይና ዩኒቨርሲቲዎች ጋር ነው፡፡ እነዚህን ዩኒቨርሲቲዎች የመረጥንበት ምክንያት በዘርፉ ደረጃውን የጠበቀ ስልጠና በመስጠት የሚታወቁ በመሆናቸው ነው፡፡ ክፍያቸው ተመጣጣኝና ከሌላው የተሻለ መሆኑ ሌላው ምክንያታችን ነው፡፡ ስለ እነዚህ ዩኒቨርሲቲዎችና ስለሚሰጡት የሙያ ስልጠና ሊነግሩኝ ይችላሉ? አንደኛው ቫንጋይ ኤሮስፔስ ዩኒቨርሲቲ ነው፡፡ ይህ ተቋም በቻይና በጣም ግዙፍና ታዋቂ ነው፡፡ በኤሮኔቲካል ኢንጂነሪንግ፣ በኤሮክራፍት ማኑፋክቸሪንግና ዲዛይኒንግ፣ በኤሮስፔስ ኢንጂነሪንግ፣ በኤሮክራፍት ቴክኒሺያን፣ በሲቪል ኢንጂነሪንግ… ባችለር ኦፍ አቪየሽን ሳይንስ ስልጠናዎችን ይሰጣል፡፡ ሁለተኛው ሊኒዋንግ ዩኒቨርሲቲ የሚባል ሲሆን ተቋሙ በፔትሮሊየም ኢንጂነሪንግ፣ በጋዝ ኢንጂነሪንግ በኢንቫይሮሜንታል ኢንጂነሪንግ… ስልጠና ይሰጣል፡፡ እኛ ፍላጎት በበዛበት ዘርፍ አብረን ስልጠና ለመስጠት አስበናል፡፡ ሶስተኛው ሊኒዋንግሸዋ ዩኒቨርሲቲ ነው፡፡ ተቋሙ በቢዝነስና ኢኮኖሚ ዘርፎች ለምሳሌ በቢዝነስ አድሚንስትሬሽን፣ በቢዝነስ ማኔጅመንት፣ በኢንተርናሽናል ትሬድና በመሳሰሉት በመጀመሪያና በሁለተኛ ዲግሪ ያሰለጥናሉ፡፡ ከእነዚህ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር ነው የመግባቢያ ሰነዱን የተፈራረምነው፡፡ ስምምነታችሁ ምን ይመስላል? ወደተግባር ለመግባትስ ምን እየጠበቃችሁ ነው? ስምምነታችን በትብብር ለመስራት ነው፡፡ በአገራችን እነዚህን የስልጠና ማዕከላት ለመገንባት ረጅም ጊዜና ከፍተኛ ወጪ ይጠይቃል፡፡ ይህን ስልጠና ሊሰጡ የሚችሉ መምህራንም የሉንም፡፡

በተጨማሪም ለስልጠናው የሚያስፈልጉ ግብአቶችን በአጭር ጊዜ ውስጥ ለማሟላት ያስቸግራል፡፡ ስለዚህ በትብብር ነው የምንሰራው፡፡ ትብብር ሲባል ለምሳሌ ስልጠናው አራት ዓመት ከሆነ፣ ተማሪዎች ሁለቱን ዓመት እዚህ ሰልጥነው፣ ቀሪውን ሁለት ዓመት በቻይና ሰልጥነው እንዲመለሱ ይደረጋል፡፡ ከዚያ አቅማችንን በማደራጀት የራሳችንን መምህራን ስናፈራና በቂ የስልጠና ማዕከላት ስንገነባ፣ ስልጠናው እዚሁ ተጀምሮ እዚሁ ይጠናቀቃል፡፡ ወደተግባር ለመግባት የምንጠብቀው የከፍተኛ ትምህርት ጥራትና አግባብነት ኤጀንሲን እውቅና ነው፡፡ በአቪየሽን ዘርፍ እየሰራን ቢሆንም ከዘርፉ ጋር ከፍተኛ ቁርኝት ያለው የሆቴል ኢንዱስትሪ ነው፡፡ ኢንዱስትሪው በአገራችን እየሰፋና እያደገ ቢሄድም የሆቴል ዘርፍ የባለሙያ እጥረት አለ፡፡ እየተሰጠ ያለው ስልጠናም ደረጃውን የጠበቀ አይደለም፤ ስለዚህ በዚህም ዘርፍ በአጭር ጊዜ ስልጠና ለመስጠት ኢንተርናሽናል ኮሜርሺያል ማኔጅመንት (ICM) ከተባለ የለንደን ድርጅት ጋር እየሰራን ነው፡፡ ሰልጣኞቹን እንደ አያታ ሰርቲፋይድ ያደርጋቸዋል፡፡ ከዚያም የትኛውም አገር ሲሄዱ ተቀባይነት አግኝተው ይሰሩበታል ማለት ነው፡፡ የከፈታችሁት ኮሌጅ በቴክኒክና ሙያ ደረጃ ስልጠና ቢሰጥም በአገራችን እምብዛም የተለመደ ዘርፍ ባለመሆኑ የመምህራን ችግር እንደሚያጋጥማችሁ የታወቀ ነው፡፡

እንዴት ተወጣችሁት? እንዳልሽው መምህራን ማግኘት ፈታኝ ነበር፡፡ በዚህም የተነሳ መምህራንን ከኬንያ ማስመጣት ነበረብን፤ ኬንያ በዚህ ዘርፍ የዳበረ ልምድ አላት፡፡ የማሰልጠኛ ተቋማቶቻቸው በመንግስትም በግልም ደረጃ ከኢትዮጵያ በጣም የተሻሉ ናቸው፡፡ ተማሪዎቻችንን ያሰለጠኑልን በአብዛኛው የኬኒያ መምህራን ናቸው፡፡ እነዚህን መምህራን በከፍተኛ ክፍያ ነው ያመጣናቸው፡፡ የኮሚዩኒኬሽንና የስነ-ልቦና ስልጠናዎችን የወሰዱት ግን በአገራችን መምህራን ነው፡፡ እንደስትራቴጂ የያዝነው ከእነዚህ መምህራን ልምድ በመውሰድ፣ከሰልጣኞችም አቅም ያላቸውን በማስቀረት በረጅም ጊዜ ሂደት በአገራችን መምህራን ለመተካት ነው፡፡ ለቀጣዮቹ አራትና አምስት ዓመታት ግን ኢትዮጵያዊ መምህራንን ማግኘት አስቸጋሪ ነው፡፡ አንዳንዴ እንደውም ናሽናል ኤርዌይስ ውስጥ ያሉ ባለሙያዎችንም ለመጠቀም እንገደዳለን፡፡ እናም በቀጣይ ላሰብናቸው የከፍተኛ ትምህርት ስልጠናዎች ከቻይና መምህራንን ማስመጣት ይኖርብናል፡፡ አሁን ካስመረቃችኋቸው ተማሪዎች ውስጥ ወደ ስራ የተሰማሩ አሉ? አዎ አሉ! ከተመረቁም በኋላ ሳይመረቁም የተቀጠሩ አሉ፡፡ ለምሳሌ ሶስት ልጆች በበረራ አስተናጋጅ፣ በተለያዩ ዘርፎችም ብዙዎች ተቀጥረዋል፡፡

