Administrator

Administrator

‹‹ማኅበሩን የማዳከምና የማፍረስ ፖለቲካዊና ሃይማኖታዊ ተልእኮ ነው››
/አባላትና ደጋፊዎ

   ማኅበረ ቅዱሳን የተዘጋጀውን የአስተዳደር መዋቅር ተቆጣጥሮ ለፖለቲካ ጥቅም ሊያውል ይፈልጋል በማለት የሚቃወሙ የአዲስ አበባ የደብር አስተዳዳሪዎች ዛሬ ስብሰባ የሚያካሂዱ ሲሆን፤ የማህበረ ቅዱሳን አባላት በበኩላቸው ዘመቻ ተከፍቶብናል ይላሉ፡፡
የአዲስ አበባ አድባራት አስተዳዳሪዎች ማኅበሩ ሀብቱንና ንብረቱን እንዲያስረክብ ሊያስገድዱት ተዘጋጅተዋል ይላሉ የማህበሩ አባላት፡፡
ማኅበሩ የቤተ ክርስቲያኒቱን መዋቅር በመጣስ እንደሚንቀሳቀስ የሚጠቅሱት አስተዳዳሪዎቹ በበኩላቸው፤ ገንዘቡንና ንብረቱን የሚያንቀሳቅሰው ከጠቅላይ ቤተ ክህነት አሰራር ውጭ ስለሆነ   የሀብቱና ንብረቱ መጠን አይታወቅም ይላሉ፡፡
‹‹ማኅበሩ አቅጣጫውን የሳተ የኦርቶዶክስ ሰለፊ ነው›› በማለት ማኅበረ ቅዱሳንን የሚፈርጁ አስተዳዳሪዎች እንዳሉ የሚናገሩት የማህበሩ አባላት፤ ዘመቻ እንደተከፈተባቸው የሚገልፁ ሲሆን፤ የአድባራት አስተዳዳሪዎች በበኩላቸው ማህበሩ በቤተክርስቲያን ላይ ዘመቻ ከፍቷል ይላሉ፡፡ ማኅበሩ ለሀገረ ስብከቱ የሠራው የመዋቅር፣ የአደረጃጀትና የአሠራር ጥናት፣ ማኅበሩ የቤተ ክርስቲያኒቱን መዋቅር በመቆጣጠርና በፖለቲካ ከቤተ መንግሥቱ አጣምሮ በመያዝ ዓላማውን ለማራመድ ያዘጋጀው ነው ሲሉ የሚቃወሙ አስተዳዳሪዎች እንዳሉ ታውቋል፡፡  
‹‹ሕግ የሌለውና ለሕግ የማይታዘዘው ማኅበረ ቅዱሳን ለእኛ ሕግ ሊያወጣልን አይችልም›› የሚሉት አስተዳዳሪዎቹ፤ ከየአድባራቱ አምስት አምስት ሠራተኞች ይገኙበታል በተባለው በዛሬው ስብሰባቸው፤ ማኅበሩ ሕግ ወጥቶለት ወደ መዋቅር እንዲገባ በመግለጫቸው እንደሚጠይቁ የማኅበሩ አባላት በበኩላቸው፣ ማኅበሩ የሚመራው በ1994 ዓ.ም. በቅዱስ ሲኖዶስ ለሦስተኛ ጊዜ ጸድቆ በተሰጠው መተዳደርያ ደንብ ነው በማለት ‹‹ሕግ የሌለው ሕገ ወጥ ነው›› መባሉን ተቃውመዋል፡፡
ማኅበሩ በየዓመቱ ፈቃድ ባለውና ብቃቱ በተመሰከረለት የውጭ ኦዲተር፣ የፋይናንስ እንቅስቃሴውን እያስመረመረ ለጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ሪፖርት እንደሚያቀርብ አባላቱ ተናግረዋል፡፡

