ኪነ-ጥበባዊ ዜና

Rate this item
(0 votes)
የታላቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ሰርጌቪች ፑሽኪን 213ኛ ዓመት ልደት ከሰኞ እስከ ቅዳሜ እንደሚከበር የሩስያ የሳይንስ እና ባህል ማዕከል አስታወቀ፡፡ዝግጅቱ በማዕከሉ የፑሽኪን አዳራሽ፣ ሳር ቤት በሚገኘው የፑሽኪን አደባባይ፣ በሩስያ ኤምባሲ እና በኢንተርኮንቲነንታል ሆቴል በሙዚቃ በባሌ ዳንስ እና በሥዕል ውድድር የታጀበ ነው፡፡…
Rate this item
(0 votes)
በአርቲስት ፍቃዱ ተክለማርያም የኪነጥበባት እና የማስታወቂያ ድርጅት በየዓመቱ የሚታተመው የግብይትና መረጃ መጽሐፍ ዘንድሮ ለአራተኛ ጊዜ ታትሞ ባለፈው ማክሰኞ ምሽት በሂልተን ተመረቀ፡፡ በ1999 ዓ.ም በአርቲስት ፈቃዱ ተክለማርያም፣ በኢንጂነር አብይ ፍቃዱ እና በኢንጅነር ብስራት ዳንኤል የተመሠረተው ድርጅት ያስመረቀው መጽሐፍ፤ 856 ገፆች ያሉት…
Rate this item
(0 votes)
አሊያንስ ኢትዮ ፍራንሴ፣ ለኢትዮጵያውያን ከያንያን ለሰጠው አገልግሎት ምስጋና ለማቅረብ ያለመ ኪነጥበባዊ ዝግጅት እንደተሰናዳ ተገለፀ፡፡ “የኪነጥበባት ባለሙያዎች ላከበሩን አክባሪ መሆናችንን ለማሳየትና ከ100 ዓመት በላይ ያገለገለውን አልያንስን ለማመስገን ነው ዝግጅቱን የምናቀርበው” ያለው አርቲስት ዳዊት ፍሬው “የራሳችን ተቋማት ትምህርት እንዲወስዱበት አሊያንስን ማመስገን አስፈልጎዋል”…
Rate this item
(0 votes)
በዓለማየሁ ታዬ (ኢንሹ) የተደረሰውና “ፍለጋ” የተሰኘው አዲስ የወጐችና የግጥሞች መድበል ትላንት ለንባብ ገበያ ቀረበ፡፡ መጽሐፉ 76 ግጥሞችንና ሦስት ወጐችን ያካተተ ሲሆን፤ የተለያዩ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮችን ይዳስሳል፡፡ በ131 ገፆች የተጠናቀረው መጽሐፉ፤ በጃፋር መጻሕፍት መደብር አከፋፋይነት በ20 ብር እየተሸጠ ነው፡፡
Rate this item
(0 votes)
በሃጂ አብዱልፈታህ አብዱላህ የተዘጋጀው የጐርደነ ሴረ (የወለኔ ሕዝብ የባህል ሕግ) መጽሐፍ ነገ በሐገር ፍቅር ትያትር ቤት ትልቁ አዳራሽ እንደሚመረቅ ተገለፀ፡፡ ከጧቱ 3 ሰዓት የሚመረቀውን መጽሃፍ አስመልክቶ ደራሲና አዘጋጁ ሃጂ አብዱልፈታህ ለዝግጅት ክፍላችን ሲናገሩ “የባህል ፍትህ ሥርአታችንን አስመልክቶ ያለን ሀገራዊ እውቀት…
Rate this item
(0 votes)
ዳዊት ነጋሽ ጽፎ ያዘጋጀውና ኩል ፊልም ፕሮዳክሽን ሰርቶ ያቀረበው “የፍቅር ABCD” የተሰኘ የ99 ደቂቃ ርዝመት ያለው ፊልም ዛሬ በአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት ትያትርና ባህል አዳራሽ ይመረቃል፡፡ ከቀኑ 7 ሰዓት ጀምሮ የሚመረቀውን ፊልም ሰርቶ ለማጠናቀቅ አንድ ዓመት ከአራት ወር ፈጅቷል፡፡ ሰሎሞን…