ዘርፉ የስራ ችግር የለበትም፡፡ ምክንያቱም ብዙ አየር መንገዶች ኢትዮጵያ ውስጥ እየተከፈቱ ነው፡፡ ወደ መካከለኛው ምስራቅና ሌሎች አገራት ሄደው እየሰሩ ያሉም አሉ፡፡ ለስልጠናው ብዙ ወጪዎች እንደምታወጡ ነግረውኛል፡፡ ለምሳሌ ፋየር ፋይቲንግ ለማሰልጠን ለሲቪል አቪየሽን ትከፍላላችሁ፡፡ በመጀመሪያ የህክምና እርዳታ ለማሰልጠን ወደ ቀይ መስቀል፣ ዋና ለማሰልጠን ደግሞ ወደ ትልልቅ ሆቴሎች ትሄዳላችሁ፡፡ የምታስተምሩባቸው መጻህፍትና ሞጁሎች ከውጭ ሲገቡ ይቀረጣሉ፡፡ ከዚህ አንፃር ለስልጠናው የምትጠይቁት ክፍያ ውድ ይመስለኛል፡፡ ልክ ነኝ ወይስ ተሳስቻለሁ? አንድ ሰው ወደ ትምህርት ዘርፍ ሲሰማራ፣ኢንቨስት ያደረገውን በአጭር ጊዜ አይመልስም፡፡ እንደ ማንኛውም ንግድ አይደለም፡፡ የረጅም ጊዜ ኢንቨስትመንት ነው፡፡ በሌላ በኩል ኢትዮጵያ ውስጥ ለትምህርት የሚከፈለው ክፍያ በጣም ርካሽ ነው፡፡ ድንገት ተነስተሽ የአቪየሽን ት/ቤት ልክፈት ብትይ አትችይም፡፡ ልጆቹ ብቃት እንዲኖራቸው ከውጭ ተቋማት ጋር ስምምነት ስናደርግም እነ አያታና አይሲኤም የሚያስከፍሉን ክፍያ አለ፡፡ ቅድም ከላይ የገለፅሻቸው ፋየር ፋይቲንግ፣ የመጀመሪያ ህክምና እርዳታ፣ የዋና ስልጠና ወዘተ የምንሰጠው ከሌሎች ድርጅቶች ጋር ሲሆን የመማሪያ ግብአቶችን የምናስመጣውም ከውጭ ነው፡፡ ይሄን ሁሉ ስታስቢው አሁን የምናስከፍለው በጣም ትንሽ ነው ማለት ይቻላል፡፡

እንደየስልጠናው አይነትና የጊዜ መጠን (ከ6-8 ወር ነው) ትንሹ ክፍያ ዘጠኝ ሺህ ብር ሲሆን ትልቁ ክፍያ 34ሺ ብር ነው፤ ነገር ግን ሰልጣኞች ተመርቀው ሲወጡ የሚቀጠሩት በጥሩ ደሞዝ ነው፤ ተፈላጊም ናቸው፡፡ በዘርፉ ዋና ዋና ፈተናዎች የሚባሉት ምንድን ናቸው? በርካታ ፈተናዎች ነበሩ፡፡ ራሱ በዘርፉ መሰማራት አንድ ትልቅ ፈተና ነው፡፡ በግል ዘርፍ ኮሌጅ ስትከፍቺ፣ የግንዛቤ እጥረት ስላለ በግል ተምረን ማን ይቀጥረናል የማለት አዝማሚያ ነበር፡፡ ይህን ለመለወጥ ብዙ ፈተናዎችን አልፈናል፡፡ ከውጭ የሚመጡ የስልጠና ግብአቶች ከፍተኛ ቀረጥ ይጣልባቸዋል፡፡ ብቻ በርካታ ችግሮች ነበሩ፤ አሁን በሂደት እየተቀረፉ ነው፡፡

            ኢስት አፍሪካ ቦትሊንግ አክሲዮን ማህበር (ኮካኮላ) ከመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በመተባበር፣ በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ከፍተኛ ውጤት ያላቸው ተማሪዎች በገንዘብ ችግር ውጤታቸው እንዳይቀንስ የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ እንደሚያደርግ አስታወቀ፡፡ ከአዲስ አበባ፣ ከባህርዳርና ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲዎች ለተመረጡ ከ3.0 ነጥብ በላይ ውጤት ላላቸውና ለአነስተኛ ገቢ ቤተሰብ ተማሪዎች፣ለሶስት ዓመት የኪስ ገንዘብ እንደሚሰጥና ለትምህርት አስፈላጊ የሆኑ ቁሶችን ድጋፍ ለማድረግ 1.2 ሚሊዮን ብር መመደቡን የኢትዮጵያ ኮካኮላ የሰው ኃይል ሀብት ማናጀር አቶ አንተነህ ተገኝ ገልጸዋል፡፡

በዚህ ዓመት ድጋፍ የሚደረግላቸው ተማሪዎች 30 ሲሆኑ 11ዱ አነስተኛ ገቢ ያላቸው የኩባንያው ሰራተኛ ልጆች ሲሆኑ የተቀሩት፣አነስተኛ ገቢ ያላቸው ቤተሰቦች ልጆች መሆናቸውን የተመረጡበት ዩኒቨርሲቲዎች እንዳረጋገጡላቸው ጠቁመዋል፡፡በቀጣዩ ዓመት 15 ተማሪዎች እንደሚጨመሩና ገንዘቡም ወደ 1.8 ሚ ብር እንደሚያድግ የጠቀሱት አቶ አንተነህ፣ ለተማሪዎቹ በየወሩ 500 ብር የኪስ ገንዘብ ይሰጣል ብለዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ በየዓመቱ አንድ ጊዜ አስፈላጊ የትምህርት ቁሳቁስ እንደሚሟላላቸው፣ትምህርታቸውን እንዴት እየተከታተሉ እንደሆነ በኩባንያው ኃላፊዎች እንደሚጎበኙ፣ ለመመረቂያ ጽሑፍ ድጋፍ እንደሚደረግና በየዓመቱ መጨረሻ ት/ቤት ሲዘጋ ወደ ኩባንያው መጥተው እንደየትምህርታቸው በንድፈ ሀሳብ የተማሩትን በተግባር እንደሚለማመዱ፣ በዚህ ወቅትም ለምግብና ለትራንስፖርት ወጪ የሚሆን ገንዘብ እንደሚሰጣቸው አስረድተዋል፡፡

ተማሪዎቹ በመንግስት 70/30 የትምህርት ፖሊሲ መሰረት፤ ከሳይንስ ዘርፍ የተመረጡ (በአብዛኛው ከኢንጂነሪንግና ከኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ) መሆኑን የተናገሩት ማናጀሩ፣ እነዚህ የትምህርት ዘርፎች እነሱም የሚጠቀሙባቸው እንደሆነ ገልፀዋል፡፡ ለ30ዎቹ ተማሪዎች በዓመት ከ400 እስከ 500 ሺህ ብር ወጪ ይደረጋል፡፡ኩባንያው የማህበራዊ አገልግሎት ተሳትፎን ለማጎልበት በጤና፣ በመጠጥ ውሃ፣ በስፖርት… ዘርፎች እየተሳተፈ እንደሆነ የጠቀሱት አቶ አንተነህ፤አሁን በትምህርት ዘርፍ የጀመሩት ተሳትፎ የአነስተኛ ገቢ ቤተሰብ ተማሪዎች፣ከፍተኛ ውጤት እያላቸው በገንዘብ ችግር ትምህርታቸውን እንዳይደናቀፍና ውጤታቸው እንዳይቀንስ በማለት መሆኑን ተናግረዋል፡፡