            ከዕለታት አንድ ቀን፣ አንድ ማታ ላይ፤ አንድ ሰው ወደ አንድ ቡና ቤት፣ አንድ አሣማ ይዞ ይገባል። የቡና ቤቱ የመጠጥ ኃላፊ፤ በጣም ጠንቃቃና የጉጉት-ዐይን ያለው ዓይነት ሰው ነው፡፡ ሰውዬው ይዞት የመጣው አሣማ አንድ እግሩ በእንጨት የተጠገነ ነው፡፡ ይህንን የመጠጥ ኃላፊው አይቷል፡፡
ወደ እንግዳው ሄዶ እንዲህ አለው፡-
“ይህ አሣማ ምን ሆኖ ነው አንድ እግሩ እንጨት የሆነው?”
ሰውዬውም፣
“አንድ ቢራ ከሰጠኸኝ፤ ስለዚህ ልዩ ባህሪ ስላለው አሣማ ታሪክ እነግርሃለሁ!” አለው፡፡
የመጠጥ ኃላፊው፤ “መልካም፡፡ ጥሩ ታሪክ የሚወጣው ስለመሰለኝ፤ እንካ አንድ ቢራና ታሪኩን ትነግረኛለህ” አለና አንድ ቢራ አቀረበለት፡፡
“ስለዚህ ተዓምረኛ አሣማ ልንገርህ” አለና ጀመረ ያ ሰውዬ፡፡ “በጣም ልዩ አሣማ ነው፡፡ አንድ ማታ፤ ከአንድ ዓመት በፊት ገደማ፣ ድንገት ቤቴ በእሳት ተያያዘ፡፡ ይሄኔ ያ አሣማ ከበረቱ በርግዶ ወጣና፣ ወደ ቤቴ መጣ፡፡ ሁለቱን ልጆቼን ተሸክሞ ይዟቸው ወጣ፡፡ እኔና ሚስቴንም ሰላም ወደሆነው ሥፍራ ይዞን ወጣ! ስለዚህ፤ ቤተሰቤንና ህይወቴን አዳነልኝ ማለት ነው!!”     
ያ የመጠጥ ክፍል ኃላፊም፤ በታሪኩ ተገርሞ፣
“በጣም የሚገርም ጉድ ነው፡፡ ግን ለምን አንድ እግሩ እንጨት ሆነ?” አለው ደገመና፡፡  ሰውዬውም፤
“አንድ ቢራ ከጋበዝከኝ የዚህን ተዓምረኛ አሣማ ታሪክ እነግርሃለሁ” ይለዋል፡፡ የመጠጥ ክፍል ኃላፊው ምሥጢሩን ለማወቅ በጣም ጓጓ፡፡ ካረግኸው ጥሩ፤ ብሎ አንድ ቢራ ጨመረለት፡፡
ሰውዬውም፤
“ከእኔ ቤት ጀርባ አንድ ሐይቅ አለ፡፡ ከዕለታት አንድ ቀን፤ ጀልባ ይዤ ልቀዝፍ ወጥቻለሁ፡፡ ድንገት ማዕበል መጥቶ ጀልባዋ ተገለባበጠች፡፡ እኔ እጀልባዋ ወለል ላይ ተፈጠፈጥኩ፡፡ ከዚያ ወዲያ መዋኘት አልቻልኩም፡፡ ይሄ አሣማ ያንን አውቆ፤ በረቱን በርግዶ ወጥቶ ወደ እኔ ዋኝቶ መጥቶ ወደ ሐይቁ ዳርቻ ወሰደኝ፡፡  መተንፈስ አቅቶኝ አሸዋው ላይ ተንጋለልኩኝ፡፡ ከዚያ ወደ ቤቴ ሄዶ፣ ባለቤቴን ቀስቅሶ ይዟት መጣ፡፡ እሷ ትንፋሽ መግባኝ ነብሴን ዘራሁ፡፡ ይሄ አሣማ ህይወቴን አዳነልኝ” እልሃለሁ አለው፡፡
የመጠጥ ክፍሉ ኃላፊ በጣም ተደንቆ፣ ግን በመጠኑ ትዕግሥት አጥቶ፤ “በጣም አስደናቂ ትንግርት ነው፡፡ ግን የአንድ እግሩ እንጨት መሆን ሚሥጥር ትርጉሙ ምንድን ነው?” አለና ጠየቀው፡፡
“አንድ ሌላ ቢራ ጋብዘኝና እነግርሃለሁ…” አለው፡፡ ባለ መጠጥ ቤቱ ሌላ ቢራ ከፈተለት፡፡
“ስለዚህ ተዓምረኛ አሳማ አሁን ልንገርህ፡፡ ባለፈው ሳምንት ከፍተኛ አውሎ ንፋስ ተነስቶ እኔ ለመሸሽ ወደ ምድር ቤት ስሮጥ አዳለጠኝና ወደቅሁኝ፡፡ አሳማ ሆይ ከበረቱ በርግዶ ወጥቶ እየጐተተ ምድር ቤት አውርዶኝ ከአውሎ-ነፋሱ ተረፍኩኝ እልሃለሁ”
ባለ መጠጥ ቤቱ ይሄ የመጨረሻው ተዓምር መሆን አለበት ብሎ፤
“ይገርማል ተዓምረኛ አሣማ ነው ባክህ! ከእሣት፣ ከውሃና ከአውሎ ነፋስ አዳነህ! ግን ይሄ የእንጨት እግሩ ከየት መጣ?”
ሰውዬውም በመጨረሻ፤     
“እንዲህ ያለውን ተዓምረኛ አሣማኮ ሁሉንም ባንድ ጊዜ አትበላውም፡፡ ቀስ ቀስ እያልክ፣ ትንሽ ትንሽ ብልቱን እየለየህ፣ ነው መብላት ያለብህ!!” አለው፡፡   
*    *    *
ለአገር ባለውለታ የሆኑን ሰዎች በምንም ዓይነት ውለታቸውን መርሳት አይገባንም፡፡ ሁሉም ዜጋ የየራሱ ድርሻ አለውና ያንን አስተዋፅዖውን አለመርሳት ብልህነት ነው፡፡ የተሻለና የበለጠ ያገለገለን ዜጋ ደግሞ፤ የተሻለ እውቅና መስጠት ይገባናል፡፡ ይህ “ሥራ ለሠሪው እሾህ ላጣሪው” ዓይነት መንገድ ነው፡፡ ስለሆነም፤ የሀገርን የዕድገት መንፈስ የሚያፀና ነው!
