በቶፓዚዩን ፊልም ፕሮዳክሽን ተዘጋጅቶ፣ በደራሲና ዳይሬክተር አንተነህ አስረስ የተሰራው “በዝምታ” የተሰኘው ፊልም ዛሬና ነገ አዲስ አበባ በሚገኙ በሁሉም ሲኒማ ቤቶች በ8፣ በ10 እና በ12 ሰዓት ይመረቃል፡፡ 850 ሺህ ብር እንደፈጀ የተነገረለት ፊልሙ፤የ1፡35 ርዝመት ያለው ልብ አንጠልጣይ የቤተሰብ ድራማ ነው ተብሏል፡፡
በፊልሙ ላይ እንግዳሰው ሀብቴ፣ አንተነህ አስረስ፣ ናሆም ጌታቸው፣ ፀደንያ ኤፍሬም፣ መራዊት ዮሐንስና ሌሎችም ተዋንያን ተሳትፈውበታል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና