Administrator

Administrator

የሬጌ ሙዚቃ አቀንቃኙ ድምጻዊ ጆኒ ራጋ፣ በአዲሱ "እሳት እና ውሃ" አልበሙ እና በአልበም ቅምሻ ፕሮግራሙ፣ ከቴክኖ ከሞን 40 ስልክ ሞዴል ጋር አብሮ ለመስራት የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራርሟል፡፡
ለበርካታ ዓመታት ድምጹ የጠፋው ጆኒ ራጋ ከሰሞኑ "እሳት እና ውሃ" የተሰኘ ሁለተኛ አልበሙን ይዞ መምጣቱ ይታወቃል፡፡
በአረርቲ ከተማ አስተዳደር አረርቲ ማርያም ቤተክርስቲያን ዓመታዊ የቅድስት ድንግል ማርያም ክብረ በዓል ላይ እየተሰራ ያለው ቤተክርስቲያን እየተጎበኘ ባለበት ‎ሰዓት፣ ለፊኒሺንግ ሥራ የተረበረበው እንጨት ተደርምሶ በርካታ ምዕመናን ላይ የሞትና የአካል ጉዳት መድረሱ ይታወቃል።
እስካሁን ትክክለኛ የሟቾችና ተጎጂዎች ቁጥር አልታወቀም። አሁንም ሰዎችን ከተናደው ርብራብ የማውጣት ስራ እየተሰራ ነው።
የአረርቲ ከተማ ሠላምና ፀጥታ መምሪያ ፤ የጉዳቱ መጠን ከፍተኛ በመሆኑና ከእንጨት ርብራቡ ሥር ያልወጡ ሠዎች በመኖራቸው የጉዳት መጠኑን መገመት አስቸጋሪ እንደሆነ ለብሔራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ ገልጿል።
ከሆስፒታል በተረጋገጠው እስካሁን የ22 ሠዎች ሕይወት ማለፉን፣ በተጨማሪ 55 ሰዎች ላይ ከመካከለኛ እስከ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን አሳውቋል።
ለተጎጂዎች የመጀመሪያ ሕክምና በአንድ ሆስፒታል እና በ4 ጤና ጣቢያዎች እየተሠጠ ሲሆን፤ ከፍተኛ ጉዳት የደረሠባቸው 5 ተጎጂዎች ለተጨማሪ ሕክምና ወደ አዲስ አበባ ተልከዋል።
ተጎጂዎችን ለማትረፍ ኅብረተሠቡ ጥረት እያደረገ ሲሆን፤ አሁንም ድረስ ከርብራቡ ሥር ያልወጡትን ዜጎች ሕይወት ለማትረፍና ሕክምና እንዲያገኙ ለማድረግ ርብርብ እየተደረገ ነው።
Tikvah-
ቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
ኬንያ ከውጭ ከምታገኘው አጠቃላይ የሃይል አቅርቦት 83 በመቶውን ኢትዮጵያ እንደምታቀርብ ተገለጸ፡፡ በዚህም ኬንያ በዓመት 10 ሚሊየን ዶላር ገደማ ማዳን ችላለች ተብሏል፡፡
ኢትዮጵያ በተያዘው ዓመት እስከ ሰኔ 2025 ድረስ ኬንያ ከውጭ ካስገባችው ጠቅላላ የኤሌክትሪክ ሃይል 83 በመቶውን በመሸፈን ፣ የኬንያ ቀዳሚ የኃይል ምንጭ መሆኗ ተጠቁሟል፡፡
የኬንያው ካፒታል ኤፍ ኤም የአገሪቱን የኢነርጂና ነዳጅ ተቆጣጣሪ ባለሥልጣን ጠቅሶ እንደዘገበው፣ የኢትዮጵያ የሃይል አቅርቦት ከአገር ውስጥ የኃይል ማመንጫ የበለጠ ወጪ ቆጣቢ ሲሆን፤ ይህም ኬንያ በዓመት 10 ሚሊዮን ዶላር እንድታድን ያስችላታል፡፡
የኬንያው ቢዝነስ ዴይሊ አፍሪካ ጋዜጣ በበኩሉ፤ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት በኬንያ ሊፈጠር የሚችለውን የኃይል ቀውስ በመከላከል ረገድ ወሳኝ ነው ሲል ገልፆታል፡፡
“ኢትዮጵያ ኬንያን ከመብራት መጥፋትና ከፈረቃ ታድጋለች” ሲልም ጋዜጣው ዘግቧል፡፡
AS-
ቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
ህወሓት የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ዋስትና ሰጪ የሆኑት አሜሪካ፣ አውሮፓ ኅብረት፣ አፍሪካ ኅብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የገቡትን ቃል ተግባራዊ ሳያደርጉ ቀርተዋል ሲል ከሰሰ።
ፓርቲው ስምምነቱ ከተፈረመ ከሦስት ዓመታት በኋላም ቢሆን፣ በትግራይ ክልል “በዝምታ ውስጥ እየተፈጸመ ያለ ዘር ማጥፋት ቀጥሏል” ሲልም ገልጿል።
ህወሓት መስከረም 19 ቀን 2018 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ፣ በክልሉ እየተፈጸመ ያለውን ውድመት ለማስቆም ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ጣልቃ እንዲገባ አሳስቧል። አክሎም፣ “ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ አሁን እርምጃ እንዲወስድ እንጠይቃለን። የትግራይ ውድመት በዝምታ እንዲቀጥል አትፍቀዱ። ለሰላም የገባችሁትን ቃል አክብሩ፣ ንጹሐንን ጠብቁ፣ እናም ሌላ አሳዛኝ ክስተት እንዳይከሰት ተከላከሉ” ብሏል።
ፓርቲው፣ ተፈናቃዮች ወደ ቀዬአቸው እንዲመለሱና የተያዙ ቦታዎች እንዲለቀቁ ለማስቻል በህዳር 2022 የተፈረመው የፕሪቶሪያው ስምምነት በአብዛኛው ሳይተገበር ቀርቷል ብሏል። መግለጫው፣ “አብዛኞቹ ድንጋጌዎች ተፈጻሚ አልተደረጉም፤ተፈናቃዮች ሳይመለሱ ቀርተዋል፣ የተያዙ ቦታዎችም አልተለቀቁም። አደጋው እየከፋ ሄዶ በዝምታ ውስጥ እየተፈጸመ ያለ ዘር ማጥፋት ቀጥሏል” ሲል አክሏል።
በተጨማሪም ፓርቲው፣ ዋስትና ሰጪዎቹ ኃላፊነታቸውን መወጣት አለመቻላቸውንም በማውገዝ፤ “የፕሪቶሪያ ስምምነት ሙሉ በሙሉ እንዲተገበር፣ ኃይሎች ከያዙት ቦታዎች አስቸኳይ ለቀው እንዲወጡና ተፈናቃዮች በሰላም እንዲመለሱ” ጠይቋል።
አስ-
ቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
May be an image of text
 