አስተሳሰባችን ሙሉ ይሁን፡፡ ለእኛ የሚመች የሚመቸውን ብቻ የፖለቲካ መዘውር ነው ካልን የሚያጎድለን እንጂ የሚያሟላን ፀጋ አልጨበጥንም ማለት ነው፡፡ ጨቋኝና ተጨቋኝ  ባለበት አገር በድሮው አነጋገር Class based society ውስጥ የተበዳዩን ቁጥር ለመቀነስ ፍትሐዊ አስተዳደር ያስፈልጋል፡፡ “በምድር ላይ የሚራመድ አንድ ‘ባሪያ’ እስካለ ድረስ፤ ሙሉ በሙሉ ነፃ አንወጣም” ይሉናል ፀሐፍት። መልካም አስተዳደር እኛ እንደምንገምተው ቀላል አይደለም፡፡ ባህላዊ ታሳቢ እሴቶችን ሳናመዛዝን፤ የውጪውን አስገብተን እንዳለ ህዝባችን ላይ እንጫን ብንልም ዓላማው ጉዳዩን ከማወሳሰብ አያልፍም፡፡ ለዚህ ነው በሀገራችን መሻሻል የማናየው፡፡ ከመሠረታችን እንደማተባችን የማንበጥሳቸው አልበገር-ባይነት (Resistance) ውስጣችን አለ፡፡ ያንን ለማውጠንጠን ነፃ አስተሳሰብ ያስፈልጋል፡፡ ለዚህ መንግሥትም የራሱን ኃላፊነት መወጣት አለበት፡፡ ህዝብም እንደዚሁ ይህ ይሆን ዘንድ መጣጣር አለበት፡፡ የረዥም ጊዜ ግልፅ ውይይት፤ ሀሜትን ያስወገደ ዕውነተኛና ልባዊ ለውጥ ላይ ያተኮረ ረዥም ጉዞ ያስፈልገናል። ችግሩ እንግዲህ፤ መለወጣችንን የሚያይልን ራሱ ያልተለወጠ ሰው ከሆነ ተያይዞ ገደል መግባት ሊሆን ነው፡፡ ለምሳሌ ይሄ የእገሌ፣ ያ የእገሌ ብሄረሰብ፣ ጎሣ፣ መንደር ወዘተ ሰው ነው በሚል ሌላውን አሳንሶ የማስቀመጥ አመለካከት፤ እንደቀንድ-አውጣ ውስጣችን ያደፈጠ የለውጥ እንቅፋት ነው። ለፍቅረኞች ቀን፤ የአበበ ዘንግ ሽያጭ፤ አበባ ልብን ላያመላክት ይችላል! ገቢ አለ፡፡ በገቢው የምንሠራው ምንድነው? ይሄ ብዙ ጊዜ ተደጋግሞ ሲነገር ሰምተናል፡፡ ጠጋ ብለን፣ የችግሩ ምንጭ የት ጋ ነው ብለን ግን ለማጤን አልፈቀድንም፡፡ “አንድን ጉድ፣ ሺ ጊዜ ከሰው ከመስማት አንዴ ሄዶ በዐይን አይቶ እርፍ ማለት ይሻላል” ይላሉ ፈረንጆች፡፡ የታመመ ሰውን ጠይቆ የሚነግረን ሰው፤ ስለበሽተኛው የግሉን ስሜት ብቻ አጋኖ እንደሚነግረን እረስተን፤ እኛም ያንኑ ወሬ ለሌላ ጆሮ እናስተላልፋለን፡፡ ሺ ጊዜ በማጉላትም ጣር-አልጋ ላይ ያለ ሰው አድርገነው ቁጭ እንላለን፡፡ አገራችን ታማለች ካልን ቀርቦ ማየት ነው፡፡ የሚሻለውን መምከር፣ የምትታከምበትን መላ መምታት ነው ያለብን፡፡
የሀገራችን ችግሮች እጅግ በርካታ ለመሆናቸው አዋቂ መጠየቅ አያሻንም፡፡ ተራ በተራ ለመፍታት መጣጣር ነው እንጂ የለም ብሎ መካድ ግን ቢያንስ ራስን ማታለል ነው፡፡ ከራሳችን አበሳ በተጨማሪ፤ በተጋቦት እስከሚመጡት የድምበርተኛ ጎረቤቶቻችን ችግር ድረስ፤ የችግር መተላለፊያ ኮሪዶር ነን ብለናልና፤ ኮሪዶሩ መጠረግ አለመጠረጉን አለማረጋገጥ ለባሰ መዘዝ ይዳርገናል፡፡ “እንኳን አሁንና ብዙ ትጥቅ እያለን
በጦር በጎራዴ፣ ታንክ እናማርካለን”
ማለት በዘመነ-ግሎባላይዜሽን (የለየለት ቅኝ-ገዢነት) እንደማያዋጣ ማንም ሊስተው አይገባም። የሀብት ምንጮቻችንን እንጠብቅ፡፡ የሰው ኃይላችንን፣ ጦራችንን በአግባቡ እንጠብቅ! ለገዛ ጥቅሙ በስተቀር ለእኛ ብሎ እሹሩሩ የሚለን የዓለም ታላቅ አገር የለም፡፡ “አበሻም ይሁን ፈረንጅ ማንም ህዝቡ ላይ ጫና ሊጥል አይገባም” የሚለውን አባባላችንን ማጥበቅ መልካም ነገር ነው! “አነስተኛ ነን ብለን እጃችንን መጠምዘዝ የለብንም፡፡ ችግራችን የብረት በር ሆኖብናል አንበል፡፡ “እጅግ በጣም ትልቁ የብረት በር እንኳን የሚከፈተው በትንሽ ቁልፍ መሆኑን አትርሳ” ይለናል ደራሲ ቻርልስ ዲከንስ፡፡ ልብ ያለው ልብ ይበል ነው ነገሩ!!   

