Administrator

Administrator

በኢትዮጵያ የአውሮጳ ኅብረት ልዑክ እና በአዲስ አበባ የሚገኙ 25 የኅብረቱ አባል አገራት ኤምባሲዎች (የጀርመን እና ፈረንሳይን ጨምሮ) እንዲሁም የአውሮፓ ኅብረት አባል ያልሆኑት ካናዳ፣ ኖርዌይ እና ስዊትዘርላንድ በጋራ በመሆን ስለ ሰባተኛው የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ መግለጫ አውጥተዋል። በግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. የተካሄደውን ምርጫ በበጎ እንደሚቀበሉ የገለጹት ዲፕሎማሲያዊ ተልዕኮዎቹ፤ ለሂደቱ ስኬት አስተዋጽዖ ላበረከቱት ለብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ ለምርጫ ሠራተኞች፣ ለፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ለዕጩዎች እና ለሲቪል ማኅበራት ተዋናዮች ያላቸውን አድናቆት ገልጸዋል። በተጨማሪም የአፍሪካ ኅብረት እና የኢጋድ የምርጫ ታዛቢዎችን ሚና በማድነቅ የዘገባዎቻቸውን ውጤት በጉጉት እንደሚጠብቁ አስታውቀዋል።
ይህ የጋራ መግለጫ ምርጫው በተካሄደ በሁለተኛው ቀን የወጣ ሲሆን፣ በትናንታው ዕለት በተለያዩ ምክንያቶች ምርጫ ያልተካሔደባቸው የምርጫ ክልሎች በሙሉ ድምጽ የመስጠት “ዕድል ይሰጣቸዋል” የሚል ከፍተኛ ተስፋ እንዳላቸውም አመልክተዋል። ዲፕሎማቶቹ በጋራ ባስተላለፉት መልዕክት ሁሉም ዜጎች በምርጫው የመሳተፍ መብታቸው ሊከበር እንደሚገባ በማሳሰብ፣ ምርጫ ባልተካሄዱባቸው አካባቢዎች ሂደቱ እንዲቀጥል ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
የአሜሪካ መንግስት በአፍሪካ አህጉር ውስጥ የሚገኙትን የቪዛ ማረጋገጫ ማዕከላቱን ቁጥር ከ50 ወደ 20 ክልላዊ ማዕከላት ዝቅ ለማድረግ ማቀዱን አስታውቋል። እነዚህ የተመረጡት 20 ማዕከላት በ19 የአፍሪካ ሀገራት ውስጥ የሚሰራጩ ሲሆን፣ ውሳኔው በአህጉሪቱ በሚገኙ በርካታ የቪዛ አመልካቾች ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ ይፈጥራል ተብሎ ይጠበቃል።
በዚህ አዲስ አሰራር መሰረት እንደ ጆሃንስበርግ፣ ሌጎስ፣ ናይሮቢና አክራ ያሉ ዋና ዋና ከተሞች ለአሜሪካ ቪዛ ሂደት ቁልፍ ማዕከላት ሆነው ያገለግላሉ። በዚህም ምክንያት በአካባቢያቸው የነበረውን የቪዛ አገልግሎት የሚያጡ ሀገራት ዜጎች፣ ለቪዛ ቃለ-መጠይቅና ለቆንስላ ጉዳዮች ወደነዚህ ወደተመረጡት ዋና ዋና ማዕከላት ረጅም ርቀት ተጉዘው ለመሄድ ይገደዳሉ።
ይህንን ውሳኔ የሚደግፉ ወገኖች አዲሱ አሰራር የአገልግሎት ቅልጥፍናን እንደሚጨምርና አላስፈላጊ ወጪዎችን እንደሚቀንስ እየተናገሩ ይገኛሉ። በአንጻሩ ግን በርካታ ተቺዎች ውሳኔው ለአመልካቾች ረጅም የጥበቃ ጊዜን ከመፍጠሩም በላይ፣ ከፍተኛ የሆነ ተጨማሪ የጉዞና የሆቴል ወጪዎችን በትከሻቸው ላይ የሚጭን አድሎአዊ አሰራር ነው ሲሉ በብርቱ እየተቃወሙት ነው።