 
 
 
ኢትዮጵያ ምርቶቿን ከቀረጥ ነጻ በሆነ ሥርዓት ወደ አፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ማዕቀፍ አባል ሀገራት መላክ እንደምትጀምር የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዶ/ር ካሳሁን ጎፌ፤ መስከረም 29 ኢትዮጵያ አህጉራዊ ነፃ የሸቀጦች ንግድ ትግበራን በይፋ ታስጀምራለች ሲሉ ተናግረዋል።
በዚህም ኢትዮጵያ በሚቀጥለው ሳምንት ወደ አፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ማዕቀፍ አባል ሀገራት ለመጀመሪያ ጊዜ ምርቷን ከቀረጥ ነፃ መላክ ትጀምራለች ያሉት ሚኒስትሩ፤ ይህም የንግድ ተወዳዳሪነትን እንደሚጨምር ተናግረዋል።
የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ስምምነት ትግበራ፣ ከንግድ ቀጠናነት ባሻገር የአፍሪካ ዘላቂ ዕድገትን ለማረጋገጥ የጎላ ጠቀሜታ እንደሚኖረው ሚኒስትሩ አክለው ገልጸዋል፡፡
ቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
የውሃ ሚኒስትር ሐብታሙ ኢተፋ፣ ሰሞኑን በሱዳን የተከሠተው ጎርፍ ከሕዳሴ ግድብ ጋር የተያያዘ አይደለም ማለታቸውን አሶሴትድ ፕሬስ ዘግቧል።
ሚኒስትሩ ይህን የተናገሩት፣ አንዳንድ የግብጽ የውሃ ባለሙያዎች፣ የሱዳኑን ጎርፍ በሕዳሴ ግድብ ምክንያት የተከሠተ መኾኑን መግለጣቸውን ተከትሎ እንደኾነ ዘገባው ጠቅሷል።
ጎርፉ የኋይት ናይል ወንዝ ሙላት የፈጠረው ሊሆን ይችላል ያሉት አቶ ሐብታሙ፣ ግድቡ ባይኖር የጎርፍ አደጋው እጅግ የከፋ ሊሆን ይችል ነበር ብለዋል ተብሏል።
ግድቡ እንዲያውም ጎርፉ ከፍተኛ ውድመት እንዳያደርስ በመከላከል ረገድ ቁልፍ አስተዋጽዖ ማድረጉን ሚኒስትሩ መግለጣቸውንም ዘገባው አመልክቷል።
ሚኒስትሩ፣ ኢትዮጵያ ከግድቡ ትርፍ ውሃ አለመልቀቋንም ተናግረዋል ተብሏል።
ዋዜማ-
ቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
በኢትዮጵያ ሀገራዊ የኤችአይቪ ስርጭቱ ካላፉት ዓመታት የተሻለ ቢሆንም፣ ከክልል ክልል፣ ከከተማ ከተማ የስርጭቱ መጠን እንደሚለያይ ተነግሯል።
በተለይ በወጣቶችና ለኤችአይቪ እጅግ ተጋላጭ ተብለው የተለዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ላይ የመያዝ እድሉ በመጨመሩ መዘናጋት እንዳያስከትል ጥንቃቄ እንደሚያስፈልግ የጠቆሙት በኤድስ ሄልዝ ኬር ፋውንዴሽን (AHF) ኢትዮጵያ የኤችአይቪ መከላከልና ምክር አገልግሎት አስተባባሪ እንዲሁም የህብረተሰብ ጤና ባለሙያ የሆኑት አቶ ቢኒያም ባዩ ናቸው።
በጠቅላላው የማህበረሰብ ክፍል ውስጥ ያለው የስርጭት መጠን ከዚህ ቀደም ከ 1 በመቶ በላይ ተሻግሮ የነበረውን በትብብር በመሰራቱ የስርጭቱ መጠን ከጊዜ ወደ ጊዜ እየቀነሰ ቢመጣም፣ በተለይም በስራቸውና በጾታቸው ምክንያት ተጋላጭ የሆኑ ሰዎች ቁጥር ከፍተኛ መሆኑንም አቶ ቢኒያም ይናገራሉ።
በወጣቶች በኩል የኤችአይቪ የመያዝ ቁጥርም ከፍተኛ ነው የሚሉት ባለሙያው፤ በኤችአይቪ መከላከል ላይ የሚሰሩ አዳዲስ ጥናቶች ወጣቶች ላይ ትኩረት ሊያደርጉ ይገባል ብለዋል፡፡
በቅርብ የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲቱዩት በሰጠው መረጃ መሰረት፤ በወጣቶች ላይ ያለው የኤች አይቪ የስርጭት ሁኔታ 1.7 በመቶ እንደሚጠጋ የተነገረ ሲሆን፤ ከትምህርት ቤት ውጪ ባሉ ወጣቶች 2.2 በመቶና በትምህርት ቤት ባሉት ደግሞ 1.3 በመቶ ነው ተብሏል።
በአጠቃላይ ወጣቶችን ስንመለከት ካለው የኤችአይቪ ስርጭት ሁኔታ ከፍ ያለ መሆኑንና ከሌላው የማህበረሰብ ክፍል በተለየ ሁኔታ ከ10 እስከ 24 ዓመት የእድሜ ክልል ላይ ብዙ መስራት እንደሚያስፈልግ በቅርብ ጊዜ እየወጡ ያሉ መረጃዎች እንደሚያሳዩ ባለሙያው መጥቀሳቸውን ሸገር ዘግቧል፡፡
በትግራይ ክልል የአስገድዶ መድፈር ሁኔታዎች ባለመቆማቸው፣ ወላጆች በ12 ዓመት ዕድሜ ላይ የምትገኝ ልጃቸውን እየዳሩ እንደሚገኙ ተገልጿል፡፡
ፆታን መሠረት አድርገዉ በሴቶች ላይ የሚፈፀሙ የኃይል ጥቃቶችን ለመከላከል የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች በተለይም ከአምስት ዓመት ወዲህ ሲሰራ ቢቆይም፣ ከፀጥታዉ ችግር ጋር ተይያዞ ሙሉ ለሙሉ ጥቃቶችን ማስቆም አለመቻሉን ትግራይ ክልልን ጨምሮ በኦሮሚያ ምሥራቅ ሐረርጌ እንዲሁም በአማራ ክልል ደቡብ ጎንደር የተደረገ ጥናት አመላክቷል፡፡
ይህም የተገለፀው የኢትዮጵያ ሴቶች ማህበራት ቅንጅት፣ በትናንትናው እለት "እሷ ትመራለች" በሚል ላለፋት አምስት ዓመታት ሲተገብር የቆየው ፕሮጀክት መጠናቀቁን አስመልክቶ በተዘጋጀው መድረክ ላይ በቀረበው የጥናት ሪፖርት ነው፡፡
በዚህ ወቅት የታዳጊዎችና ስርአተ ጾታ አለም አቀፍ ድርጅት ጥናት የኢትዮጵያ ተወካይና ተመራማሪ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ዶክተር ወርቅነህ አበበ፤ በትግራይ ክልል ከጦርነቱ አስቀድሞ የልጅነት እርግዝናን ለመግታት የግንዛቤ ስራዎች ሲሰሩ መቆየታቸውን ተናግረዋል።
አክለውም፤ ከጦርነቱ በፊትና በኋላ እነዚህ ሁኔታዎች በመቆማቸው፣ በክልሉ እንደ አዲስ በልጅነት የሚከሰት እርግዝና መንሰራፋቱን አስረድተዋል፡፡
ወላጆች ጥቃቱን ለመከላከል በሚል ልጆቻቸውን ለ-ያለእድሜ ጋብቻ እየዳረጉ መሆኑን ባቀረቡት የጥናት ሪፖርት አመላክተዋል፡፡
ችግሩ በተመሳሳይ በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ሃረርጌ፣ በአማራ ክልል ደቡብ ጎንደር ዞን ደብረታቦር፣ በአፋርና ሶማሊያም አሳሳቢ መሆኑን ጠቁመዋል ሲል ሃራምቤ ሬዲዮ ዘግቧል፡፡
May be an image of 3 people and text that says '"End child marriage and say no to teenage pregnancy" CHR ican mUnion mignto lign to meignto WMarriage'
 