        66 አጫጭር ግጥሞችን ያካተተውና በተማሪ ማንያዘዋል እሸቱ የተፃፈው “የህይወት ኮስሞቲክስ” የግጥም መድበል ሰሞኑን ለንባብ በቃ፡፡
በ66 ገፆች የተቀነበበው የግጥም መድበሉ፤ ተማሪው ከ2002 ዓ.ም ጀምሮ ያሰባሰባቸው ግጥሞች የተካተቱበት ሲሆን በማህበራዊ፣ በፍቅር፣ በአገር፣ በወጣትነት፣ በካምፓስ ህይወትና ሌሎች ጉዳዮች ዙሪያ የሚያጠነጥን እንደሆነ ታውቋል፡፡
በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ የሁለተኛ አመት የኢንቫይሮንሜንታል ኢንጂነሪንግ ተማሪ የሆነው ገጣሚው፤ የፊልም ስክሪፕት የመፃፍ ስራ ላይ ማተኮሩን ገልፆ የመጀመሪያ ስራው የሆነው ይህ የግጥም መድበል፤ ህይወትን የሚያስውቡና በብዙ የህይወት ጉዳዮች የሚያጠነጥኑ ግጥሞች ስለተካተቱበት “የህይወት ኮስሞቲክስ” የሚል ርዕስ እንደሰጠው ጠቁሟል፡፡ መፅሀፉ በ25 ብር ለገበያ የቀረበ ሲሆን የሚማርበት ዩኒቨርስቲ ስፖንሰር እንዳደረገው ገጣሚው ተናግሯል፡፡