የዘንድሮውን የ7ኛ ዙር አገራዊ ምርጫ ለመታዘብ የሚያስችለኝን ዕድል አግኝቼ ነበር። እናም በግልና የተለያዩ ተቋማትን ወክለን የመጣን የአገር ውስጥ ታዛቢ ቡድን አባላት ምርጫውን ለመታዘብ ከመጡ የአፍሪካ ኅብረት እና የኢጋድ የታዛቢ ቡድን አባላት ጋር በስካይ ላይት ሆቴል የትውውቅና ሰፋ ያለ የጋራ ውይይት አድርገን ነበር።
በዚህ ውይይት ላይም የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪና የቀድሞ የኡጋንዳ የቀድሞው ምክትል ፕሬዚደንት የነበሩት ዶ/ር ዋንዲራ ካዚብዌ በምክር መልኩ ለወጣቶች ያነሱት ሐሳብ ቀልቤን ገዛው። እናም ከእኚህ ጉምቱ ፖለቲከኛ አፍሪካዊ እናት ከሐሳባቸው ጥቂት ሰበዞችን ለመምዘዝ ወደድኹ።
በአገራቸው ኡጋንዳ ፖለቲካ ውስጥ የሴቶችን/የእናቶችን የፖለቲካ ተሳትፎ ትርጉም ባለው መንገድ በመቀየር ጉልህ አሻራ ያኖሩት የህክምና ሳይንስን ከሥነ-መንግሥት ትምህርት ጋር ያጣጣሙ እኚህ አፍሪካዊ ምሁር እናት በውይይታችን መካከል እንዲህ አሉን።
"When women lead, even water climbs uphill."
"ሴቶች ሲመሩ ውኃ ሳይቀር እንኳን ሽቅብ ይፈሳል፤" የሚል አፍሪካዊ አባባል አለ።
መቼም ለዚህ አባባል እናንት ኢትዮጵያውያን ሕያው ምስክሮች ናችሁ። ከኢትዮጵያዊቷ ንግሥት ሳባ፣ የዐድዋውን ጦርነት በሴትነት ብልሃት ከመሩት እቴጌ ጣይቱ ድረስ የአገራችሁ የፖለቲካ ታሪክ በሴቶች ጉልህ ተሳትፎና አሻራ የደመቀ ነው። በእውነት በእነዚህ ጀግኖች እናቶቻችሁ ታሪክ ልትኮሩ፤ ልትደነቁ ይገባችኋል።
ዶ/ር ካዚብዌ ቁጭት በቀላቀለ ስሜት ያነሱትን ሌላኛው የሐሳባቸውን ሰበዝ ለዚህች አጭር ማስታወሻ መደምደሚያ ይሆነኝ ዘንድ መረጥኩት።
እኛ አፍሪካውያን ዲሞክራሲያዊ ሥርዓትን እንደ ሸቀጥ ዕቃ ሙሉ በሙሉ ከምዕራቡ ዓለም ለማስገባት የምናደርገውን ልፋት ቆም ብለን መፈተሽ ይገባናል። ከሌሎች የምንቀበለውን ያህል እኛ አፍሪካውያን ለተቀረው ዓለም ልንሰጠው የምንችላቸው በርካታ ነገሮች አሉን።
አፍሪካ ለሺህ ዓመታት የቆየ የራሷ የሆነ ግዙፍ ታሪክ፤ ገናና ሥልጣኔ፤ በዘመናት ተፈትኖ ያለፈ የዳበረ ባህላዊ የፖለቲካ ሥርዓት ያላት አህጉር ናት። እናንት ኢትዮጵያውያን ደግሞ በዚህ የአኅጉራችን የአፍሪካ የሺህ ዘመናት ታሪክና ባህል ውስጥ የአንበሳውን ድርሻ ትወስዳላችሁ።
ከአክሱም ገናና ሥልጣኔ የቅኝ ገዢዎችንና የተስፋፊዎችን ቅስም እስካንኮታኮተው የዐድዋ ድል ድረስ አኩሪ ታሪክ ያላችሁ ታላቅ ሕዝብ ናችሁ። አብዛኛው የታሪካችሁ ምዕራፍ ሲገለጽም- የአንድነትን፤ የኅብረትን ኃይል ቀድሞ የተረዳችሁ ጠቢባን ሕዝቦች መሆናችሁን ነው የሚመስክረው። እናም ዛሬ ልዩነታችሁን በማጥበብ አንድነታችሁን አጠናከሩ፤ ኅብረታችሁን አጎልብቱ። አንድነት ኃይል ነው!!
