Tuesday, 29 December 2015 07:40

“የፍሬሿ ማስታወሻ” ሰኞ ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

   በአዲስ አድማስ ጋዜጣ “የተማሪና አስተማሪ ወግ” ላይ “የፍሬሿ ማስታወሻ” በሚል በሄርሜላ ሰለሞን በተከታታይ ሲቀርቡ የነበሩ ታሪኮች በመጽሐፍ ተሰባስበው የታተሙ ሲሆን ከነገ ወዲያ ከቀኑ 11፡00 ሰዓት ጀምሮ በዋቢ ሸበሌ ሆቴል ትልቁ አዳራሽ ይመረቃል ተብሏል፡፡ ታሪኩ ፀሐፊዋ በዩኒቨርሲቲ ቆይታዋ ያሳለፈችውን ህይወት የሚያስቃኝና በግል የዕለት ማስታወሻ (ዳያሪ) መልክ ሲከተብ የነበረ እንደሆነ ታውቋል።  በምረቃ ስነስርዓቱ ላይ ደራሲ ሲሳይ ንጉሱ፣ አርቲስት ስዩም ተፈራ፣ አርቲስት ፈለቀ አበበ፣ አርቲስት ፍቃዱ ከበደ፣ ድምፃዊ ቴዎድሮስ ሞሲሳና ሌሎች ወጣትና አንጋፋ ገጣሚያን ሥራዎቻቸውን እንደሚያቀርቡም ተገልጿል። በ191 ገፆች የተቀነበበው መጽሐፉ፤ በ47 ብር ከ50 ሳንቲም ለገበያ ቀርቧል፡፡ ደራሲዋ ከዚህ ቀደም “ሰብስቤና ፈረሱ” “ወርቃማው ወንዝ” እና “ዝርጋዳዋ ዤ” የተሰኙ የህፃናት መጽሐፍትን ማሳተሟም ታውቋል፡፡

Read 1781 times