በጋዜጠኛ ግርማ ለማ የተፃፈውና በቀዳማዊ ሀ/ስላሴ የቤት ውስጥ ውሎ፣ ቤተሰባዊ ህይወትና የጓዳ ታሪክ ላይ የሚያጠነጥነው “የንጉሱ ገመና” ለንባብ በቅቷል፡፡
መፅሀፉ እስከ ዛሬ በንጉሱ ዙሪያ ከተፃፉት መፅሀፎች የሚለየው በቤት ውስጥ ውሏቸውና ገመናቸው ላይ የሚያተኩር በመሆኑ ነው ተብሏል፡፡ 170 ገፆች ያሉት መፅሀፉ፤ በአርጋኖ የህትመት ኢንዱስትሪ ታትሞ በጃፋር መፅሀፍ መደብር እየተከፋፈለ ሲሆን በ49 ብር ከ75 ሳንቲም ለገበያ መቅረቡም ታውቋል፡፡

    ነዋሪነታቸውን በለንደን ባደረጉት ኢንጂነር ወንድሙ ነጋሽ የተፃፉት “የአዕምሮ አስተዳደር ሞዴል” እና “ፍቅር ምንድን ነው?” የተሰኙ መፅሀፎች ለንባብ በቁ፡፡ እነዚህ መፅሀፎች ተከታታይ ክፍል እንደሚኖራቸው የተገለፀ ሲሆን በመጀመሪያው እትም ሰላም፣ ደስታና ፍቅር ስለማግኘት፣ በአላማ ስለመፅናት፣ ስሜትን ስለመቆጣጠር እና በራስ ስለመተማመን በስፋት መተንተኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡
በ49 እና በ59 ብር ለገበያ የቀረቡት መፃህፍቱ ቀጣይ ክፍላቸው ለህትመት በዝግጅት ላይ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን ፀሀፊው ኢ/ር ወንድሙ ነጋሽ ላለፉት 15 ዓመታት በእንግሊዝ የጦር መርከቦችን ከአደጋ የመከላከል ሲስተም መሃንዲስ በመሆን ከመስራታቸው በተጨማሪ በስነ-አዕምሮና በስነ-ልቦና ላይ የተመሰረቱ ተከታታይነት ያላቸው ጥናታዊ መፅሀፍትን በመፃፍ ላይ እንደሚገኙ ለማወቅ ተችሏል፡፡ የመፃህፍቱ ተከታይ ክፍሎች ስለ ጣፋጭ ፍቅር፣ ስለ መልካም ግንኙነት፣ ስለ ስኬታማ ትዳር ስለ ስነ-አዕምሮና ስነ-ልቦና በሳል ግንዛቤ ያስጨብጣሉ ተብሏል።

Saturday, 15 March 2014 13:19

“ስንክርተነ” የተባለ

የጉራጊኛ የግጥም መፅሀፍ ነገ-ይመረቃል
የቤተ ጉራጌ ባህል ማዕከል ዋና ስራ አስኪያጅ በሆኑት በአቶ ተስፋዬ ጐይቴ የተፃፈው “ስንክርተነ” የተባለ የግጥም መፅሀፍ ነገ በደሳለኝ ሆቴል ይመረቃል። 135 ግጥሞችን ያካተተውና በ140 ገፆች ላይ የተመጠነው መፅሀፉ፤ በጉራጊኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን አብዛኞቹ ግጥሞች የጉራጌን ባህል፣ ወግና ትውፊት ያስቃኛሉ ተብሏል፡፡ ትልቁን የነፃነት ታጋይ የኔልሰን ማንዴላን ህይወት የተመለከተ ረጅም ግጥም እንደተካተተበትም አቶ ተስፋዬ ጐይቴ ገልፀዋል፡፡
በ33 ብር ለገበያ የቀረበው መፅሀፉ፤ በሴትኛ አዳሪነት ህይወት እና በሌሎችም ማህበራዊ ህይወት ላይ ትኩረት ያደረገ ሲሆን ፀሀፊው ከዚህ በፊት “የኬርጋት” እና “ጉራጌንዶ” የተሰኙ የግጥም መፃህፍትን በጉራጊኛ ቋንቋ ፅፈው ለንባብ አብቅተዋል።
ሶስተኛውና “ስንክርተነ” የተሰኘው የግጥም መፅሀፍ ነገ ጠዋት ከ2፡30 ጀምሮ ባለስልጣናት፣ የባህልና ቱሪዝም ሀላፊዎች፣ ጋዜጠኞችና ጥሪ የተደረገላቸው ሌሎች እንግዶች በተገኙበት በድምቀት ይመረቃል ተብሏል፡፡