አቶ አንተነህ፣ ይህ የኩባንያው እቅድ የሚሳካው በተማሪዎቹ፣ በዩኒቨርሲቲዎቹና በህብረተሰቡ ተሳትፎ እንደሆነ ገልጸው፣ ተማሪዎቹ ትምህርታቸውን በአግባቡ እንዲከታተሉ አሳስበዋል፡፡ ባህሪያቸው ያማረና በአዲስ አበባና በድሬዳዋ ፋብሪካዎች ለሶስት ዓመት በሚያደርጉት የተግባር ልምምድ የሚሰጠውን ፈተና በሚገባ የሚያልፉት በኩባንያው እንደሚቀጠሩ አስታውቀዋል፡፡ ቅድስት ታደለና ቤዛዊት ዚያድ አነስተኛ ገቢ ያላቸው የኩባንያው ሰራተኞች ልጆች ናቸው፡፡ ቅድስት በደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ የ2ኛ ዓመት የኮምፒዩተር ሳይንስ፣ ቤዛዊት በአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሜካኒካል ኢንጂነሪንግ የ2ኛ ዓመት፣ ማተቡ ወርቁ ደግሞ በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የ2ኛ ዓመት ኤሌክትሪካል ኢንጂነሪንግ ተማሪ ነው፡፡ ተማሪዎቹ ይህን ዕድል በማግኘታቸው መደሰታቸውን ገልጸዋል፡፡ ዕድሉን ባያገኙ ኖሮ ለተግባር ልምምድ (አፓረንትሽፕ) የሚወጡት 4ኛ ዓመት ሲደርሱ እንደነበር ጠቅሰው፣ አሁን ግን ሶስት ዓመት የሚያደርጉት ልምምድ፤ ለእውቀታቸው መዳበርና ለውጤታቸው ማማር በእጅጉ እንደሚረዳቸው ተናግረዋል፡፡

ኢትዮጵያ ችግሩ ከተስፋፋባቸው አገራት አንዷ ናት ተብሏል

          የአለማችን ህዝብ በአሁኑ ወቅት ከሚያስፈልገው የምግብ እህል ከሁለት እጥፍ በላይ ማምረት ቢቻልም፣ አሁንም ድረስ በተለያዩ የአለም አገራት የሚገኙ ከ800 ሚሊዮን በላይ ሰዎች በቂ ምግብ እንደማያገኙ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አስታወቀ፡፡ባለፉት አስርት አመታት በአለማችን የርሃብ ችግር በተወሰነ መልኩ ቢቀንስም ባለፉት ሁለት አመታት 11 ነጥብ 3 በመቶ የሚሆነው የአለማችን ህዝብ የምግብ እጥረት ተጠቂ እንደነበረ የጠቆመው ዘገባው፣ የምግብ እጥረቱ በከፍተኛ ሁኔታ ከሚታይባቸው አገራት መካከልም፣ ቻድ፣ መካከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ እና ኢትዮጵያ እንደሚገኙበት ገልጿ ል፡፡ በቂ ምግብ የማያገኙ በርካታ ዜጎች ካሏቸው አገራት አንዷ በሆነችው ኢራቅ፤ ከአራት ኢራቃውያን አንዱ የምግብ እጥረት ችግር ሰለባ መሆኑንም፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በሳምንቱ መጀመሪያ ያወጣውን መረጃ በመጥቀስ ዘገባው ጠቁሟል ፡፡

የአለም የምግብና የእርሻ ድርጅት እንዳለው፣ ምንም እንኳን በአለማችን በአሁኑ ወቅት ከሚያስፈልገው የምግብ እህል ከሁለት እጥፍ በላይ ማምረት ቢቻልም፣ ምርቱን ለተመጋቢዎች በማድረስ ረገድ ክፍተቶች በመኖራቸው የምግብ እጥረት ችግሩ ሊቀረፍ አልቻለም፡፡ ምርታማነት ቢያድግም የተመረተውን የምግብ እህል ለሸማቾችና የችግር ተጋላጭ ለሆኑ የማህበረሰብ ክፍሎች ማድረስ ካልተቻለ፣ የምግብ እጥረቱ እንደማይቀረፍ የገለጸው ድርጅቱ፣ ለዚህም ሴፍቲ ኔትና ሌሎች የማህበራዊ ዋስትና አሰራሮችን ማጠናከር እንደሚገባ አስታውቋል፡፡

ከሚሊኒየሙ የልማት ግቦች አንዱ በታዳጊ አገራት የምግብ እጥረት የሚያጋጥማቸውን ዜጎች ቁጥር እስከ 2015 ድረስ በግማሽ መቀነስ መሆኑን ያስታወሰው ዘገባው፤ የተመድ ሪፖርትም ግቡን ለማሳካት እንደሚቻል አመላካች ውጤቶች እየተመዘገቡ እንደሚገኙ ማስታወቁን ጠቁሟል፡፡ ይሄም ሆኖ ግን፣ ከሰሃራ በታች በሚገኙ አገራትና በመካከለኛው ምስራቅ የሚከሰቱ Yተፈጥሮ አደጋዎችና ግጭቶች፣ የአካባቢው አገራት ግቡን ለማሳካት የሚደርጉትን እንቅስቃሴ እያደናቀፉት እንደሚገኙ ሪፖርቱ አመልክቷል፡፡

            ከ500 ሚ. በላይ ኮምፒውተሮችን ሊያጠቃ ይችላል

           በአለም ዙሪያ የሚገኙ ከ500 ሚሊዮን በላይ ኮምፒውተሮችንና ሰርቨሮችን ሊያጠቃ እንደሚችል የተነገረለት ‘ሼልሾክ’ የተባለ እጅግ አደገኛ የኮምፒውተር ቫይረስ ከሰሞኑ እየተሰራጨ እንደሚገኝ ቢቢሲ ዘገበ፡፡ የኮምፒውተር ባለሙያዎችን ጠቅሶ ዘገባው እንዳለው፣ ይህ አዲስ አይነት አደገኛ ቫይረስ ባሽ ተብሎ በሚጠራውና በበርካታ የሌኑክስና ማክ ኦፕሬቲንግ ሲስተሞች ውስጥ በሚገኘው የሶፍትዌር አካል ላይ ላይ ተሰራጭቶ Yተገኘ ሲሆን፣ ማንኛውንም አይነት ሲስተም በርቀት ሆኖ ለመቆጣጠር የሚያስችል ነው፡፡

