የግጥም ጥግ

Saturday, 12 September 2020 15:10

የግጥም ጥግ

Written by
Rate this item
(10 votes)
“ልብ ያለው ልብ ይበል”መልካ ምሳለክፋት መርጠን፣ደምብ ጥሰንህግ አፍርሰን፣ብርሃን ትተንሰንዳክር በጨለማ፣ከሰውነት ተራ ወረድንማንነታችን ተቀማ።ፈጣሪን እረስተንግፍ አንፈራ ብለን፣ቀኙን መንገድ ትተንግራውን አጥብቀን፣ገንዘብ ስልጣን ወደንሰይጣንን አንግሰን፣በፈፀምነው ክደትበሰራነው ሥራ፣ያመፃችን ልኬትበፅዋተ ሰፍራ፣ደምወዝ ተከፈለንአጨድን መከራ።ባውቃለሁ ባይነትትዕቢት ተወጥረን፣ቅዱሱን አርክሰንእርኩሱን ቀድሰን፣አውሬ ያልሞከረውንስንት ነገር ሰርተን፣ያጠራቀምነው ግፍሰይጣን አስቀንተን፣ዛሬ ፅዋው ሞልቶበትንፋሽ ጨረሰን።አያድርስ…
Sunday, 06 September 2020 16:13

የግጥም ጥግ

Written by
Rate this item
(5 votes)
 ሀገር ይሁን ሰላምያንቺ ደህና መሆን፣አያስጨንቀኝም፣ ሀገር ይሁን ደህናሰላም ይሁን ቀዬው፣አያሰማኝ እንጂ፣ አንድም የሞት ዜናበመርዶ ነጋሪ፣አልቃሽ እና አስለቃሽ፣ አይመልከት አይኔያንቺን ጤና መሆን፣አትንገሪኝ ደግመሽ ፣ምን ሊጠቅመኝ ለኔ?!ያንቺ ደህና መሆን፣ካሳደገኝ ወገን፣ከሀገር አይበልጥምእንደዚህም ስልሽ፣የራስሽ ጉዳይ፣ማለቴ አይደለምእኔ አንቺን ምወድሽ ፣ሳልጨምር ሳልቀንስ፣ ያገሬን ያህል ነው“ያ ማለት…
Saturday, 29 August 2020 15:32

እስከዚህም ፍቅርሽ

Written by
Rate this item
(14 votes)
እስከዚህም ፍቅርሽከሰንደል ጭስ በላይደምቆ የማይገዝፈውምንሽን ልፃፈው?እስከዚህም ፍቅርሽበጧት የረገፈውከዕድሜ እሬሳ ውጭዋኝታ ምኑን ታውጣውነብሴ ከባለፈው?እስከዚህም ፍቅርሽዘመን ያሳረጠውምኑን አስታውሼሣጌን እየማኩኝእንባዬን ልዋጠው?እስከዚህም ፍቅርሽሲነድፍ ያለሰንኮፍመታሁ ቢልም ለኮፍእንኳንና ሰምበርስምሽስ ማን ነበር?
Tuesday, 25 August 2020 06:31

ሰለሞን ጎሳዬ ገዳ

Written by
Rate this item
(7 votes)
 ኧረ ጉድ ባየህ ወዳጄ ኧረ ጉድ ባየህ ጓዴ!ጓዴ ባለህበት ፅና! ስምንት አመት ሆነው ዝክርህ፤ ይህንን ጉድ ከማየት ያለህበት ነው እሚሻልህ!ገበያው ተደበላልቋል፤ ተገዢው ጊዜውን ይቃኛል ገዢው ግና ተሰናብቷል ስምንት ዓመት ሆነህ ጓዴ፣ ካለፍክ ከዚህ ሀገር እክል ተበዳይ አርፎም ቢተኛ፣ በዳይ ዘራፍ…
Saturday, 08 August 2020 15:23

ሠም እና ሠም

Written by
Rate this item
(5 votes)
አበባው አብቦ ንቡ ገብቶልህእንግዲህ ጉብሌ ማር ካላበላህ...“እንኳንስ ማርና...አላየሁም ሠፈፍ...”እያልህ በመራራ፣ ዜማ ከመንሠፍሠፍ...ያ!... የቀፎው አውራ፣ ማሩን የደበቀውንብ ሆኖ ሲመጣ...ጭስ ሆነህ ጠብቀው!
Saturday, 08 August 2020 15:20

ከዛፍ ስትጣላ...

Written by
Rate this item
(4 votes)
የተነሳብህ ለትየዛፍ ባላንጋራከምትተናነቅከመቶ ቅርንጫፍከሺህ ቅጠል ጋራእንደ ጡንቻ ሁሉስልት በማፈርጠምወርደህ ከግንዱ ጋርአንድ ለአንድ ግጠም!...