ነዋሪነታቸውን በለንደን ባደረጉት ኢንጂነር ወንድሙ ነጋሽ የተፃፉት “የአዕምሮ አስተዳደር ሞዴል” እና “ፍቅር ምንድን ነው?” የተሰኙ መፅሀፎች ለንባብ በቁ፡፡ እነዚህ መፅሀፎች ተከታታይ ክፍል እንደሚኖራቸው የተገለፀ ሲሆን በመጀመሪያው እትም ሰላም፣ ደስታና ፍቅር ስለማግኘት፣ በአላማ ስለመፅናት፣ ስሜትን ስለመቆጣጠር እና በራስ ስለመተማመን በስፋት መተንተኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡
በ49 እና በ59 ብር ለገበያ የቀረቡት መፃህፍቱ ቀጣይ ክፍላቸው ለህትመት በዝግጅት ላይ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን ፀሀፊው ኢ/ር ወንድሙ ነጋሽ ላለፉት 15 ዓመታት በእንግሊዝ የጦር መርከቦችን ከአደጋ የመከላከል ሲስተም መሃንዲስ በመሆን ከመስራታቸው በተጨማሪ በስነ-አዕምሮና በስነ-ልቦና ላይ የተመሰረቱ ተከታታይነት ያላቸው ጥናታዊ መፅሀፍትን በመፃፍ ላይ እንደሚገኙ ለማወቅ ተችሏል፡፡ የመፃህፍቱ ተከታይ ክፍሎች ስለ ጣፋጭ ፍቅር፣ ስለ መልካም ግንኙነት፣ ስለ ስኬታማ ትዳር ስለ ስነ-አዕምሮና ስነ-ልቦና በሳል ግንዛቤ ያስጨብጣሉ ተብሏል።

በመምህርት ኑሀሚን ዋቅጅራ ተፅፎ በኢትጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርቲያን ማህበረ ቅዱሳን አሳታሚነት የተዘጋጀው “ማህቶተ-ጥበብ ዘልሳነ” ግዕዝ መፅሀፍ ለንባብ በቅቷል፡፡ 292 ገፆች ያሉት መፅሐፍ እየጠፋና እየተረሳ የመጣውን የግዕዝ ቋንቋ ለመታደግ ጥረት የተደረገበት ሲሆን በ20 ምዕራፎች ተከፋፍሏል፡፡
መፅሐፉ ስለ ግዕዝ ቋንቋ አመጣጥና ቀዳማዊነት፣ ስለ ግዕዝ ምንነት፣ ስለ ግዕዝ ፊደላትና ስለ በርካታ ጉዳዮች ቅኝት ያደርጋል፡፡ መፅሀፉ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ-ክርስቲያን ማህበረ ቅዱሳን ታርሞና ተስተካክሎ የተፈቀደ ሲሆን መታሰቢያነቱ ለፀሀፊዋ የግዕዝ አስተማሪ የቅኔ መምህር እና ጥበብ ፕሮፌሰር መጋቤ ምስጢራት ጌዲዮን መኮንን የተደረገ ሲሆን በ50 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡ ፀሀፊዋ ከዚህ ቀደም ለአቡነ ጐርጐ 1ኛ እና 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች የሚያገለግሉ ከአንደኛ እስከ አራተኛ፣ ከአምስተኛ እስከ ስምንተኛ እንዲሁም ከዘጠነኛ እስከ አስረኛ ክፍል ላሉ ተማሪዎች የሚረዱ መፅሀፍቶችን አዘጋጅታለች፡፡
ማህቶተ-ጥበብ ዘልሳነ መፅሀፍ ባለፈው ሳምንት በአማኑኤል ቤተ-ክርስቲያን ተመርቋል፡፡  

Saturday, 15 March 2014 13:01

አብረን ያደርን ቀን

ሰው እንዴት ተታሏል…
   ምስራቅ ምትገኝ
   ከምዕራብ በስተቀኝ
   ሰማይ ላይ ነዉ ብሎ
   ጀንበርን ሰቅሏታል አድማስ ላይ ጠቅሎ፤
ግን እንዲህ አይርቁም አይደሉም ሰማይ ላይ
     ምስራቅም በከንፈር በጥርስ አምሳል ፀሀይ
     እኔ ቤት አድረዋል ጠባብ መደቤ ላይ፡፡
* * *
    አዝናለሁ ያዳም ዘር
        ብርሃን ካልቀላወጥክ በጉበኔ ተገን
                   አ-ታ-ያ-ት-ም   ነገን !!