በሱሬይ ዩኒቨርሲቲ የደህንነት ተመራማሪ የሆኑት ፕሮፌሰር አለን ውድዋርድ ለቢቢሲ እንደተናገሩት፣ አዲሱ ቫይረስ ባለፈው ሚያዝያ ወር ላይ ተከስቶ ከነበረው ኸርትብሊድ የተባለ ቫይረስ በእጅጉ የከፋ እና ማንኛውንም የኮምፒውተር ሲስተም ሊቆጣጠር የሚችል ነው፡፡የአሜሪካ የኮምፒውተር አደጋ ዝግጁነት ቡድን፣ ከሰሞኑ የተከሰተውንና በርካታ ድረ ገጾችን ሊያጠቃ እንደሚችል የተነገረለትን ይህን አደገኛ ቫይረስ በተመለከተ ለተጠቃሚዎች አፋጣኝ የማስጠንቀቂያ መልዕክት ያስተላለፈ ሲሆን፣ ከቫይረሱ ጥቃት ሊታደጋቸው የሚችለውን ተገቢ ጥንቃቄ እንዲያደርጉም መክሯል፡፡ የኢንተርኔት ወንጀለኞች ቫይረሱ የሚፈጥረውን ቀውስ በመጠቀም ኦፕሬቲንግ ሲስተሞችን ሊቆጣጠሩ፣ የሚስጥር መረጃዎችን ሊያገኙ፣ በመረጃዎቹ ላይ ለውጥ ሊፈጥሩና ሌሎች የወንጀል ድርጊቶችን ሊፈጽሙ እንደሚችሉም ባለሙያዎች ስጋታቸውን እየገለጹ ይገኛሉ፡፡

            አሜሪካ በድብቅ የያዘቻቸውን 1 ነጥብ 7 ሚሊዮን ያህል የብሄራዊ ደህንነት ሚስጥሮችና የተለያዩ ድብቅ መረጃዎችን በማውጣት ለአለም ይፋ ያደረገውና በአገሪቱ መንግስት ክስ የተመሰረተበት ኤድዋርድ ስኖውደን፣ ለፕሬስ ነጻነት ባበረከተው አስተዋጽኦ፣ አማራጭ የኖቤል ሽልማት በመባል የሚታወቀው ‘የስዊድን ራይት ላይቭሊሁድ ኦኖራሪ አዋርድ’ ተሸላሚ መሆኑን ሮይተርስ ዘገበ፡፡ ‘ራይት ላይቭሊሁድ ኦኖራሪ አዋርድ ፋውንዴሽን’ ስኖውደን የአሜሪካ መንግስት የዲሞክራሲያዊ ስርአት ሂደቶችንና ህገ መንግስታዊ መብቶችን በሚጥስ መልኩ የምታከናውነውን የመረጃ ክትትል ለማጋለጥ ባደረገው ጥረት ለሽልማቱ መመረጡን አስታውቋል፡፡ ተቋሙ ሽልማቱን ለስኖውደን ከማበርከቱ በተጨማሪም፣ በቀጣይ ከአሜሪካ መንግስት ለሚገጥመው የወንጀል ክስ ህጋዊ ድጋፍ እንደሚያደርግ አስታውቋል፡፡

የመንግስት ንብረትን መዝረፍ፣ ብሄራዊ የመከላከያ መረጃዎችን በህገወጥ መንገድ ማሰራጨትና የስለላ መረጃዎችን ለማይገባቸው ሰዎች አሳልፎ መስጠት የሚሉ ክሶች ባለፈው አመት በአሜሪካ መንግስት የተመሰረተበት ስኖውደን፤ በዚያው አመት ከአሜሪካ ወጥቶ ወደ ሆንግ ኮንግ፣ ከዚያም ወደ ሩስያ አቅንቷል፡፡ በአሁኑ ወቅትም ከሩስያ መንግስት በተሰጠው ለሶስት አመታት የሚቆይ ጊዜያዊ የመኖሪያ ፍቃድ በሞስኮ ይገኛል፡፡ በዘንድሮው ‘የስዊድን ራይት ላይ ቭሊሁድ ኦኖራሪ አዋርድ’፣ስኖውደን ያወጣቸውን መረጃዎች ለህትመት በማብቃት ትብብር ያደረጉት የታዋቂው ዘ ጋርዲያን ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ አለን ራስብሪጀርም ተሸላሚ እንደሆኑ ዘገባው አስረድቷል፡፡

            አለም በቴክኖሎጂ እየረቀቀች ነው፣ የህትመት ኢንዱስትሪውም እጅግ እየዘመነ ነው በሚባልበት በ‘ዘመነ - ኮምፒውተር’፣ ታዋቂው ጋዜጣ ‘ዘ ታይምስ’ 30 አመታትን ወደ ኋላ ተመልሶ ፊቱን ወደ ታይፕ ራይተር ማዞሩን ዘ ኢንዲፔንደንት ዘገበ፡፡ ዘ ታይምስ ጋዜጠኞቹን ለማነቃቃትና በሙሉ ሃይላቸው ሰርተው ዜናዎቻቸውን በተቀመጠላቸው የጊዜ ገደብ እንዲያስረክቡ ለማስቻል ሲል ነው፣ የጋዜጦች ዝግጅት ክፍሎች በዘመናዊ ኮምፒውተሮች ታግዘው በሚሰሩበት በዚህ ዘመን፣ ዘመኑ ያለፈበት የጽህፈት መሳሪያ ወደሚባለው ታይፕ ራይተር ፊቱን ያዞረው፡፡ዘ ኢንዲፔንደንት እንዳስነበበው፣ የጋዜጣው የስራ ሃላፊዎች በዜና ዝግጅት ክፍሉ ውስጥ ግዙፍ የድምጽ ማጉያ ተክለዋል፡፡

ይህ የድምጽ ማጉያ የታይፕ ራይተር ድምጽ የሚያወጣ ሲሆን፣ ድምጹ እየፈጠነ የሚሄድና ጋዜጠኞችን የሚያነቃቃ ነው ተብሏል፡፡ ድንገት በዝግጅት ክፍሉ ውስጥ ተገትሮ ባገኙት የድምጽ ማጉያ ግራ የተጋቡ ጋዜጠኞች እንደነበሩና ከመካከላቸው አንዱም፣ በሚያደምጠው የታይፕ ራይተር ድምጽ በመረበሽ ድምጽ ማጉያውን ለመዝጋት መሞከሩን ዘገባው ገልፃል፡፡ የጋዜጣው የቀድሞ ባልደረባ የነበሩትና በአሁኑ ወቅት ለንደን በሚገኘው ሲቲ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነት መምህር የሆኑት ጆርጅ ብሮክ፣ ዝግጅት ክፍሉ ታይፕ ራይተሮችን መጠቀም ያቆመው እ.ኤ.አ በ1980 ዎቹ እንደነበር አስታውሰው፣ የአሁኑ የታይፕ ራይተር ድምጽ እርግጥም እንደታሰበው ጋዜጠኞችን ለስራ የሚያተጋ መሆንና አለመሆኑን ለመገመት እንደሚያዳግታቸው ገልጸዋል፡፡ የጋዜጣው የዲጂታል ክፍል ምክትል ሃላፊ ሉሲያ አዳምስ በበኩላቸው፣ ነገርዬው አስቂኝ ነው፤ ታይፕ ራይተር ጊዜው ያለፈበት ቢመስልም፣ ቴክኖሎጂ ነውና ሊዘነጋ አይገባም ብለዋል፡፡

