Monday, 04 April 2016 08:45

አርቲስቱ የአጭር ልብወለድ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 ደራሲ ፦ ኦስካር ዋይልድ
                ተርጓሚ ፦ አሸናፊ አሰፋ

      አንድ ምሽት ነፍሱ ‘ለቅጽበት የሚኖር ደስታ’ ሀውልት መቅረጽ ሻተች። ለዚህ ሀውልት የሚሆን ነሀስ ፍለጋ ወደ አለም ተሰማራ። ማሰብ የሚችለው በነሀስ ብቻ ነው።  መጠበብ የሚችለው በነሀስ ብቻ ነው።
በአለም ላይ ያለው ነሀስ ሁሉ ተሰውሯል። በየትኛውም ስፍራ ነሀስ ብሎ ነገር አልነበረም። የነበረው፦ ‘ለዘለአለም የሚፀና ሀዘን’ ሀውልት የተቀረፀበት ነሀስ ብቻ ነው ።
የዚህም ሀውልት ባለቤት ይኸው አርቲስት ነው። ሀውልቱን የቀረፀውም እራሱ ነበር። ይህንኑ ሀውልት በህይወት ይወደው የነበረው ብቸኛ ነገር መቃብር ላይ አኑሮታል። የሰው ልጅን የማይሞት ፍቅር ምልክት ይሆንለት ዘንድና የሰው ልጅን ለዘለአለም የሚፀና ሀዘን ይወክልለት ዘንድ፣ በራሱ እጅ የቀረፀውን ይህን ሀውልት እጅግ ይወደው የነበረው  ነገር መቃብር ላይ አኑሮታል። በአለም ላይም ይህ ሀውልት ከተሰራበት ነሀስ ሌላ ነሀስ አልነበረም።እራሱ ያበጀውን ይህን ሀውልትም ወደ ታላቅ ምድጃ ወስዶ ለእሳት ሰጠው።
‘ለዘለአለም ከሚፀናው ሀዘን’ ሀውልት ነሀስም፦ ‘ለቅጽበት የሚኖር ደስታ’ን ሀውልት ቀረፀ፡፡
 (የእንግሊዝኛው ርዕስ ፦ The Artist)

Read 1301 times