ፍርቱና
ስንገናኝ…
ያርባ ቀን እድሌ ያርባ ቀን እድሉ
በቀለበት ታስረው ሰማንያ ተባሉ፤
ስንለያይ…
ሰማንያዉ ተቀዶ
ለሁለት ተጎርዶ
እኔ አርባዬን ይዤ ዳግም እናቴ ጋ
እሱ አርባዉን ይዞ ሌላ አርባ ፍለጋ፡፡
አበባ የሽጥላ
   

በኤርትራውያን ታጣቂዎች የተጠለፉትን ጀርመናውያን ያስመለሱ የአፋር  ሽማግሌዎች ምን ይላሉ?

         ከሁለት አመት በፊት ነው ድርጊቱ የተፈፀመው። በአፋር ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ከሚገኙ የቱሪስት መዳረሻ ቦታዎች አንዱ ወደ ሆነው ኢርታአሌ ይጓዙ የነበሩ ጀርመናውያን ቱሪስቶች ከኤርትራ ድንበር አቋርጠው በመጡ ታጣቂዎች ሲጠለፉ ሁለት ኢትዮጵያውያን ተገደሉ፡፡ ከመካከላቸው ማምለጥ የቻለው አንድ ኢትዮጵያዊ፣ በአቅራቢያ ወደ ምትገኘው የአፍዴራ ቀበሌ ኩሩርዋድ መንደር በመምጣት የተፈጠረውን ሁኔታ ለአካባቢው ነዋሪዎች ተናገረ፡፡ የመንደሯ ሽማግሌዎችም በኤርትራ ከሚገኙ የአፋር ባላባቶች ጋር በመደራደር፣ ጀርመናውያኑ በህይወት እንዲመለሱ አደረጉ፡፡ በአዲስ አበባ የሚገኘው የጀርመን ኤምባሲም ባለፈው ሳምንት የመንደሯ ሽማግሌዎች ጀርመናውያኑን በማስመለስ ላደረጉት ውለታ ምስጋና ያቀረበ ሲሆን ከትግራይ ደጋማ አካባቢዎች በመነሳት በአለት ውስጥ ለውስጥ ይሄድ የነበረን የዝናብ ውሀ አቅጣጫ በማስቀየር፣ ለህብረተሰቡ ጥቅም እንዲሰጥ ያሰራውን ፕሮጀክት በኢትዮጵያ የጀርመን አምባሳደር ኢዝሎር ሲሩስ በተገኙበት አስረክቧል፡፡
በኤርትራ ታጣቂዎች ተወስደው የነበሩትን ጀርመናውያን በማስመለስ ትልቅ ሚና የተጫወቱት ጊልሳ ያኢድ እና ሳልህ ኡስማን ሁኔታውን አስመልክቶ የተናገሩትን እንደሚከተለው በአጭሩ አቅርበነዋል፡፡
ቱሪስቶች ኢርታአሌን ለማየት ሲሄዱ ከአፍዴራ የሚያጅቧቸው ሁለት ሚሊሺያዎች እና አንደ መንገድ መሪ ይመደባል፡፡ ከኤርትራ የመጡት ሽፍቶች ሁለቱን ጀርመናውያን ጠልፈው ሲወስዱ ሁለት ኢትዮጵያውያንን ገድለው ነው፡፡ አንዱ ኢትዮጵያዊ ስላመለጠ ሁኔታውን መጥቶ ነገረን። በአፋር ባህል እኛን ብሎ የመጣ ሰው፣ እኛ መሬት ላይ መግደል ወይም ሲገደል ማየት ትልቅ ነውር ነው፡፡ ቱሪስቶቹ ምንም አይነት መሳሪያ አልያዙም። የውሀ ጥማቸውን ለመቁረጥ የላስቲክ ውሀ ብቻ ነበር የያዙት፡፡ ድርጊቱን እንደ ሰማን የአገር መከላከያ ሰራዊት፣ ልዩ ሀይል፣ ፖሊስ እንዲሁም  ሴቶች እና ህፃናት ሳይቀሩ ወደ ስፍራው ሶስት ቀን ተጉዘን ደረስን፡፡ ቦታው ከፍተኛ የውሀ እጥረት ያለበት ስለሆነ ግመሎቻችንን ውሀ ጭነን ነበር የሄድነው። ሴቶቹ እና ህፃናቱ ምግብና  ውሀ ለማቅረብ ነው ተከትለውን የመጡት፡፡ የሄድነው እጅግ ተቆጥተን ነበር፡፡ ብንሞትም እንሙት እንጂ እኛን ብለው የመጡ የውጪ ሰዎችን አፍነው መውሰዳቸውና ሚሊሺያዎቹንም መግደላቸው እጅግ አስቆጭቶናል። አርታአሌን  በቁጥጥር ስር ካዋልን በኋላ የተወሰኑት የተገደሉትን ሰዎች አስከሬን ጭነው ወደ አፍዴራ ሲመለሱ፣ እኛ በባህላዊው የአፋር የመረጃ መቀባበያ ዘዴ “ዳጉ” መሰረት መረጃ ማሰባሰብ ጀመርን፡፡ በኤርትራም ሆነ በኢትዮጵያ የሚኖረው አፋር  በጎሳ የተሳሰረ ነው፡፡ ማንም የታጠቀ ሀይል ይሁን ሽፍታ ከጎሳው ባላባቶች ትእዛዝ አይወጣም፡፡  አስራ ሁለቱ  የባላባት ልጆች ተሰባስበው መከሩ፡፡ ከአገር ውጪ ያሉ የባላባት ልጆችም የታገቱትን ሰዎች እንዲያስለቅቁ ጥሪ ቀርቦ መላላኩ ተጀመረ፡፡ ኤርትራ ለሚገኙት ባላባቶች ሰዎቻችን ለምን ተገደሉ? ተጠልፈው የተወሰዱት በምን ሁኔታ ላይ እንዳሉ እንዲነግሩንና አሳልፈው እንዲሰጡን ጠየቅናቸው፡፡ ባላባቶቹም በጥያቄያችን መሰረት የተጠለፉት ሰዎች እንዲመለሱ ተነጋገሩ። የባላባት ትእዛዝ የማያከብር ማንኛውም አፋር፣ የአፋር ዘር ያለበት ቦታ ላይ መኖር አይችልም። ታጣቂዎቹም ቢሆኑ የባላባቶችን ትእዛዝ ከጣሱ ማረፊያ ስለማይኖራቸው፣ የጠለፏቸውን ሰዎች ለመመለስ በተደረገው ድርድር ተስማሙ፡፡ የመንግስት አካላት በህገ መንግስት ላይ የሰፈሩ ድንጋጌዎችን እንደሚያከብሩ ሁሉ ሽፍቶችም ቢሆኑ የጎሳ ስርአቱንና ውሳኔውን ያከብራሉ፡፡  እኛም ድንበሩን ተሻግረን የተጠለፉትን ሰዎች ለመረከብ ኤርትራ ገባን፡፡ በኤርትራ ከሚኖሩ የአፋር ጎሳዎች አንዱ የሆነው የዳሂሜና ጎሳ ልጅ ሰዎቹን ይዞልን መጣ፡፡  እኛም ለሁለቱ አንዳንድ ግመል ሰጥተን፣ ውሀ የጫነችላቸውን አንድ ግመል አስከትለን ወደ መንደራችን ስንወስዳቸው፣ አጠገባቸው የነበሩት ሰዎች በጭካኔ ተገድለው፣ እነሱ በህይወት መመለሳቸው ደስታና ግራ መጋባት ውስጥ ከተታቸው፡፡ ደስታቸው ግን ወሰን አልነበረው፡፡
በኤርትራ ያሉ ታጣቂዎች እኛ ከቱሪስቶቹ በምናገኘው ጥቅም ደስተኞች ባለመሆናቸው በጣም እናዝናለን፡፡ እኛ ግን ማንም ቢሆን በኛ መሬት እንግዳ ሆኖ እስከመጣ ድረስ የደህንነቱን ጉዳይ በሀላፊነት መውሰድ ባህላዊ ግዴታችን ነው። ፈረንጆቹ እሳቱን ለመጎብኘት  ሲመጡ የግመል ኪራይ፣የአጃቢ፣ የመንገድ መሪ --- እየተባለ ስለሚከፈለን ብዙ ጥቅሞችን እናገኛለን፡፡ ከዛን ቀን በኋላም  ለቱሪስቶቹ የበለጠ ጥበቃ ማድረግ ጀመርን። አሁን በአንድ ቀን ውስጥ ብቻ ከአስር በላይ የጎብኚ  ቡድን  ይሄዳል፡፡  ሁሉም በሰላም ደርሶ እየተመለሰ ነው። ከሁለት አመት በፊት ጠለፋውን የፈፀሙት ሰዎች ስላልተያዙም ልዩ የፀጥታ  ሀይል እስከአሁን ጠለፋው የተደረገበት ቦታ ላይ ይገኛል፡፡