(አዋቄ ሞሽሪያ ተ እቸሹ እራሻ መቾ ገውሱ) - የወላይታ ተረት

አንዳንድ ተረቶች በአንድ ወቅት አልደመጥ ሲሉ በሌላ ወቅት ተደግመው መነገራቸው ግድ ይሆናል፡፡

የሚከተለውም እንደዚያው ነው፡፡
ከዕለታት አንድ ቀን ሶስት አህዮች በጠፍ ጨረቃ ሰፊ መስክ ላይ እየጋጡ ሳሉ፤ ሶስት ጅቦች የሚበላ ፍለጋ

ሲዘዋወሩ ያገኙዋቸዋል፡፡
ጅቦቹ ገርሟቸዋል፡፡
አንደኛው ጅብ፤
“እነዚህ አህዮች እንዴት ቢጠግቡ ነው በእኛ ሰዓት፣ በእኛ ግዛት እንደዚህ ተዝናንተው የሚግጡት?”
ሁለተኛው ጅብ
“ዕውነትም የሚገርም ነው፡፡ የተማመኑት ነገር ቢኖር ነው እንጂ እንዲህ ያለ ድፍረት አይፈጽሙም ነበር”
ሦስተኛው ጅብ
“ታዲያ ለምን ችሎት ተቀምጠን አንፈርድባቸውም?” ሲል ሃሳብ አቀረበ፡፡
አህዮቹን ከበቡና ተራ በተራ ሊጠይቋቸው ተሰየሙ፡፡
የመጀመሪያዋን አህያ ጠሩና ጠየቋት፡፡ የማህል ዳኛው ነው የሚጠይቃት፡፡
“እሜቴ አህያ፤ ለመሆኑ በእኛ ሰዓት፣ በእኛ ግዛት፣ በጠፍ ጨረቃ፣ እንዲህ ዘና ብለሽ የምትግጪው ማንን

ተማምነሽ ነው?”
እሜቴ አህያም፤
“አምላኬን፣ ፈጣሪዬን፣ ተማምኜ ነው፡፡ በእኔ ላይ ግፍ የሚሠራን አምላኬ ዝም አይለውም፡፡ መዓት

ያወርድበታል፡፡”
የማህል ጃኛው ጅብም፤
“መልካም ሂጂ፡፡ ፍርድሽን ትሰሚያለሽ፡፡ ሌላዋን ጥሪያት”
ለሁለተኛዋ አህያም ጥያቄው ቀረበላት:-
“አንቺስ ማንን ተማምነሽ ነው በጠፍ ጨረቃ፣ በእኛ ሰዓት፣ በእኛ ግዛት
ፍንጥዝጥዝ ብለሽ የምትግጪው?”
ሁለተኛይቱ አህያም፤
“ጌታዬን፣ አሳዳሪዬን ተማምኜ ነው፡፡ በእኔ ላይ ጥቃት የሚያደርስን ማንንም ቢሆን ጌታዬ ዝም አይለውም፡፡

ይበቀልልኛል ብዬ በማመን ነው” ስትል መለሰች፡፡
ማህል ዳኛው ጅብ፤
“መልካም፡፡ አንቺም ፍርድሽን ትሰሚያለሽ፡፡ ሌላዋን ጥሪያት” አላት፡፡
ሦስተኛይቱ ቀረበች፡፡
ማህል ዳኛው ጅብም፤
“አንቺስ ማንን ተማምነሽ ነው ይሄ ሁሉ መዝናናት?” አላት
ሦስተኛይቱ አህያም፤
“እናንተን፣ እናንተን፣ የአካባቢውን ገዢዎች ተማምኜ ነው ጌቶቼ”
ዳኛውም፤
“መልካም፡፡ ሁላችሁም ፍርዳችሁን ጠብቁ” አሉና ሸኟት፡፡
ዳኞቹ መምከር ጀመሩ፡፡
ግራ ቀኝ ዳኞች አስተያየት ከሰጡ በኋላ፤ የመካከል ዳኛው ጅብ እንዲህ አሉ :-
“የመጀመሪያዋን ብንበላት እንዳለችው አምላክ አይለቀንም፡፡ ይበቀልላታል፡፡ ሁለተኛዋን ብንበላት ምናልባት

አሳዳሪ ጌታዋ ተከታትሎ፣ ያጠፋናል፡፡ ይቺን ሶስተኛዋን፣ እኛን የተማመነችውን ብንበላት ማናባቱ ይጠይቀናል?”

ሲል መሪ - ሀሳብ አቀረበ፡፡
ሁለቱ ጅቦች ባንድ ድምጽ፤
“ዕውነት ነው፡፡ እኛን የተማመነችውን እንብላት!” አሉ፡፡
እነሱን የተማመነችው ላይ ሰፈሩባት፡፡
***
የጌቶች አስተሳሰብ ምን እንደሚመስል ተገዢ ወዳጆች ማወቅ አለባቸው፡፡ ሎሌነቱንም በቅጥ በቅጥ አለመያዝ፣

የመጨረሻውን ቀን ከማፋጠን አያልፍም፡፡ “የምጣዱ እያለ የእንቅቡ ተንጣጣ የሚለውን ተረት፤ በአፉ የሚንጣጣ

ሁሉ በጊዜ ሊገነዘብ ይገባል፡፡ መጨረሻው፤ “ያመኑት ፈረስ፣ ይጥል በደንደስ” ነውና፡፡ “እናቴን ያገባ ሁሉም

አባቴ ነው” ለሚሉ የዋሀን ሁልጊዜ ፋሲካ ሊመስላቸው ቢችልም፤ ለሁሉም ጊዜ አለውና “ምነው ምላሴን

በቆረጠው” የሚያሰኝ የፍርድ ቀን እንደሚኖር አሌ አይባልም፡፡
“እንብላም ካላችሁ እንብላ፤ አንብላም ካላችሁ እንብላ” በሚል ጅባማ ፍልስፍና ውስጥ መበላላት መሪ መርሀ -

ግብር መሆኑን ለአፍታም መዘንጋት የለበትም፡፡
“ለጋማማ አህያም ጋማ አላት
አያስጥልም እንጂ ጅብ ሲዘነጥላት” ሲባል የከረመው ያለ ነገር አይደለም፡፡
“እነሆ ብዙ ዘመን አለፍን፡፡ ከሁሉም የተረፈን ብዙ ምላሶችና እጅግ ጥቂት ልቦች ናቸው” ይላል ሲ ጆርጅ

የተባለ ፀሐፊ፡፡ በሀገራችን በቅንነት ሃሳብ የሚሰጡና በሎሌነት ሃሳብ የሚሰጡ መለየት አለባቸው፡፡ “ውሸት

አለምን ዞሮ ሊጨርስ ሲቃረብ ዕውነት ገና ቦት ጫማውን እያጠለቀ ነው” መባሉ በምክን እንጂ በአቦ - ሰጡኝ

አይደለም፡፡ በየአገሩ፤ የንጉሥ አጫዋቾች የተለያዩ ናቸው፡፡ አንድ የጋራ ባህሪ ግን አላቸው - ንጉሱ ሲያስነጥሱ

ማስነጠስ፡፡ አድር ባይነት፡፡ በመካያው ራሱ አድርባዩ ማንነቱ ይጠፋበትና “የዘሬን ብለቅ ያንዘርዝረኝ” ማለት

እንኳን ይሳነዋል፡፡ “ነገር አንጓች፤ እንኳን ለጌታው ለራሱም አይመች” ነውና ፍፃሜው አጓጉል መሆኑ ዕሙን

ነው፡፡
የትዕዛዝ ሁሉ ጉልላት ለህሊና መታዘዝ ነው፡፡ ማንም ቢሆን ማን፤ ህሊናውን ሲክድ
አታላይ መሆኑ አይቀሬ ነው፡፡ ብልጥ ለማኝ፤ “ጌታዬ ጌታዬ አምና የሰጡኝን ልብስ አምስት ዓመት ለበስኩት”

