Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62

የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ምክትል ዋና ዳይሬክተር የነበሩት አቶ ሰለሞን ተስፋዬ ተሊላ፤ በጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ/ቤት የአስተዳደርና ፍትህ ጉዳዮች ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው ተሾሙ፡፡  ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በትያትር ጥበብ የመጀመርያ ድግሪያቸውን ያገኙት አቶ ሰለሞን፤ በጠ/ሚ ጽ/ቤት የተመደቡበት ሃላፊነት ከፍትህና ከአስተዳደር አካላት ለጠ/ሚኒስትሩ የሚመጡ ሪፖርቶችንና ሰነዶችን መመርመርና 
ሙሉ አጭር መግለጫ ማዘጋጀት፣ እንዲሁም የማጣራት ስራን ያካትታል፡፡ በመምህርነት የሰሩት አቶ ሰለሞን፤ በደቡብ ክልል ማስታወቂያ ቢሮ በኃላፊነት፣ በደቡብ ክልል መገናኛ ብዙሃን በስራ አስኪያጅነት ያገለገሉ ሲሆን በ1998 ዓ.ም በኢትዮጵያ ሬዲዮ የሬዲዮ ዘርፍ ስራ አስኪያጅ የነበሩ ሲሆን ኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ሲዋሀዱ በምክትል ዋና ዳይሬክተርነት ተሾመው ሲያገለግሉ እንደቆዩ ታውቋል፡፡

ለግብፅም ሆነ ለአውሮፓና ለኤሺያ ታህሳስ ልዩ ትርጉም አለው
ብርድ ወደ ሙቀት፤ ከጨለማ ወደ ብርሃን መሸጋገሪያ ወር ነው
ታህሳስ 16 (ዲሰምበር 25)፡ “ፀሐይ የምትወለድበት ቀን” ነው
ዲሰምበር 25 ቀን የልደት ቀን የሚከበርላቸው አማልክት
ናዝራዊው ኢየሱስ፣ የፔርሻው ሚትራ፣ የግብፁ ሖረስ፣ የግሪኮቹ ዲየኒሰስ፣ የቱርክ አቲስ
ሁሉም የአምላክ ልጅ አምላክ ተብለው ይመለካሉ።
ሁሉም ከድንግል የተወለዱ እንደሆኑ ይታመንባቸዋል።
ሁሉም ሞተው ተነስተዋል - ብዙዎቹ በሶስተኛው ቀን።

በአዲስ የአመራር መዋቅር መመራት የጀመረው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በተያዘው የውድድር ዘመን በሚያደርገው እንቅስቃሴ ብንጀምርስ---እንግዲህ ብንዘገይም በያዝነው ሳምንት የብሄራዊ ቡድን አትሌቶች ምርጫ ማካሄድ ጀምረናል፡፡ አሰልጣኞችም በመመደብ ወደ ዋናው ስራ እንገባለን፡፡ ክልሎችና ክለቦች በጥሩ ዝግጅት ሲሰሩ እንደቆዩ እናውቃለን፡፡ በአገር ውስጥ የምናካሂዳቸው ትልልቅ ውድድሮች ይኖሩናል፡፡ አያይዘንም ለኢንተርናሽናል ውድድሮች ሰፊ ዝግጅት እናደርጋለን፡፡ ከአገር ውስጥ ውድድሮች ከፍተኛ ትኩረት የምንሰጠው የጃንሜዳ አገር አቋራጭ ሻምፒዮና አለ፡፡

Saturday, 29 December 2012 09:38

የመንገድ ዳር ሰዓሊው

“በውስጥህ ያለውን ሃሳብ ሳል የሚልህ የለም”
ፒያሳ ከሚገኘው አፍሪካዊያን መፃሕፍት መደብር ወደ ዶሮ ማነቂያ ልኳንዳ ቤቶች ሲያቀኑ ዳገቱን ከመጨረስዎ በፊት በቀኝ በኩል ሲታጠፉ፣ ወደ ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት የሚያደርስ የኮረኮንች መንገድ ያገኛሉ፡፡ በቅያሱ ካሉ ቤቶች በአንዱ ደጅ ላይ አንድ ወጣት ዘወትር ሸራ ወጥሮ በሥዕል ሥራ ተጠምዶ ይታያል፡፡ ሥዕሉ፣ አሳሳሉና ሁለመናው በመንደሩ የሚያልፉ ሰዎችን ቀልብ የሚስብ ነገር አለው፡፡ ጋዜጠኛ ብርሃኑ ሰሙ ከወጣቱ ሰዓሊ ሚሊዮን ታደሰ ጋር ባደረገው ቃለ ምልልስ ስለህይወቱ፣ ስላሳለፈው ውጣ ውረድ፣ ስለ ሙያውና አመለካከቱ ጠይቆት ምላሽ ሰጥቶታል፡፡

Saturday, 29 December 2012 09:32

ውሸትን ፍለጋ!

