ልብ-ወለድ
*… መንገደኛ ሆይ መንገደኛ ትላንት አንጥፍና ዛሬን ደርብና ተኛ ጧት በበርህ በምድራኳየነገ ዛሬ እስኪያንኳኳ!(መንገደኛ፣ የብርሃን ፍቅር፣ ደበበ ሰይፉ)* * *የፍልስፍና አስተማሪዬን በጣም እወደው ነበር፡፡ ሙሉ ሰው ነው፡፡ ጣጣ የማያውቅ፣ ይሉኝታውን ያራገፈ፣ ምንም ነገር የማያስጨንቀውና ስለሰው ልጅ ሰላምና ፍትህ ተጨንቆ የሚያስብ…
Read 3401 times
Published in
ልብ-ወለድ
በክረምቱ ዝናብና ቅዝቃዜ ተሸንፎ፤ጋቢ ተከናንቦና ሶፋ ላይ ተኝቶ ፊልም የሚመለከተዉን ጎረምሳ ከደቂቃዎች በፊት ለሙቀት ብሎ የጠጣውን ሻይ መጠጫ ብርጭቆ ከጎኑ ካለች ጠረጴዛ ላይ ተኮፍሶ ተቀምጦ እይታዉን በከፊል ጋርዶታል፡፡ ጎረምሳው ክረምቱ ከፈጠረበት ስንፍና የተነሳ የሻይ ብርጭቆውን ጠጋ ለማድረግ እንኳን ሳይሞክር ከግርዶሽ…
Read 3844 times
Published in
ልብ-ወለድ
ካሜራው “Close in” አድርጎ ሲቀርብ ትልቅ አልጋ ያሳያል፡፡ አልጋው እራስጌ ላይ “መኝታ ቤት Show” የሚል ፅሑፍ ላይ ያተኩራል፡፡ የአልጋውን የራስጌ ቅርፃ ቅርፅ የሰራው አናጢ የተጣመመ አክሱም ሐውልት፤ የገዘፈ የዋሊያ አይቤክስ ፍየል በሚያስፈራ መልክ አስቀምጧል፡፡ ይኼ የሚታየው መሀል ላይ ከተሰቀለው የጥያቄ…
Read 3783 times
Published in
ልብ-ወለድ
የሰንበት ትምህርት ቤቱ ወጣቶች አንድ የሚያከብሩት ወጣት አለ፡፡ ዮሴፍ ይባላል፡፡ ልክ እንደ ትልቅ ካህን፣ እሱ የሚለው ለእነሱ ሁልጊዜ ትክክል ነው፡፡ የሰንበት ትምህርት ቤቱ መርሐ ግብር እንዳለቀ ወንዶች ሴቶችን መሸኘት ግዴታ ያለባቸው ይመስል በየሴቶች መንደር ይታያሉ፡፡ ጨለም ካለ እና ደፈር ካሉ…
Read 3661 times
Published in
ልብ-ወለድ
ቃሌ…….ሰማይና ምድር የድብቅ ፍቅራቸዉን አጣጥመዉ ከሰዓታት በኋላ ለመገናኘት ተቀጣጥረዉ ተላቀቁ፡፡ በየመንገዱ በሚገኙ ትርፍራፊ ዛፎች ላይ ያሉ ትርፍራፊ ወፎች ያረጀ ያፈጀ ዜማቸዉን እንደ ጥንቱ ያለመሰልቸት ያዜማሉ፡፡ የዉስጣቸዉ ሙቀት ከዉጪዉ ብርድ የበለጠባቸዉ ዉሻዎች በየመንገዱ እየተሯሯጡ ይዳራሉ። ጠንፌ፣ አልማዝና በለጡ እንደጉንዳን ከራሳቸዉ ሰባት…
Read 3933 times
Published in
ልብ-ወለድ
‹‹--አንድ እንሁን፡፡ በአንድነታችን ዉስጥ ግን ክፍተት ይኑር፡፡ በክፍተቱ ዉስጥ ከሰማይ መስኮቶች የሚወጡ ነፋሳት ይደንሱ፡፡ አንዳችን አንዳችንን እናፍቅር፡፡ ፍቅራችንን አንድ ለማድረግ ግን በፍጹም እንዳንሞክር፡፡ ይልቅ ፍቅራችን በነብሶቻችን ዳርቻ መሀከል እንደሚንቀሳቀስ የባህር ዉሃ እንዲጫወት እንተወዉ፡፡ አንዳችን የአንዳችንን ጽዋ እንሙላ፡፡ ከአንድ ጽዋ ግን…
Read 4807 times
Published in
ልብ-ወለድ