እያለ ይኖራል፡፡ በዕውቀት ያልተደገፈ ድፍረት፣ የህሊና ማጣት ምርኩዝ ነው፡፡” ወትሮም፤ “መራዡ ተኳሹ” ሲል

የኖረ፣ “በራዡ ከላሹ” ማለት ከጀመረ ሁለተዜ ጥፋት ነው፡፡ ሀገራችን አያሌ አድር - ባይ አይታለች፡፡ ለሀገራችን

ጐታቿም አጥፊዋም፣ “አሾክሿኪው” ነው፡፡ ከታሪክ መማር ዕርም በሆነባት አገር ቀለሙን እየለዋወጠ አድር -

ባይ ሁሉ እየመጣ፤ “እንቅፋት በመታው ቁጥር ቲዎሪ ድረሽ” (ያውም ዕውነተኛ ቲዎሪ ካለው) እያለ፤ “መንገድ

ባስቸገረው ቁጥር” መመሪያ ማሪኝ” እያለ ህሊናውን እየሸጠ ይኖራል፡፡ ልባም አይደለምና አፍ ያወጣል፡፡ ምላሱ

እየረዘመ፣ አንጐሉ እየጨለመ ይሄዳል፡፡ አበው “ከመሃይም ምላስ ይሰውረን” የሚሉት ለዚህ ነው፡፡ ማህታማ

ጋንዲ እንግሊዝን “በመጨረሻ ባዶህን ትወጣታለህ!” ማለቱን አንርሳ፡፡
“ቅዳሴው ሲያልቅበት ቀረርቶ አከለበት” እንዲሉ በምላሱ የሚተዳደር ሰው ውሸት ማብዛቱ ግዱ ነው፡፡ ዕውቀተ

- ቢስ መሠረቱ ለዕውነት ረሃብ ያጋልጠዋልና! “አፈኛ ሴት፤ የአምስት ዳኛ ሚስት ነኝ፤ ትላለች” የሚለው

የወላይታ ተረት ኢላማ ይሆናል!!
መልካም የመስቀል በዓል!

 “የደሞዝ ጭማሪው ለሌላው ሲደርስ ለጋዜጠኛው አልደረሰም” ጋዜጠኞች

“ጭማሪው ሰሞኑን በቦርዱ ተወስኗል፤ በቀጣዩ ወር ይደርሳቸዋል” አቶ ሽመልስ ከማል

 

“ድርጅቱ በደመነፍስ ይመራል የሚለው አጉል አሉባልታ ነው” የፕሬስ ድርጅት ሥ/አስኪያጅ

በኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ስር የሚታተሙት አዲስ ዘመን፣ ኢትዮጵያን ሄራልድ፣ በሪሳ እና አል-አለም ጋዜጠኞች በመስሪያቤታቸው የመልካም አስተዳደር እጦት እየተማረሩ መሆኑን ገለፁ፡፡ መንግስት በድርጅቱ ውስጥ ያለውን ዘርፈ ብዙ ችግር እያወቀ ምላሽ አለመስጠቱ እንዳሳዘናቸው ጋዜጠኞቹ ተናግረዋል፡፡ ሌላው ቀርቶ ለመንግስት ሰራተኞች የተደረገው የደሞዝ ጭማሪ ለጋዜጠኞች አለመድረሱን የገለፁት ሰራተኞቹ፤ ላለፉት አራት ዓመታት የቦርድ ሰብሳቢ ሆነው እያገለገሉ ያሉት አቶ ሽመልስ ከማል አንድም ቀን ሰብስበው አወያይተዋቸው እንደማያውቁ በምሬት ገልፀዋል፡፡

“ድርጅቱ በዚህ ዓመት ይህን እሰራለሁ ብሎ ያስቀመጠው ግብ የለም፣ ጋዜጠኛው የሚመራው ብቃት በሌለው ስራ አስኪያጅ ነው፣ ይህንንም በስብሰባ ለራሳቸው ለስራ አስኪያጁ ተናግረን ችግሩን የሚያጣራ ኮሚቴ ተቋቁሞ ያጣራውን ለሚመለከተው አካል ቢያቀርብም የተሰጠ ምላሽ የለም” ብለዋል - ጋዜጠኞቹ፡፡ የቦርዱ ሰብሳቢ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ሚኒስቴር ዴኤታ አቶ ሽመልስ ከማል በበኩላቸው፤ አንድም ቀን አወያይቶን አያውቅም የሚለው ፍፁም ሀሰትና የተሳሳተ መረጃ መሆኑን ገልጸው፣ በየጊዜው ከጋዜጠኞችና ከኤዲተሮች ጋር እንደሚወያዩና በኤዲተሮችና ዋና አዘጋጆች ፎረም ላይ የተለያዩ ሃሳቦች እየተነሱ በምክክር እንደሚሰሩ ተናግረዋል፡፡

“ከሰራተኛው መካከል የራሳቸው ጥቃቅን የጥቅም ግጭት ያላቸው አንዳንድ ግለሰቦች የሚነዙት አሉባልታ እንደ አጠቃላይ የሰራተኛው ችግር ተደርጎ መነሳቱ መሰረተ ቢስ ነው” ብለዋል - አቶ ሽመልስ፡፡ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ሰብስቤ ከበደን በጉዳዩ ዙሪያ አነጋግረናቸው በሰጡት ምላሽ “ድርጅቱ በእቅድና በፕሮግራም እንደሚመራ በቢሮ ተገኝቶ አሰራሩን ማረጋገጥ ይቻላል” ያሉ ሲሆን፣ አንዳንድ የግል ችግር ያለባቸው ግለሰቦች የድርጅቱንና የአመራሩን ስም ለማጥፋት ሆን ብለው የሚነዙት ተጨባጭ ያልሆነ ወሬ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ ድርጅቱ ችግር ቢኖርበት ኖሮ ሰራተኛውን የሚያወያይበት የስብሰባ መድረክ እያዘጋጀ አያወያይም ነበር” ያሉት ሥራ አስኪያጁ፤ በቅርቡ አጠቃላይ ስብሰባ ተጠርቶ ከሰራተኞች የተለያዩ አስተያየቶች መሰጠታቸውንና በውይይት መድረኩ ላይ የተነሱትን አንዳንድ ክፍተቶች እንደግብአት በመጠቀም የአሰራር ማስተካከያ እየተደረገ እንደሆነ ለአዲስ አድማስ ገልፀዋል፡፡