“በጣም አዝናለሁ መክሊት…ባለቤትሽ መብራቱ በደረሰበት የመኪና ግጭት የተነሳ በጣም የሚያሳዝን እና…ምናልባትም የሚያስገርም ሊባል የሚችል የአንጐል ጉዳት እንዳጋጠማው ማረጋገጣችንን ስገልጽልሽ በእውነት በእውነት እያዘንኩ ነው” አላት የአእምሮ ሀኪሙ ሙልተዘም አንገቱን ግራ ቀኝ እየነቀነቀ፡፡ ባለቤቷ መብራቱ በመኪና አደጋ በደረሰበት አደጋ በሆስፒታሉ ውስጥ ለሶስት ወር ተኝቶ ሲታከም ቆይቷል። ሙሉ አካላዊ ጤንነቱ ቢመለስም በጭንቅላቱ ላይ የደረሰበት ግጭት የተወሰነ የባህሪ ለውጥ እንዳመጣበት ዶክተር ሙልተዘም ተገንዝቧል፡፡ ይኼንኑ ለሚስቱ ለመንገር ነበር ቢሮው ጠርቷት እያነጋገራት የነበረው፡፡

Saturday, 29 December 2012 09:18

ፈልገኸኝ

ቀሰቀስከኝ ተቀሰቀስሁ 
ይኸው ነቃሁ እንደ ልምዴ፡፡
ለካ እኔ ሁሌም ተኚ ነኝ!
ንቃት አልለመደም ልቤ፡፡
ትዝታህን በትራሴ፣ ለመኝታ ተደግፌ፣
ሳልነቃ እንደ ረፈደ፣
ንጋቴ ከእጄ ቢያመልጥም፣
ትራሴ ተነቃነቀ፡፡

* በሰለጠነ አለም ውስጥ ብንሆንም በጨቋኝና ተጨቋኝ ስርአት ውስጥ ነን
* እኛ የምንለው በትክክል እንወዳደር ነው፤ ያንን ደግሞ ኢህአዴግ አልፈቀደውም
* አገሪቱ ውስጥ ትናንሽ አምባገነኖች እየተፈጠሩ ነው፤ ሲስተም መዘርጋት አለበት
ለበርካታ ዓመታት በተቃዋሚ ፓርቲ አመራርነት ያገለገሉት ዶ/ር ኃይሉ አርአያ፤ ከጤና ጋር በተያያዘ ምክንያት ከአንድነት ፓርቲ ሃላፊነታቸው የለቀቁት ከሳምንት በፊት ነበር፡፡ የፓርቲው አመራርም የእሳቸው ምክትል ሆኖ ሲሰራ የነበረውን አቶ ዳንኤል ተፈራን በቦታቸው ተተክቷል፡፡

ባለፈው እሁድ በኢቲቪ የተሰራጨው የነ ሠራዊት ፍቅሬ ፕሮግራም በርካታ ተመልካቾችን አበሳጭቷል። ወይም ብዙዎችን አነጋግሯል ልንል እንችላለን - ለማሳመር ስንሞክር። “እንዳለመታደል ሆኖ፤ እሱ ላይ ነገር ይከርበታል” የምትል አድናቂ አጋጥማኛለች። እንዴት ነው? “ነገር ስለሚከርርበት” ይሆን እንዴ ትችትና ወቀሳ የበዛበት?
የጠፉ ነገሮች ላይ መከራከር
አንድ የስራ ባልደረባዬ እየተንጨረጨረ የተናገረውን ላካፍላችሁ። “ክርክርና ውይይትኮ ደስ ይለኛል። የነ ሠራዊት ፍቅሬ ክርክር ግን፤ ቀሽም ድራማ ሆነብኝ። የሌለ የምናብ አለም ፈጥሮ መከራከር አያስጠላም። ገና ድሮ የጠፉና የሌሉ ነገሮች ላይ፤ ወይም ሊጠፉ የተቃረቡ ‘ብርቅዬ’ ነገሮች ላይ መወያየት ምንም ጥቅም የለውም። የጠፉ ነገሮችን እንዳልጠፉ መቁጠርና መከራከር፤ በከንቱ ጊዜ ማጥፋት ነው።

(ቴኾን ሰብ ምኬር ሰጨም፤ ቴያሰጭም ወጣም ሞተም) የእነሞር ምሣሌያዊ አነጋገር
ቻይናዎች ሁሌም የሚተርቱት አንድ አፈ-ታሪክ አላቸው፡፡
ከዕለታት አንድ ቀን ሱንግ በተባለ የቻይና ቀበሌ ውስጥ ይኖር የነበረ አንድ ገበሬ ሞፈር - ቀንበሩን ሰቅሎ፣ በሬዎቹን ፈትቶ፣ ማሳው ዳር ቁጭ ብሎ ብዙ ሰዓት ያሳልፋል፡፡ በአገሩ የታወቀው አንድ ፈላስፋ ደግሞ የዚህ ገበሬ ነገር ገርሞታል፡፡ ምክንያቱም በዚህ ማሳ አካባቢ ባለፈ ባገደመ ቁጥር ገበሬው እግሩን አጣምሮ እንደተቀመጠ ስለሚያየው ነው፡፡
አንድ ጠዋት ያ ገበሬ እማሳው ዳር እንደተቀመጠ ያ ፈላስፋ ይመጣና፤
“አቶ ገበሬ ደህና አድረሃል?” ይልና የእግዜር ሰላምታ ያቀርባል፡፡

ቀነ ገደቡ ዛሬ ያበቃል
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ በሚያዝያ ለሚደረገው የአዲስ አበባና የአካባቢ ምርጫ ፓርቲዎች የውድድር ምልክት የሚወስዱበትን ጊዜ በሁለት ቀናት እንዳራዘመ ሲገልፅ ፓርቲዎች በበኩላቸው የውድድር ምልክት መውሰጃ ቀነ ገደብ አልነበረውም አሉ፡፡ ምርጫ ቦርድ ከትናት በስቲያ ፓርቲዎችን ለውድድር ለማነሳሳት በሚል የውድድር ምልክት የሚወስዱበትን ጊዜ በሁለት ቀን በማራዘም ዛሬ ታህሳስ 20 ቀን 2005 ዓ.ም ድረስ በቦርዱ ፅ/ቤት በመገኘት ምልክታቸውን እንዲወስዱ ጥሪ አቅርቧል፡፡

Page 4 of 163