ልብ-ወለድ

Saturday, 22 February 2014 13:14

ከመሸ ብትመጡ …

Written by
Rate this item
(2 votes)
“ለሜላት ያለህ ፍቅር ለማክዳ ካለህ ፍቅር እንደሚበልጥ ማቲማቲካል ሎጂክ በመጠቀም በፍጥነት አስረዳ” አለው አቃቤ ህጉ፤ ለተከሳሹ፡፡ ተከሳሹ አይኑን ጣራው ላይ ሰቅሎ መልስ ሲፈልግ ለቅፅበት ከቆየ በኋላ የሸመደደውን እንደሚለፈልፍ ተማሪ መንተባተብ ጀመረ፡፡ “X ኢዝ ኢኩዋል ቱ … እኔ ለእንግሊዝኛ ግጥም ያለኝ…
Rate this item
(4 votes)
ምስኪን ጁዋን! አንድ ቀን በራሱ ጠባቂ እግር ስር አንበረከኩት፡፡ እያጣደፈ ወደ ላይኛው እርካብ ያወጣው የዕድሉ መሰላል ቁልቁል ተሽቀንጥሮ የሚፈጠፈጥበት የውድቀት ዕጣ ፈንታው ወጥመድ እንደነበር ከቶም አልጠረጠረም፡፡ ይህን መሰሉ ውድቀት፤ ነገሮችን ችላ ባልንበት ቅፅበት የሚከሰት ነው፡፡ ችላ የማለት አመል በተጠናወተው ሰው…
Rate this item
(10 votes)
ሉሲ ጭንቅላቷን መስተዋቱ መስኮት ላይ አስደግፋ ያሸለበች ትመስላለች፡፡ ባቡሩ በተንገራገጨ ቁጥር ከመስኮቱ ጋር ትላጋለች። በተደጋጋሚ ከተላጋች በኋላ ዓይኗን ገልጣ ዙሪያዋን መቃኘት ያዘች፡፡ ባቡሩን የሞሉት ጥንዶች ናቸው፤ፍቅረኛሞች፡፡ ዓይኗን መልሳ ጨፈነች- ጥንዶቹን ላለማየት፡፡ በየመሃሉ ባቡሩ ያቃስታል፡፡ የድካም ድምጽ፣ የመታከት እንጉርጉሮ ያስተጋባል፡፡ የእሷና…
Monday, 03 February 2014 13:51

ወንጀል እና ቅጣት

Written by
Rate this item
(7 votes)
ወጠምሻው ከአይገር ባሱ እንደወረደ መሮጥ በመጀመሩ አይናችንን አሳረፍንበት፡፡ እኔ እና ጓደኛዬ የሙዚቃ ቤቱ ደጃፍ ተቀምጠናል፡፡ በጠዋቱ ቅመናል፡፡ አፋችን ተለጉሟል፡፡ ከትራንስፖርት እንደወረደ መሮጥ የሚጀምር ሰው ወይ የቸኮለ ነው፣ ካልሆነ የሆነ ጥፋት ፈጽሟል፡፡ መጀመሪያ፣ አሯሯጡ ሶምሶማ ይመስል ነበር፡፡ ሁለት ወይ ሶስት ሰዎች…
Monday, 27 January 2014 08:40

አደገኛው ውሻ!

Written by
Rate this item
(7 votes)
አለሙ ገዳ እሳት የላሰ ደላላ ነው፡፡ አንደበተ ርዕቱ-አፈ ቅቤ፡፡ ልበ ምላጭ፡፡ ወደሚከራየው ቤት አቀናን፡፡ ከእርምጃውም ከምላሱም እየፈጠነ… “አሁንም ሌጣ ወንደላጤ ነህ! አግባ አግባ እንጂ…. እኔ ጣፋጭ የትዳር ሕይወትን አጣጥሜለሁ፡፡ ነገር ግን ምን ያደርጋል አምና ባለቤቴ ወደ ሳውዲ ተሰደደች “ባስና ሴት…
Saturday, 18 January 2014 11:44

የሦስት ፎቅ ሰማይ

Written by
Rate this item
(7 votes)
“ሳምሶን ወደ ጥንቅሹ እንዴት ተቀየረ?” ሳምሶንን ድሮ ለሚያውቁት ሁሉ አስገራሚ ጥያቄ ነው፡፡ እንደ ሳምሶን አይነት ከይሲ …. ቂጡን በእግሩ የጠረገ ዱርዬ …. አንገቱን የሰበረውን፣ ሰው ቀና ብሎ የማያየውን … ከቤቱ የማይወጣውን ጥንቅሹን እንዴት በቅጽበት ሆነ? መልሱ ሳይሆን ጥያቄው ነው አስገራሚ፡፡…