ጋዜጠኞቹ በበኩላቸው ለመልካም አስተዳደር እጦቱ እንደዋና ማሳያ ያቀረቡት የድርጅቱ ህንፃ በሁለት ዓመት ተገንብቶ ይጠናቀቃል ቢባልም አራት አመት ፈጅቶ እንኳን አሁንም ይቀረዋል፣ የሰራተኛ የቅጥር ሁኔታው ግልፅነት የለውም፣ ሹፌር ሳይቀር በፍሪላንስ የሚቀጠርበት ሁኔታ አለ፣ የደሞዝ ጭማሪና የእድገት ሁኔታ በአድሎአዊ አሰራር የተተበተበ ነው፤ በዚህም የተነሳ ለጋዜጦቹ አለኝታ የሚባሉ ወደ 50 ሰራተኞች ባለፈው ዓመት ለቀዋል፤ ዘንድሮም የለቀቁ አሉ በማለት ተናግረዋል፡፡ መንግስት ይህን ሁሉ ችግር ያውቃል፤ ግን ማስተካከያ አልተደረገም ብለዋል፡፡ ፕሬስ ውስጥ በሲቪል ሰርቪስና በቦርድ የሚተዳደር ሁለት ዓይነት ሰራተኛ መኖሩን ጋዜጠኞቹ ገልጸው፣ በሲቪል ሰርቪስ የሚመራው ሰራተኛ ጭማሪው ሲደርሰው የእኛ ዘግይቷል ብለዋል፡፡

“በአንድ ወቅት ከኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ድርጅት ጋዜጠኞች ደሞዝ የፕሬሱ ጋዜጠኞች ይበልጥ ነበር” ያለው አንድ ቅሬታ አቅራቢ ጋዜጠኛ፤ ኢዜአዎች ፕሬስ አቻ ድርጅት ሆኖ እንዴት ደሞዝ ይበልጡናል በሚል ላነሱት ጥያቄ በአፋጣኝ ምላሽ ተሰጥቷቸው ደሞዛቸው መስተካከሉን አስታውሶ፤ የእኛ አቻ ድርጅት በሆነው የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (EBC) በቅርቡ እስከ 200 ፐርሰንት የደሞዝ ጭማሪ ቢደረግም በእኛ ድርጅት ምንም የተባለ ነገር ባለመኖሩ ጋዜጠኛው በድርጅቱ ተስፋ እየቆረጠ ነው ብሏል፡፡ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ስራ አስኪያጅ ጭማሪውን በተመለከተ በሰጡት ምላሽ፤ በሲቪል ሰርቪስ የሚተዳደሩት የሚከፈላቸው በመንግስት በመሆኑ እንደማንኛውም የመንግስት ሰራተኛ ጭማሪው ቀድሞ እንደረሳቸው አምነው፣ ሆኖም በቦርድ ለሚተዳደሩት ጋዜጠኞች የሚከፈለው ድርጅቱ ከማስታወቂያና ከጋዜጣ ሽያጭ ከሚያገኘው ገቢ ላይ በመሆኑና ስኬሉ ስለሚለያይ ቦርዱ ተወያይቶ ውሳኔ እስኪሰጥበት ሲጠበቅ እንደነበር አብራርተዋል፡፡ “ውይይቱ ተጠናቅቆ ቦርዱ ከትላንት በስቲያ ስለወሰነላቸው ጭማሪው በቀጣዩ ወር ይደርሳቸዋል” ብለዋል - ሥራ አስኪያጁ፡፡

በስብሰባው ላይ የአመራር ብቃት የለዎትም፤ ቦታውን ይልቀቁ በሚል ከጋዜጠኞች ቅሬታ ስለመቅረቡ አቶ ሰብስቤን ጠይቀናቸው፤ “እኔ ስብሰባ ላይ እንዲህ የሚባል ትችት አልቀረበብኝም” ያሉት አቶ ሰብስቤ፤ እርግጥ በስነ-ምግባርም ሆነ በእውቀት ብቃት የሌለው አንድ ጋዜጠኛ “ቦታውን ልቀቅ” ብሎ በግል ተናግሮኛል፤ ጋዜጠኛው አሁን ስራ ለቋል” ብለዋል፡፡ ብዙ ጋዜጠኞች ከድርጅቱ ይለቃሉ ስለሚባለው አንስተንባቸው በሰጡት ምላሽ፤ “ከጥቅማጥቅም ጋር በተያያዘ ጋዜጠኞች ይለቃሉ፣ የተሻለ ደሞዝ ሲያገኙ የትኛውም መ/ቤት እንደሚልቁት ሁሉ እዚህም ይለቃሉ፤ በዚያው ልክ እኛም እንቀጥራለን” ብለዋል፡፡ ሰራተኞቹ፤ የመልካም አስተዳደር ችግሩ በአስቸኳይ ካልተቀረፈ፣ እንደአቻ ድርጅት ማግኘት የሚገባንን የደሞዝ እድገት ካላገኘንና አድሎአዊ አሰራር ካልቀረ ድርጅቱን ለመልቀቅ እንገደዳለን ሲሉ አሳስበዋል፡፡ ዋና ሥራ አስኪያጁ በበኩላቸው፤ በድርጅቱ ውስጥ መሻሻሎችን ለመፍጠርና ወደ ኮርፖሬት አደረጃጀት ለመቀየር ስራዎች ተሰርተው በመጠናቀቅ ላይ ናቸው ብለዋል፡፡

              የአፍሪካ የጋዜጠኞች ፌዴሬሽን የኢትዮጵያ መንግስት በእስር ላይ የሚገኙ ጋዜጠኞችን እንዲፈታና በቅርቡ አገራቸውን ጥለው የተሰደዱ ጋዜጠኞችም፣ ወደ አገር ቤት ተመልሰው ስራቸውን የሚቀጥሉበትን ምቹ ሁኔታ እንዲፈጥር ጠየቀ፡፡ አለማቀፉ የጋዜጠኞች ፌዴሬሽን ባለፈው ረቡዕ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ፤ በኢትዮጵያ የሚታየው የፕሬስ ነጻነት ጥሰት፣ የጋዜጠኞች እስርና ስደት ያሳስበኛል ብሏል፡፡ “በኢትዮጵያ የፕሬስ ነጻነትን የሚጥሱ ተግባራት መከናወናቸው መቀጠሉ እንዲሁም የሚታሰሩና አገር ጥለው የሚሰደዱ ጋዜጠኞች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱ ያሳስበናል” ያሉት የአፍሪካ የጋዜጠኞች ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ሞሃመድ ጋርባ፤ የኢትዮጵያ መንግስት ከመገኛኛ ብዙሃን ጋር ሃቀኛ ውይይትና ምክክር በማድረግ፣ ራሳቸውን ተቆጣጥረው በአግባቡ እንዲንቀሳቀሱ ምቹ ሁኔታዎችን እንዲፈጥር ጥያቄ ማቅረባቸውን ገልጸዋል፡፡በኢትዮጵያ ብሄራዊ ጋዜጠኞች ህብረትና በምስራቅ አፍሪካ የጋዜጠኞች ማህበር አዘጋጅነት በቅርቡ በአዲስ አበባ በተካሄደው የምርመራ ጋዜጠኝነት አውደ-ጥናት ላይ የተሳተፈውና ከምስራቅ አፍሪካ የጋዜጠኞች ማህበርና ከአለማቀፉ የጋዜጠኞች ፌዴሬሽን የተወከሉ 3 አባላት ያሉት የልኡካን ቡድን፣ ከመንግስት የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ሚኒስትር አቶ ሬድዋን ሁሴን ጋር በጉዳዩ ዙሪያ መምከሩንም የፌዴሬሽኑ መግለጫ አስታውሷል፡፡