 
 
 
 
በሀገረ ስኮትላንድ የሀበሻ ምግብ ቤት የከፈተችው ወይዘሮ ሙና፤ የኢትጵያን ምግቦች በማስተዋወቅ ዝናን አትርፋለች፡፡
በራሷ ሼፍ ሙና የተመሰረተው ምግብ ቤቱ በሀገራችን በብዛት የተለመደውና የኢትዮጵያውያን መለያ የሆነው በየአይነቱ፣ ጥብስ፣ ክትፎ፣ ዶሮ ወጥ፣ ጥሬ ስጋ፣ ዱለትና ሽሮ የመሳሰሉ ምግቦች የሚገኝበት ሬስቶራንት ነው፡፡
ከኢትዮጵያ ተጉዘው ወደ ስኮትላንድ ጎራ የሚሉ ኢትዮጵያውያንን እንዲሁም የኢትዮጵያን ምግብ የለመዱ የሀገሬው ስኮትላንዳውያንን ሞቅ ባለ መስተንግዶ ለዓመታት አገልግሎት ሲሰጥ ቆይቷል፡፡
ወይዘሮ ሙና ከምግብ ቤትና የንግድ ስራዎቿ ባለፈ የኢትዮጵያን ምግቦች በተመረጡ አደባባዮች ይዛ በመውጣት ማስተዋወቋ ደግሞ ሬስቶራንቷን በውጭ ሀገር ከተከፈቱ የሀበሻ ምግብ ቤቶች የተለየ ያደርገዋል፡፡
አንዳንዴ ምግቦችን በነፃ በማቅረብና በማስተዋወቅ እንዲሁም ምግቦች ላይ ልዩ የዋጋ ቅናሽ በማድረግ የኢትዮጵያውያን ምግቦች በስኮትላንድ እንዲታወቁና እንዲለመዱ ማድረግ ችላለች፡፡
ብዙ ጊዜ ምግቦቿን በዋና ዋና ጎዳናዎች ላይ ይዛ በመውጣት እየተመገበች ሌሎችም እንዲመገቡ የምታደርገው የኢትዮጵያ ምግብ አምባሳደሯ ሼፍ ሙና፤ መንገደኞችን ምግቡን በነፃ በማቅመስ ታለማምዳለች፡፡
በዚህም በርካታ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ አትዮጵያውያን እንዲሁም የስኮትላንድ ዜጎች ኢትዮጵያና ምግቦቿን እንዲያውቁ ማድረግ ችላለች፡፡
በዚህ ብቻ ሳታበቃ የኢትዮጵያውያን ብሔር ብሔረሰቦች ባህል፣ ወግ፣ ቋንቋ፣ ጭፈራና የአለባበስ ዘዴ በማስተዋወቅ ለሀገሯ የአምባሳደርነት ሚናዋን እየተወጣች ትገኛለች፡፡
ግለሰቧ የኢትዮጵያን ምግቦች ለማስተዋወቅ በምታደርገው ጥረትም በስኮትላንድ ባይት በተባለው ጋዜጣ እንዲሁም ኢድንበርግ በተባለው የስነ ምግብ ድረ ገፅ ላይ አርዕስት መሆን ችላለች፡፡
-WMCC-
ቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
 
 
 
 
 
 
 
 
Page 9 of 793