ኢትዮጵያ በመከፋፈል ሳይሆን በአንድነት የደመቀ፤ በጦርነት ሳይሆን በሰላም ያሸበረቀ፤ በጥላቻ ሳይሆን በፍቅር የተዋበ አፍሪካዊ ተምሳሌትነቷንና እናትነቷን ያስመሰከረች አገር ሆና እንድትቀጥል ነው ምኞታችን፤ ተስፋችንና ጸሎታችን።
እግዚአብሔር አፍሪካን ይባርክ፤ አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ!!
ነገርን ነገር ያነሳዋል እንዲሉ አበው፤ ጠቅላይ ሚ/ር ዶ/ር ዐብይ አሕመድ ወደ ሥልጣን በመጡ ማግሥት- ኢትዮጵያውያን እናቶች ይጸልዩልኛል፤ የእናቶቼ ጸሎታቸውና ምርቃታቸው ያግዘኛል፤ ጉልበት ይሆነኛል። የሚል ቃልን አብዝተን ከአንደበታቸው አንሰማ ነበር። ዛሬስ...?!
ታላቁ መጽሐፍ፤ "የእናት ምርቃት ቤትን ያጸናል፤" እንዲል በእናቶቻችን ምርቃትና ጸሎት የሁላችን ቤት የሆነች ኢትዮጵያ፤ አፍሪካ የአንድነት መሠረቷ ጸንቶና ሰላሟ ተጠብቆ በአንድነት ጸንታ ትኖር ዘንድ በመመኘት ልሰናበት።
ሰላም!!
በተረፈ ወርቁ (ዲ/ን)
በመካከለኛው ምስራቅ ባለው ወቅታዊ ቀውስ ምክንያት ከፍተኛ የጸጥታ ስጋት በነበረበት የሆርሙዝ ሰርጥ አካባቢ የነበረችው የኢትዮጵያ ባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ንብረት የሆነችው “አሶሳ” መርከብ ሰርጡን በሰላም መሻገሯ ተሰምቷል።
መርከቧ ከሰርጡ በቅርብ ርቀት ላይ ወደምትገኘው ኮርፋካን ወደብ በመድረስ፣ ለሀገራችን እጅግ ወሳኝ የሆኑ የሕክምና እና የንግድ ጭነቶችን በተሳካ ሁኔታ በመጫን ጉዞዋን አጠናቃ በሰላም ወደ ሀገሯ ተመልሳለች።
የአርሰናልን የፕሪሚየር ሊግ ዋንጫ ድል ለመዘከር "WE CHAMPIONS 2026" የተሰኘ ታሪካዊ የእግር ኳስና የመዝናኛ ፌስቲቫል የፊታችን ቅዳሜ ግንቦት 29 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስታዲየም ሊካሄድ ነው። በቫርደስ ኢንተርቴይመንት አዘጋጅነትና በአዋሽ ባንክ (አዋሽብር ፕሮ) ዋና ስፖንሰርነት የሚከናወነው ይህ ዝግጅት፣ ከ30 ሺህ በላይ የእግር ኳስ አፍቃሪያንን፣ ዓለም አቀፍ ሌጀንዶችንና የሚዲያ ባለሙያዎችን በአንድ ላይ የሚያሰባስብ ታላቅ መድረክ ነው። ዝግጅቱ የሀገራችንን ባህል፣ እንግዳ ተቀባይነትና የመዝናኛ ኢንዱስትሪ ለዓለም ለማስተዋወቅ ትልቅ ዕድል እንደሚፈጥርም ተገልጿል።
በዚህ ደማቅ መርሃ ግብር ላይ የቀድሞው የአርሰናል እና የኮትዲቯር ብሔራዊ ቡድን ኮከብ ተጫዋች ኤማኑኤል ኢቡዌ በልዩ እንግድነት የሚገኝ ሲሆን፣ ታዋቂው የለንደኑ "Arsenal Fan TV" (AFTV) ተወካዮችም በቦታው ይገኛሉ። ዝግጅቱ በአጠቃላይ በAFTV የዩቲዩብ ቻናልና በተለያዩ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች በቀጥታ የሚተላለፍ በመሆኑ የሀገራችንን ገጽታ ለመገንባት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሏል።