ከአካባቢው አገራት በበለጠ ሁኔታ ጋዜጠኞች የሚታሰሩትና የሚሰደዱት በኢትዮጵያና በኤርትራ እንደሆነ ለሚኒስትሩ የገለጹት የልኡካን ቡድኑ አባላት፣ የኢትዮጵያ መንግስት በእስር ላይ የሚገኙትን ሁሉንም ጋዜጠኞች እንዲፈታና በስደት የሚገኙትም ወደአገራቸው የሚመለሱበትን ሁኔታ እንዲያመቻች መጠየቃቸውን ጠቁሟል፡፡ አቶ ሬድዋን በበኩላቸው ለልኡካን ቡድኑ በሰጡት ምላሽ፣ በቅርቡ አገር ጥለው የተሰደዱት ጋዜጠኞች ክስ እንዳልተመሰረተባቸውና ከአገር የሚያስወጣቸው ምክንያት እንደሌለ ፤ የአገሪቱ መንግስትም ሃሳብን የመግለጽ ነጻነትን ለማስከበር ቁርጠኛ አቋም ይዞ እየሰራ እንደሚገኝ መናገራቸውን መግለጫው አመልክቷል፡፡ የአፍሪካ የጋዜጠኞች ፌዴሬሽን በ40 የአህጉሪቱ አገራት ውስጥ የሚገኙ ከ50ሺህ በላይ ጋዜጠኞችን እንደሚወክል፣ አለማቀፉ የጋዜጠኞች ፌዴሬሽን ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡

      ሆቴሉ የብድርና የኮንትራት ማናጅመንት ስምምነቶችን ነገ ይፈራረማል

ግንባታው ከ18 ወራት በኋላ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ይጀምራል የተባለው የአለማቀፉ ኢንተርኮንቲኔንታል ግሩፕስ አካል የሆነው “ክራውን ፕላዛ ሆቴል”፤ በአዲስ አበባ በአገልግሎት ላይ ከሚገኘው “ክራውን ሆቴል” የስያሜ ኮፒ ራይት መብት ጥያቄ ቀርቦበት ፍ/ቤት የንግድ ስያሜ እግድ አስተላልፎበታል፡፡ “ክራውን” የሚለው ስያሜ በኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ፅ/ቤት የተመዘገበና በስራ ላይ የሚገኝ እንደሆነ የጠቆመው “ክራውን ሆቴል”፤ ስያሜው ለሌላ አካል መሰጠቱ ተገቢ አይደለም ሲሉ ለፍ/ቤቱ ይግባኝ ብሏል፡፡ “ክራውን ሆቴል” የሚለው የንግድ ምልክት በኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ፅ/ቤት ተመዝግቦ አገልግሎት መስጠት ከጀመረ ከ20 አመታት በላይ አስቆጥሯል የሚለው ለይግባኝ ሰሚ ፍ/ብሔር ችሎት የቀረበው የሆቴሉ ማመልከቻ፤ ውሳኔው “ክራውን ሆቴል” በሁለት አስርት ዓመታት ያገኘውን ስምና ዝና እንዲሁም ገበያውን አዲሱ ሆቴል እንዲሻማበት የሚያደርግ ነው ብሏል፡፡

የኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ጽ/ቤት “ክራውን ሆቴልን” ሳያማክር ሚያዚያ 28 ቀን 2006 ዓ.ም የዓለም አቀፍ ኢንተርኮንቲኔንታል ፕሩፕስ አካል ሆነው ሆቴል “ክራውን ፕላዛ” የሚለውን ስያሜ መፍቀዱ አግባብ አይደለም ሲል ይግባኝ የጠየቀው ክራውን ሆቴል፤ ፍ/ቤቱ አዕምሯዊ ንብረት ፅ/ቤት የሰጠው ውሳኔ የይግባኝ ባይን በንግድ ምልክቱ የመጠቀም ህጋዊ መብት በእጅጉ የጎዳ መሆኑን ፍ/ቤቱ ተገንዝቦ የፅ/ቤቱን ውሳኔ ሙሉ በሙሉ በመሻር ስሙ በድጋሚ የተሰጠው ሆቴል “ክራውን ፕላዛ” በሚለው የንግድ ምልክት መጠቀም አይችልም የሚል ውሳኔ እንዲሰጥለት በሰኔ 23 ቀን 2006 ዓ.ም ለፍ/ቤቱ በፅሁፍ አመልክቶ ነበር፡፡ ፍ/ቤቱም መስከረም 7 ቀን 2007 ዓ.ም በዋለው ችሎት፤ ይግባኝ ባይ መስከረም 5 ቀን 2007 ዓ.ም በቃለ መሃላ በተደገፈ አቤቱታ እግድ መጠየቃቸውን አስታውቆ በሰጠው ትዕዛዝ፤ ሌላ ተለዋጭ ትዕዛዝ እስኪሰጥ ድረስ የኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ፅ/ቤት የሰጠው ውሳኔ አፈፃፀም ታግዷል ብሏል፡፡

የይግባኝ ቅሬታውን ለመስማትም ለጥቅምት 12 ቀን 2007 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡ በጉዳዩ ላይ ያነጋገርናቸው በኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ፅ/ቤት የንግድ ምልክትና ኢንስፔክሽን ዋና የስራ ሂደት ጊዜያዊ ዳይሬክተር አቶ ደረጀ ፅጉ፤ የፍ/ቤቱ እግድ ትዕዛዝ እንደደረሳቸው አረጋግጠው፣ ጉዳዩ በፍ/ቤት የተያዘ በመሆኑ ምንም አይነት አስተያየት መስጠት እንደማይችሉ፣ ነገር ግን ጽ/ቤታቸው የፍ/ቤቱን እግድ እንደሚያስከብር ገልፀዋል፡፡ አለማቀፍ የሆኑ የሆቴልም ሆነ ሌሎች ኩባንያዎች ስያሜና የንግድ አርማ የሃገራችን ኩባንያዎች በምን አግባብ ነው እንዲጠቀሙ የሚደረገው ስንል የጠየቅናቸው ዳይሬክተሩ፤ “ባለ ኩባንያው የንግድ ምልክቱን ያስመዘግባል፤ በንግድ ምልክቱ ዙሪያም ተቃዋሚ ካለ እንዲቀርብ የጋዜጣ ማስታወቂያ ይወጣል፤ ካልቀረበና በምርመራ ከተረጋገጠ ይሰጠዋል፤ በዚህ መንገድ ነው የሚስተናገደው” ብለዋል፡፡ በሌላ በኩል የስትራክቸር ግንባታ ስራው ሙሉ ለሙሉ መጠናቀቁ የተገለጸው “ክራውን ፕላዛ ሆቴል”ን የሚያስገነባው ፀሜክስ ሆቴሎችና ቢዝነስ ኃ/የተ/የግ ማህበር ከአለም ባንክ ጋር የ19 ሚሊዮን ዶላር የብድር ስምምነት የሚፈራረም ሲሆን በፀሜክስ እና በኢንተርኮንቲኔንታል ሆቴል ግሩፕ መካከል ደግሞ የሆቴል ማናጅመንት ኮንትራት ውል ስምምነት በነገው ዕለት ይፈራረማል ተብሏል፡፡