በዕለቱ መድረኩን የሚያደምቁ ከ10 በላይ ታዋቂና ወጣት ኢትዮጵያውያን ድምፃውያን የተሰለፉ ሲሆን፤ ታደለ ሮባ፣ ልጅ ሚካኤል (ፋፍ)፣ ሳሚ ዳን፣ አስጌ ዴንዳሾ፣ ራሄል ጌቱ፣ ሮቤል ሚዲቅሳ፣ ዮ ማሪዮስ፣ ሚክ ዋን፣ አማኑኤል የማነ፣ አዲስ ሙላት እንዲሁም እውቁ የአፍሮቢትስ ሙዚቃ ተጫዋች ፍራንኪዬ ዲ ስራዎቻቸውን ያቀርባሉ። ለፌስቲቫሉ መግቢያ የሚሆን ትኬትን በአዋሽ ብር ፕሮ፣ በአዋሽ ባንክ ቅርንጫፎች ወይም በስታዲየም በሚገኙ ጊዜያዊ የትኬት ጣቢያዎች መግዛት እንደሚቻል አዘጋጆቹ አስታውቀዋል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዕውቅና የሰጣቸው መገናኛ ብዙኃንና ጋዜጠኞች በምርጫ ጣቢያዎች ውስጥ እንዳይንቀሳቀሱና መረጃ እንዳይሰበስቡ ከተለያዩ የፓርቲ ታዛቢዎችና የፀጥታ ኃይሎች ክልከላ እየገጠማቸው መሆኑን አስታወቀ። በተለይም «ኢትዮጵያ ኢንሳይደር» የተባለው የዜና ምንጭ በልደታ፣ የካ፣ ቂርቆስ እና ለሚ ኩራ ክፍለ ከተሞች ውስጥ ጋዜጠኞቹ ባጅ ይዘው እንኳ እንዳይቀርጹና መረጃ እንዳይሰበስቡ መከልከላቸውን ይፋ አድርጓል። ቦርዱ ይህንን ጋዜጠኞችን ከሥራ የማስቆም ድርጊት «የተሳሳተ» ሲል የኮነነ ሲሆን፣ ማንኛውም አካል ቦርዱ ሕጋዊ ኃላፊነቱን ሲወጣ የመተባበር ግዴታ እንዳለበት በጥብቅ አሳስቧል።
ምርጫ ቦርድ ሂደቱን በነጻነት እንዲዘግቡ በአጠቃላይ 68 መገናኛ ብዙኃንን እና 1,815 ጋዜጠኞችን መዝግቦ መለያ ባጅ መስጠቱን ገልጿል። እነዚህ የጋዜጠኝነት ባጅ ያላቸው ባለሙያዎች በምርጫ ጣቢያዎች 200 ሜትር ንፍቀ ክበብ (ራዲየስ) ውስጥ ገብተው የመዘገብ ሙሉ ሕጋዊ መብት እንዳላቸው ቦርዱ አስታውቋል። በሌላ በኩል፣ ቢቢሲ ምርጫውን በአገር ውስጥ ለመዘገብ ፈቃድ እንዳልተሰጠው የተገለጸ ሲሆን፣ ምርጫ ቦርድ የመገናኛ ብዙኃንን ነጻነት የሚጋፉ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡና ከሕግ አሠራር ጋር እንዲሰለፉ ጥሪ አቅርቧል።

የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ልዑክ መሪና የቀድሞው የኬንያ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ በኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሰላማዊ ሁኔታ መጀመሩን ገልጸዋል።

በምርጫ ጣቢያዎች የተመለከቱት ነገር መልካም እንደነበር የጠቀሱት ኬንያታ፤ ይህ በሰላምና በሥርዓት የመምረጥ ሂደት ቀኑን ሙሉ እንዲቀጥል ተመኝተዋል።

“ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋና ከተማ ናት፤ በዚህች ሀገር የሚመዘገብ ስኬት ለመላው አህጉር ብርሃን ነው” በማለት ለኢትዮጵያ ሕዝብ መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።

Page 3 of 808